Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 076
المشتركون
+224 ساعات
+37 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
"ወጣቱ በአስተዳደሩ የተለዩ ፀጋዎችን ተጠቅሞ በስራ እድል ፈጠራ የራሱንና የሌሎችን ህይወት ለመቀየር መሰማራት ይገባዋል!"
አቶ ሰኢድ አሊ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ እድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
ዳይሬክተሩ በኢ.ዲ.አይ(ኢስተርን ዴቨሎፕመንት ኢኒሼቲቪ) እየተዘጋጀ በኤፍ ኤም ድሬ 106.1 የሚቀርብ #እኔ ሰላማዊ ነኝ# የተሰኝ የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ በተጋባዥ እንግድነት ቀርበዋል።
በዚህ መሰረት አቶ ሰኢድ አሊ በፕሮግራሙ ላይ ቀርበው በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
✍️ አቶ ሰኢድ በአስተዳደሩ በርካታ የስራ እድል መፍጠር የሚቻልባቸው ዘርፎች መኖራቸው እሙን ነው ይሁን እንጂ ወጣቱ ያሉ አጋጣሚዎችን ተጠቅሞ ስራ ከመፍጠር አኳያ ክፍተቶች መኖራቸውን ገልፀዋል።
✍️ በመሆኑም የስራ ባህልን አሳድጎ ስራን በመፍጠር ብሎም ባሉ የስራ አማራጮች ላይ ስራን ሳይንቁ በመስራት ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ አቶ ሰኢድ አብራርተዋል።
✍️ ድሬዳዋ በሰላምና አብሮ በመኖር በአገር አቀፍ ደረጃ ተሞክሮ መሆን እንደቻለች ይህንን ሰላም ለማስጠበቅና የአስተዳደሩን እድገት እውን ለማድረግ ወጣቱ እራሱን ስራ ፈጣሪና አምራች እንዲሆን መስራት እንደሚገባ አቶ ሰኢድ መልዕክት አስተላልፈዋል።
©️ ኤፍ ኤም ድሬ 106.1
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ የOSH( Occupational Safety & Health) የሙያ ደህንነት ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ጀመረ::
ኮሌጁ እየሰጠ የሚገኘው ይህ የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ በኢንጂነሪንግ እና በጤናው ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን ትኩረት ያደረገ ሲሆን በመስፈርቱ መሰረት ተመልምለው የመጡ ወጣቶችንም ለማሰልጠንና ወደ ኢንዱስትሪው ለማሰማራት በማሰብ በመጀመርያ ዙር 31 ሰልጣኞችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል::
ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የLife skills ስልጠናን ጨምሮ በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባር፣የንድፍ ሃሳብን ጨምሮ ኢንዱስትሪዎች ላይ የትብብር ስልጠናዎችን የሚወስዱ መሆኑም ተግልፇል::
የOSH( Occupational Safety & Health) ስልጠናው በአጫጭር ስልጠና መደብ የሚሰጥ ሲሆን ለቀጣዮቹ አንድ ወራትም የሚቆይ ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ፍትሃዊ ተደራሽነትና ተጠቃሚነትን የሚረጋገጡ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተገለፀ፤
****
የሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በሴቶች፣ በአካል ጉዳተኛ ለሚመሩ ኢንተርፕራይዞች፣አንቀሳቃሾች እንዲሁም ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ለሚያደርጉ ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ከድጋፍ ማእቀፍ አንዱና ዋነኛ የሆነውን የንግድ ክህሎት እና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡
በስልጠናው ላይ የኢንተርፕሩነርሺፕ ምንነትና የንግድ ክህሎታቸውን ሊያዳብሩ የሚችሉና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ጋር ያለባቸውን ክፍተት ከመሙላት አንጻር ያለው አስተዋፅኦ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን ሰልጣኞች ከዚህ በፊት የነበራቸውን እውቀትና ግንዛቤ እንዲያሳድጉ የሚያስችል እድል የፈጠረላቸው ሆኗል፡፡
ኢንተርፕራይዞቹ እርስ በእርስ ያላቸውን መስተጋብር ይበልጥ በማጠናከር የልምድ ልውውጥና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ ያስቻለ ሲሆን ለኢንተርፕራይዞች የተሻለ ትኩረት በማድረግ ውጤት ተኮር ተግባር ማስመዝገብ የሚቻለው ከጊዜው ጋር የዘመነ ስልጠና በመስጠት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ከኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾቹ ጋር በስልጠናው የተሳተፉት የግል ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን ኤጀንሲው ከግል ከኮሌጆቹ ጋር በደረሰው የጋራ መግባባት ለሚያደርጉት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የድጋፍ አይነቶች አቅማቸውን ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ መሆኑም ታውቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ፍትሃዊ ተደራሽነትና ተጠቃሚነትን የሚረጋገጡ ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተገለፀ፤
****
የሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በሴቶች፣ በአካል ጉዳተኛ ለሚመሩ ኢንተርፕራይዞች፣አንቀሳቃሾች እንዲሁም ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ለሚያደርጉ ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ከድጋፍ ማእቀፍ አንዱና ዋነኛ የሆነውን የንግድ ክህሎት እና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡
በስልጠናው ላይ የኢንተርፕሩነርሺፕ ምንነትና የንግድ ክህሎታቸውን ሊያዳብሩ የሚችሉና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ጋር ያለባቸውን ክፍተት ከመሙላት አንጻር ያለው አስተዋፅኦ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን ሰልጣኞች ከዚህ በፊት የነበራቸውን እውቀትና ግንዛቤ እንዲያሳድጉ የሚያስችል እድል የፈጠረላቸው ሆኗል፡፡
ኢንተርፕራይዞቹ እርስ በእርስ ያላቸውን መስተጋብር ይበልጥ በማጠናከር የልምድ ልውውጥና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ ያስቻለ ሲሆን ለኢንተርፕራይዞች የተሻለ ትኩረት በማድረግ ውጤት ተኮር ተግባር ማስመዝገብ የሚቻለው ከጊዜው ጋር የዘመነ ስልጠና በመስጠት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ከኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾቹ ጋር በስልጠናው የተሳተፉት የግል ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን ኤጀንሲው ከግል ከኮሌጆቹ ጋር በደረሰው የጋራ መግባባት ለሚያደርጉት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የድጋፍ አይነቶች አቅማቸውን ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ መሆኑም ታውቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራቱ በርካታ ወጣቶች የስራ ባለቤት መሆናቸው ተገለፀ
በዛሬው እለት የኢፌድሪ ማዕድን ሚንስተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከመስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ ወረዳ ሁለትና ሶስት አስተዳደር በውበት ሳሎን ስራ፣ በእንጨት ስራ ውጤቶች እንዲሁም በህትመት ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶችን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
በአጠቃላይ በድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰቶበት እየተሰራበት በመሆኑ በርካታ ወጣቶች የስራ ባለቤት መሆናቸው ተገልፆ፤ ይህም በቀጣይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተጠቁሟል።
በጉብኝቱ ወቅት ያነጋገርናቸው የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች በበኩላቸው በዚህ መልኩ የስራ ቦታቸው በመጎብኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው፤ አስተዳደሩ ላበረከተላቸው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አመስግነዋል።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን
የኢፌድሪ ማዕድን ሚኒስተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በወረዳ 9 አስተዳደር ስር እየተከናወኑ የሚገኙ የሌማት ቱሩፋት እንዲሁም የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ስራዎችን ጎበኙ፤
በዚህም የወረዳ 9 አስተዳደር በ 5 ወራቶች ውስጥ በአካባቢ ፅዳትና ውበት፣ በስራ እድል ፈጠራ ፣ በክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች እንዲሁም በሌማት ቱሩፋትና በሌሎችም ዘርፎች ያከናወናቸው ስራዎች ላይ ለእንግዶች ገለፃ የተደረገ ሲሆን፤ በመስክም በልብስ ሽያጭ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶችን በተጨማሪም በሌማት ቱሩፋት ስራም የማር ምርትን እንግዶች ተመልክተዋል።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የፈጠራ ሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከል እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች መፍለቂያ ተቋማት መሆን እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ፡፡
በዛሬው እለት የኢፌድሪ ማዕድን ሚንስተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከመስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት የኮሌጁን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
በኮሌጁ የተሰሩ የተለያዩ ስራዎች በልህቀት ማእከል ግንባታ፣ ተቋሙ ከኢንትርፕራይዞች መፍለቂያነት አንጻር፣የፈጠራ ሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከልነት አንጻር ፣ከቴክኖሎጂ ማእከልነት ፣ኮሌጁ በሚያስገነባቸው ፕሮጀክቶች አንጻር እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች የተከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች ላይ ለእንግዶች ማብራሪያና ገለፃ በኮሌጁ ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ በኩል ገለጻ ተደርጓል።
በአጠቃላይ በኮሌጁ የፈጠራ ሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከል እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች መፍለቂያ ተቋማት ላይ ትኩረት ተሰቶበት እየተሰራበት በመሆኑ በርካታ የኮሌጁ ሰልጣኞች የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደ ተግባር በማውረድ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉን በምልከታው ወቅት ተብራርቷል፡፡
የኮሌጁ ኮምሚኬሽን
ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+8
#ዜና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ከሌጅ መካኒክ አሽከርካሪዎችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡
በሀገራችን እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳድር መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ አሽከርካራችን ማፍራት ማፍረት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ያጠናቀቁ አሽከርካሪዎችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡
በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንዳሉት ይህ ስልጠና መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ ዋናው አላማ ነው በተጨማሪም ብቃት ያለውና ተወዳዳሪ አሽከርካሪ በማፍራት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያግዝ ትልቅ ስልጠና ነው ይህንን ስልጠና በምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመሰጠቱ ልባዊ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆን በንግግራቸውም የትራፊክ አደጋ በሰው ህይወት፣በንብረት በአጠቃላይ አምራች የሆነውን ማህበረሰብ የሚጎዳ ነው ይህንን አደጋ ደግሞ ለመቀነስ ብቁና ተወዳዳሪ አሽከርክሪዎችን ማፍራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን አያይዘውም ብቁ እና ተወዳዳሪ አሽከርካሪዎችን ለማፍራት ደግሞ ዛሬ እንደተመረቃችሁት አይነት አሽከርካሪዎችን ማፍራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ይህንን ስልጠና እንዲሳካ ላበረከቱ በሙሉ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
መካኒክ አሽከርካሪዎች ስልጠና ይህ የመጀመሪያ ዙር ሲሆን በዚህም ስልጠና 47 አሽከርካሪዎች የተሳተፉበት እንደሆነና ሁለተኛ ዙር ስልጠናም እንደተጀመረ በእለቱ ተገልጿል ፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ ፌደራል ማረሚያ ቤት ውስጥ ላሉ የህግ ታራሚዎች ለተከታታይ 7 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን የህይወት ክህሎት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና አጠናቀቀ፡፡
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት የተገኙትና ስለ ስልጠናው ያብራሩት በድሬዳዋ ፌደራል ማረሚያ ዳይሬክተር የሆኑት ረ/ኮምሽነር ሙላት ጫንያለው ሲሆኑ በንግግራቸውም ከኮሌጁ ጋር ከዚህ ቀደም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመናል ዛሬ የተጠናቀቀው የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠናው የስምምነቱ አንድ አካል ነው ያሉት ረ/ኮምሽነሩ አያይዘውም ይህ ስልጠና ማረሚያ ቤት ውስጥ ያሉ ታራሚዎች ባህሪያቸውን እንዲያሻሽሉ፤ወደ ህብረተሰቡም ሲቀላቀሉ ግላዊ ማህበራዊ ስሜቶቻቸውን እንዴት ማንጸባረቅ እንደሚችሉ ያሳየ ስልጠና ነው ብለዋል፡፡ለዚህ ስልጠና መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የኮሌጁ ኃላፊዎች እንዲሁም መምህራን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በስልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና ለታራሚዎች መሰጠቱ የግል ክህሎቶቻቸውን እንዴት ማዳበር እንዳለባቸው እንዲሁም በቀጣይ ከማህበረሰቡ ጋር ሲቀላቀሉ በራሳቸው የሚተማመኑ ከቀድሞ ስህተታቸው ተምረው ማህበረሰቡን እንዴት መካስ እንዳለባቸው ያስገነዘበ ስልጠና ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ታራሚዎችን ስብእና መገንባት የአንድ ተቋም ብቻ ሳይሆን ሁሉ አካላት በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ይህ ስልጠና በህይወት ክህሎት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በተመረጡ ሞያዎች የክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡
ይህ የመጀመሪያ ስልጠና ለ73 ታራሚዎች ለ7 ቀን የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ከአስተባባሪዎቹ መረዳት ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምንኬሽን
ታህሳስ 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
