Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 089
المشتركون
+324 ساعات
+257 أيام
+1730 أيام
أرشيف المشاركات
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት የመጀመሪያው 6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሄደ ።
==========================
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች በስራቸው የተደለደሉትን የአስተዳደሩ ተቋማት እቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆኑ በዛሬው እለትም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድ ና ኢንዱስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ክትትልና ቁጥጥር ከሚያደርግባቸው የአስተዳደሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነውን የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት የ2016 በጀት አመት የመጀመሪያውን የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ና የመውጫ ውይይት አድርጓል ።
ቋሚ ኮሚቴው በቢሮው ስር ያሉ ፕሮጀክቶች እና ከስራ እድል ፈጠራ ጋር ተያያዝነት ያላቸውን ተግባራት አፈፃፀም ያሉበትን ደረጃ ባለፉት ቀናት የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ ቆይቶ በዛሬው እለትም ከቢሮው ማኔጅመንት አባላት ጋር በተቋሙ የግማሽ አመት እቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአፈፃም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በውስንነት የተለዩ ጉዳዮች መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የመውጫ ግብረ መልስ ሰጥቷል።
በአጠቃላይ ቢሮው በ2016ዓ/ም የ6 ወር እቅድ አበረታች አፈፃፀሞች መታየቱንና በዘርፉ በውስንነት የተለዩትን እንዲታረሙ በማድረግ በቀጣይ ሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ በማስቀጠል በስፋትና በጥራት የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
©️ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን የ2016 በጀት አመት የመጀመሪያው 6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሄደ ።
==========================
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች በስራቸው የተደለደሉትን የአስተዳደሩ ተቋማት እቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆኑ በዛሬው እለትም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድ ና ኢንዱስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ክትትልና ቁጥጥር ከሚያደርግባቸው የአስተዳደሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነውን የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት የ2016 በጀት አመት የመጀመሪያውን የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ና የመውጫ ውይይት አድርጓል ።
ቋሚ ኮሚቴው በቢሮው ስር ያሉ ፕሮጀክቶች እና ከስራ እድል ፈጠራ ጋር ተያያዝነት ያላቸውን ተግባራት አፈፃፀም ያሉበትን ደረጃ ባለፉት ቀናት የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ ቆይቶ በዛሬው እለትም ከቢሮው ማኔጅመንት አባላት ጋር በተቋሙ የግማሽ አመት እቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአፈፃም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በውስንነት የተለዩ ጉዳዮች መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የመውጫ ግብረ መልስ ሰጥቷል።
በአጠቃላይ ቢሮው በ2016ዓ/ም የ6 ወር እቅድ አበረታች አፈፃፀሞች መታየቱንና በዘርፉ በውስንነት የተለዩትን እንዲታረሙ በማድረግ በቀጣይ ሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ በማስቀጠል በስፋትና በጥራት የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
©️ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ካሉ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ጋር ውይይት ተደረገ።
በዚህም ውይይት ላይ የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎችና የአንድ ማዕከል አስተባባሪዎች የተገኙ ሲሆን አጠቃላይ ስለሚሰጠው አገልግሎት በተለይም ስራ ፈላጊዎችን ከስራ ጋር ለማስተሳሰር በመጀመሪያው ዙር “ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የማጠቃለያ ስራዎች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ተወያይተዋል።
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ አንድ ማዕከላቱ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለዜጎች ስራ መፍጠር ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግና ከዚህ ጋር በተያያዘ መረጃዎች በጠራ መልኩ ተይዘው በየአካባቢው ያለውን አቅምና ጸጋ ሊጠቀሙ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
አያይዘውም በአስተዳደሩ የሚገኙ ዜጎችን በተለይም አብዛኛውን ሴቶች ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገው የመጀመሪያው ዙር “ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የተገኘውን ውጤት በሚያሳይ መልኩ በደማቁ የማጠቃለያና መዝጊያ መርሃግብር ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ከተለያዩ ተቋማት ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156 ላይ ገለጻ የተሰጣቸው ሲሆን በሚገጥሟቸው ተጨባጭ የሁለትዮሽ ጉዳዮችን በማንሳት ውይይት ማድረግ ተችሏል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ ይፈጥራል፡፡
ዳይሬክቶሬቱም የኢንደስትሪ ሰላም ዝርጋታ ስራዎች በተለያዩ ተቋማት በአሰሪውና ሰራተኛው መካከል መቀራረብና መነጋገር እንዲፈጠር ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል በመሆኑም እየተገኙ ያሉ ውጤቶች ምን እንደሚመስሉ በቀጣይ የምናስቃኛችሁ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 14/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በቤተክርስቲያኗ ሥርዓት እና ትውፊት መሰረት የ2016 ዓ/ም የጥምቀት በዓል በድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ በደማቅ ሁኔታ ተክብሯል።
በዓሉንም በማሥመልከት በዓሉ ላይ ለተሳተፋ ምእመናን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተለያዩ ድጋፎችን ያደረገ ሲሆን ድጋፉንም የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ የኮሌጁን ማህበረሰብ እና ማኔጅመንቱን በመወከል በትናው እለት ያሥረከቡ ሲሆን በዛሬው እለትም የኮሌጁ ዲን ም/ዲኖች እንዲሁም የማኔጅመንት አባላቶችና የኮሌጁ ማህበረሰብ በጋራ በመሆን በዓሉን ለሚያከብሩ ምእመናን ድጋፋን ሲያድሉ ውለዋል::
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 11/2016 ዓ•ም ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የሚገኘው የፌደራል ማረሚያ ቤት ለታራሚዎች በሚሰጠው አጫጭር ስልጠና ላይ የ2016 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠናዉን ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ ክትትልና ድጋፍ ተደረገ፡፡
በዚህም ድጋፍና ክትትል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲው የሚሰጡ ስልጠናዎች ሁሉንአቀፍና አካታች መሆናቸውን በሚያሳይ መልኩ ማረሚያ ቤቱ በእርምት ላይ የሚገኙ ዜጎችን በማሰልጠንና በማብቃት ላይ ሀገርና ህዝብን የሚጠቅሙ በማድረግ ሂደት ውስጥ ትምህርትና ስልጠናው ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ የሚያስችል አቅምን እንዲፈጥር ታሳቢ ያደረገ ነው፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ማረሚያ ቤቱ እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀው በምልከታው የታዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች በቀጣይ ሁለቱን የመንግስት ኮሌጆች በማስተባበር ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል፤
አቶ ታሪኩ ለገሰ አክለው ይሄው የድጋፍና ክትትል ኤጀንሲው እውቅና በሰጣቸው በአስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት ላይ ተመሳሳይ መልኩ የሚደረግ መሆኑን አስታውቀዋል፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 9/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ለአንድ ማዕከል እና ለማይክሮ ፋይናንስ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡
በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንዲሁም ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድር ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ እንዲመለስ በማድረጉ ረገድ ደግሞ የሚመለከታቸው አካላት ቁርጠኝነት አለመኖር በሰፊው ተነስቷል፡፡
በማጠቃለያውም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እንደተናገሩት የሚመለከታቸው አካላት በሚመለከታቸው ልክ ትኩረት በመስጠት በቅንጅት የማስተካከሉን ስራ መረጃዎችን ከማጥራት እስከማስመለስ ያለውን በመናበብ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 9/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ለአንድ ማዕከል እና ለማይክሮ ፋይናንስ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡
በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንዲሁም ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድር ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ እንዲመለስ በማድረጉ ረገድ ደግሞ የሚመለከታቸው አካላት ቁርጠኝነት አለመኖር በሰፊው ተነስቷል፡፡
በማጠቃለያውም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እንደተናገሩት የሚመለከታቸው አካላት በሚመለከታቸው ልክ ትኩረት በመስጠት በቅንጅት የማስተካከሉን ስራ መረጃዎችን ከማጥራት እስከማስመለስ ያለውን በመናበብ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 9/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የምረትና ምርታማነት ፍልስፍና ወይም ካይዘን በስልጠና ተቋማት ውስጥ መተግበር በስልጠና ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን በመሙላት የስልጠና ስርአቱን ያስጠብቃል ተባለ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምረትና ምርታማነት ፍልስፍና ወይም ካይዘን በኮሌጁ ውስጥ ብሎም በኢንተርፕራይዞች ላይ ለመተግበር የሚያስችል ስልጠና ለትምህርት ክፍል ጠተሪዎች እና ተወካዮች እንዲሁም ለተለያዩ የስራ ክፍል አስተባባሪዎች ስልጠና በዛሬው እለት ሰጠ፡፡
በስልጠናው ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉትና ስልጠናውን ያስጀመሩት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም የምረትና ምርታማነት ፍልስፍና ካይዘን በኮሌጃችን ውስጥ መተግበር መቻል በስልጠና ስርአቱ ላይ እንዲሁም ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ላይ የሚያመጣው ለውጥ ከፍተኛ ስለሆነ ሁሉም የኮሌጁ ሰራተኞች እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍል ተጠሪዎች በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
አያይዘውም ኮሌጃችን በአንዳንድ የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የስራ ክፍሎች እየታየ ያለው የካይዘን አተገባበር ሁኔታዎች ለሌሎች መነቃቃትን የሚፈጥርና ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡
የምረትና ምርታማነት ፍልስፍና ወይም ካይዘን ስልጠና እንደተጠናቀቀ በኮሌጁ ውስጥ ካይዘን ትግበራ በተደራጀ መልኩ መስራት የሚቻልበትን አደረጃጀት በመፍጠር የከልቡ አደረጃጀት በማዘጋጀት ወደስራ እንደሚገባ በስልጠናው ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 09/05/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
