Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 065
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችንና የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ሌሎች ኮሌጆች በአካባቢያቸው ተግባራዊ ሊያድርጓቸው ይገባል ተባለ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት አዘጋጅነት ከመጋቢት 23 - 25 ቀን 2026 በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የቀጣይ 15 አመት እቅድ 2ተኛ ዙር ግምገማ እና መሪ እቅድ ልማት አውደ ጥናት ተሳታፊዎች በኮሌጁ የተከናወኑ ተግባራትን እና የለውጥ ስራዎች ተዘዋውረው ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ላይ በመገኘት የኮሌጁን ምርጥ ተሞክሮና የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን ያጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት ኮሌጁ ከስልጠና ባሻገር learning factory እንዲሆን ከመንግስትና ከግል ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል ለዚህም ማሳያው ለረጅም አመት አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየውና የከተማ አስተዳደሩ ለኮሌጁ የተለያዩ ምርቶችን እንዲያመርት የሰጠው የተርኒኪ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በኮሌጁ የሚገኘው የEASTRIP ፕሮጀክት ሃብትን በማፈላለግ ለኮሌጁ ተጨማሪ ግብአት እንዲሆኑ ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር የተገኙ ገብአቶች በተጨማሪም የICT ልህቀት ማእከሉ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ አያይዘውም እነዚህ ግበአቶች ወደ ኮሌጁ መምጣታቸው ስልጠናዎችን በብቃትና በጥራት መስጠት እንድንችልና ለማህበረሰቡ ተደራሽ እንድንሆን አድርገውናል ብለዋል፡፡
የኮሌጁን ተሞክሮ ለመጎብኘት የተገኙትን እንግዶች የመሩት ዶ/ር ተሾመ እንዳሉት ደግሞ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችንና የተገኙ ልምዶችን በመቀመር ሌሎች ኮሌጆች በአካባቢያቸው ተግባራዊ ሊያድርጓቸው ይገባል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 16/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በEASTRIP ፕሮጀክት የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል እና ዘላቂ መሪ እቅድ በማዘጋጀት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ለማህበረሰቡ ተደራሽ የሚሆኑበትን አሰራር ሊቀይሱ ይገባል ተባለ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት አዘጋጅነት ከመጋቢት 23 - 25 ቀን 2026 የሚቆየው በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የቀጣይ 15 አመት እቅድ የደረሰበትን 2ተኛ ዙር ግምገማ እና ማስተር ፕላን ልማት አውደ ጥናት መርሀ ግብር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል::
በአውደ ጥናቱ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ኃላፊ ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት የአውደ ጥናቱ አላማ በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6ቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች በጋራ በመሆን የ15 አመት መሪ እቅዶቻቸውን የሚገመግሙበትና ግብአት የሚሰበሰብበት እንደመሆኑ መጠን በዚህ አውደ ጥናትና የእቅድ ግምገማ መድረክ ላይ የተሳተፉችሁ አካላቶች ገንቢ ሚናችሁን እንደትወጡ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በተያያዘም የግምገማ ቡድኑን የሚመሩት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት የተወከሉት ዶ/ር ተሾመ እንዳሉት በEASTRIP ፕሮጀክት የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል እና ዘላቂ መሪ እቅድ በማዘጋጀት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ለማህበረሰቡ ተደራሽ የሚሆኑበትን አሰራር በመቀየስ የስልጠና ተደራሽነታችንን ልናሰፋ ይገባል ብለዋል፡፡
በዚህም አውደ ጥናት ላይ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም ከዚህ በፊት ሲሰራቸው የነበረውን ስራ እንዲሁም በቀጣይ 15 አመታት ሊደርስበት ያሰበውን የልህቀት ማእከልነት ለገምጋሚው ቡድን ያቀረበ ሲሆን ግምገማውን ያደረገው ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተወከለው ቡድንም ኮሌጁ እስካሁን ሲሰራቸው የነበሩና በቀጣይ በስፋት ሊሰራቸው ያሰባቸው ስራዎች ወሳኝና ኮሌጁን በተለየ አይነት መልኩ ወደፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ስራዎች እንደሆኑ ገልጿል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በ EASTRIP ፕሮጀክት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ልህቀት ማእከል ኮሌጁን ከሌሎች ኮሌጆች በተሸለ ለኢንዱስትሪዎቹ ግብአት መሆን የሚችል ሰልጣኞችን በማብቃት ረገድ ትልቅ ስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገለጸ፡፡
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣ከአለም ባንክ፤ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ፤የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች፤የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት PIU አባላት እንዲሁም ከኮንትራክተሩና አማካሪ ድርጅቱ በተውጣጣ የSupervision team የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም እና ኮሌጁ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት ገመገሙ፡፡
በኮሌጁ እየተተገበረ የሚገኘውየEASTRIP ፕሮጀክት ኮሌጁን ከሌሎች ኮሌጆች በተሸለ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መሆን የሚችል ሰልጣኞችን በማብቃት ረገድ ትልቅ ስተዋጽኦ አለው ያሉት ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የኮሌጁን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም ሰልጣኞች በኮሌጃችን በሚቆዩበት ወቅት ክህሎትን ብቻ ሳይሆን የስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅርበት እየሰራን እንገኛለን በኮሌጁ የሚገነባውም የልህቀት ማእከል በሚቀረው ጊዜ ተጠናቆ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል ኮሌጁ የድርሻውን ሚና የሚወጣ ይሆናል ብለዋል፡፡
ልኡክ ቡድኑ የህንጻ ግንባታውን እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ግንኙነት በኮሌጁ እንዲሁም በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታና በቀጣይ በሚቀሩ ጊዜያት የሚሰሩ ስራዎች የአማካሪ ድርጅቱ መሐንዲስ ዮሃንስ እቁባይ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ከሪፖርቱና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጠ ሲሆን በቀጣይም በሚቀረው ጊዜ ግንባታው ተጠናቆ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል ሁሉም ባለድርሻ አካላት የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
በመደበኛ ከሚሰጠው ስልጠና በተጨማሪ በተለያዩ ገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናዎች የአካባቢውን ወጣቶች በማብቃት የኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ኮሌጁ እየሰራ እንዳለ ገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ05 ወረዳ የተውጣጡ በተለያዩ የሙያ መስኮች ለመሰልጠን ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች በዛሬው እለት ተቀበለ፡፡
ኮሌጁ በመደበኛ ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች በተጨማሪ የተለያዩ ገበያ ተኮር ስልጠናዎችን በማዘጋጀት ወጣቶቸን የሙያ ባለቤት እንዲሆኑና የኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል ያሉት በአቀባበሉ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም በአጫጭር ስልጠና የምናሰለጥናቸው ሰልጣኞች በኮሌጁ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አካባቢዎች ባዘጋጀናቸው Mobile TVET ማእከላት ጭምር ስለሆነ ስልጠናችንን በደንብ ለማህበረሰቡ ተደራሽ እንድንሆን አስችሎናል ብለዋል፡፡
በዛሬው እለት በኮሌጁ ለመሰልጠን ፍላጎት ኖሯቸው የመጡት የ05 ወረዳ ወጣቶች በኮሌጁና በአካባቢያቸው በተዘጋጁ የስልጠና ማእከላት የሚሰለጥኑ ሲሆን መሰል ስጠናዎች ከዚህ በፊት በወረዳ 08 እና በወረዳ 09 ለሚገኙ ወጣቶች በተለያዩ ገበያ ተኮር ስልጠናዎች በአካባቢያቸው በተዘጋጁ የስልጠና ማእከላት መስጠት እንደተቻለ በእለቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 14/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
የስልጠና ሂደቱን ለማቀላጠፍ የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን የዲጂታል ሲስተሞችን በመጠቀም የተቀላጠፈ ለማድረግ እየሰራ እንዳለ ኮሌጁ ገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አጠቃላይ አሰራር በዲጂታል ሲስትም ለመቀየር በማሰብ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል እና በኮሌጁ በቀጣይ ስለሚተገበረው ሲስተም ላይ ትኩረቱን ያደረገ የግንዘቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት ለኮሌጁ ማህበረሰብ ተሰጠ፡፡
ኮሌጁ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንዲሁም አጠቃላይ የተቋሙን አሰራር በዲጂታል ስርአት ለመተካት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንዳለ የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ በመድረኩ በመገኘት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም ዘመኑ ቴክኖሎጂን የመጠቀም ብቻ ሳይሆን አሰራሮችንም በዲጂታል ስርአት በመቃኘት ሊተገበሩበት የሚገባ ወቅት እንደመሆኑ መጠን ኮሌጃችንንም ዘመናዊና ተወደዳሪ እንዲሆን ሁሉንም አገልግሎቶቻችንን በዲጂታል ስርአት ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ይህም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲሳካ የበኩላችንን ድርሻ እንደንወጣ ያስችለናል ብለዋል፡፡
የግንዛቤ ስልጠናው ከኢትዮ ቴሌኮም በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን የኮሌጁ አሰራር በዲጂታል ሲስተም ሲቀየር በምን መልኩ ተግባራዊ ይሆናል የሚለውና የተለያዩ የስራ ክፍሎች ሲስተሙን እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው በዝርዝር ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን::በቀጣይ ቀናትም ሲስተሙ የሚተገበርባቸው ሁሉም ስራ ክፍሎች ላይ በመገኘት የሲስተሙን አጠቃላይ አተገባበርና አጠቃቀምን በተመለከተ የተግባር ስልጠና እንደሚሰጡም ለማወቅ ተችሏል::
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 14/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል ፈጥር የሂጅራ አመት አደረሳችሁ ኮሌጃችን ከድሬ TV ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የበአል ፕሮግራም የኢድ አል ፈጥር በአል ይጠብቁን
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ከመንግስትና የግል ኮሌጆች የተወጣጡ አሰልጣኞች ሲዘጋጅ የነበረውን የተቋም ውስጥ ምዘና መመዘኛ መሳሪያዎች (Institutional Assessment) በመገምገም አጠናቀቀ፡፡
በዚህም መመዘኛ መሳሪያዎቹ ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ያገኟቸውን እውቀቶች፣ ክህሎቶችና አመለካከቶች በተቋም ደረጃ የሚመዘኑበት ሲሆን ቲዎሪውን በተግባር የመለወጥ አቅምን ስለሚፈትሽ ሰልጣኞች በስራው አለም ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝ፣ የመማር ማስተማር ሂደቱንም የሚያሻሽል ይሆናል፤
ይህም ምዘና በብሔራዊ ደረጃ የሚሰጠውን የብቃት ምዘና (COC) ከመውሰዳቸው በፊት ለስራው የሚፈለገውን ብቃት ማሟላታቸውን ለማረጋገጥና ከደረጃ ወደ ደረጃ ለመሸጋገር የሚሰጥ ምዘና ነው ፡፡
በአጠቃላይ ኮሌጆቹ ብቁና ጥራት ያለው ሰልጣኝ እያፈሩ መሆኑን ለማረጋገጥና ለኢንዱስትሪዎች ዝግጁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለማቅረብ የሚጠቅም ሲሆን የተዘጋጁትም የምዘና መሳሪያዎች፣ በኤሌክትሪክ፣ አይሲቲ፤ በሜካኒክስ፣ በአውቶሜካኒክስ፣ በኮንስትራክሽን ፕለምቢግ ኢንስታሌሽን፣ በቢዝነስ ዘርፍ ማርኬትንግ እና የሴክረተሪያል እና የቢሮ አስተዳደር፣ በጤና ነርሲንግ እና ፋርማሲ ቴክኖሎጂ ሲሆኑ የምዘና መሳሪያዎቹም ተዘጋጅተው የሚቀመጡ ሳይሆን በስራ ላይ በማወል ተግባራዊ የሚደረጉ መሆኑን ማወቅ ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 9/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለአስተዳደሩ ሥራ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱ ተገለጸ፤
በስልጠና መክፈቻው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደገለፁት፤ ቢሮው ለነባርና አዳዲስ የወረዳ ሥራ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች አዲሱን እሳቤ ለማሰረፅና ተቀናጅቶ በመስራት ወደ ተግባር ለማውረድ የተለያዩ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙና በዚህም ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ የተቀረፁ እሳቤዎች ወደ መሬት ወርደው የልማት ፀጋዎቻችንን አልምቶ መጠቀም በሚያስችል አግባብ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
አቶ ሰኢድ አሊ አክለው የዘርፉ የአዲሱ እሳቤዎች ዓላማ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር ያሉ ማነቆዎችን በመፍታትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የታለመውን ሀገራዊ ልማትና ብልጽግናን እውን ማድረግ ሲሆን የወረዳ የሥራ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች የእሳቤዎቹን ዓላማና ግብ በአግባቡ ተረድተው ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 9/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ የስራ ሂደቶችና ክፍሎች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወር የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር አጠናቀቀ::
የ2018 የመጀመርያ ግማሽ አመት የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩ በድጋፍና ክትትል ቡድኑ አማካኝነት ባለፉት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን በዚህም አጠቃላይ በኮሌጁ የሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎችን ተደራሽ በማድረግ በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል::
በድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩ ወቅት በኮሌጁ የሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶች፣ ደጋፊ ስራ ሂደቶች፣ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችን ጨምሮ አጠቃላይ የስራ ክፍሎችን ተደራሽ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በድጋፍና ክትትል ቼክሊስት መሰረት የተለዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠል እንዲሁም የተስተዋሉ ውስነቶችንም ለማሻሻል የሚያግዝ ግብረ-መልስ ለስራ ሂደቶችና ክፍሎች ተሰጥቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መጋቢት 9/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
