Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 063
المشتركون
-224 ساعات
-77 أيام
+130 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
#ዜና /የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ADRA Ethiopia ፕሮጀክት በSolar PV Installation & maintenance ሰልጥነው በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች በጸሐይ ብርሃን የሚሰራ የእህል ወፍጮ በመስጠት ለወጡበት የገጠር ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን እድል አመቻችቷል::
#DGC ህዳር 16/2018
ነዋሪነታቸው በድሬዳዋ አስተዳደር ቃልቻ የገጠር ቀበሌ የሆኑት እና በSolar PV Installation & maintenance (በጸሐይ ብርሃን የኃይል ምንጭ መሳሪያዎች ገጠማና ጥገና) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ADRA Ethiopia ፕሮጀክት ሰልጥነው በማህበር ለተደራጁ አስራ ስምንት ወጣቶች በጸሐይ ብርሃን ኃይል የሚሰራ የእህል ወፍጮ የጀርመን የተራድኦ ድርጅት ADRA Germany ዋና ሀላፊ በተገኙበት የተበረከተላቸው ሲሆን ወጣቶች ለአካባቢያቸው ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማገዝ ድጋፉን ማበርከታቸውን የተርአድዎ ድርጅቱ የምስራቅ አፍሪካ አስተባባሪ አቶ ዳዊት መሃሪ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው የADRA Ethiopia ከኮሌጁ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation & maintenance ስልጠና ወጣቶችን በማብቃት ራሳቸውን ማህበረሰባቸውን እንዲጠቅሙ በማድረግ በኩል ትልቅ አስተዋጾ እያበረከተ መሁኑን ገልጸው ፤ ወጣቶቹ ባገኙት በዚህ እድል ወደ ተሻለ ምእራፍ በመሸጋገር አርአያ ለመሆን ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል ፡፡
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ADRA ፕሮጀክት በSolar PV Installation & maintenance (በጸሐይ ብርሃን የኃይል ምንጭ መሳሪያዎች ገጠማና ጥገና) ሙያ እስካሁን ከ120 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማሰልጠን ማስመረቁ ይታወቃል ፡፡
#DGC
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የእድገት ደረጃ እና ከፍተኛ የማደግ አቅም ያላቸውን ኢንተርፕራይዞች መረጃ ለመሰብሰብ የተዘጋጁ ቅጾች ላይ ከገጠር ወረዳ አንድ ማዕከላት ከተወጣጡ አስተባበሪዎችና ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሄደ፡፡
በዚህም ኢንተርፕራይዞች ሲመዘገቡ ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም የተሰማሩበትን ዘርፍና ያለባቸውን ክፍተት በሚለይ መልኩ ቅጾቹን መሰረት በማድረግ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በቀጣይም በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጨባጭ ስራ ላይ የሚገኙ ለመለየት የሚያስችል መረጃዎች የሚሰበሰቡ ይሆናል፡፡
በተያያዘ በአስተዳደሩ ገጠር የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን ከመለየትና ከማደራጀት በዘለለ አቅማቸውን በማጎልበት የአንቀሳቃሾች አመለካከታቸውን ሊቀይር የሚችል ስልጠና መስጠት፣ የብድር አቅርቦትና አመላለስ ላይ ትኩረት ማድረግ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር በመፍጠር የድጋፍ ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የዳይሬክቶሬቱ ተወካይ ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ትውልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሠራር!"
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ትውልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሠራር!" በሚል በአለምና በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ ከቢሮው ማህበረሰብ ጋር ተወያይቷል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አሚን አብዱላሂ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት የሙስና ምክንያት የሆነውን የስነ-ምግባር ዝቅጠትንና ስግብግብነትን ለማረም እና አይቶ እንዳላየ ማለፍን ለማስቆም የቢሮው ሰራተኞችና አመራሮች ሚና ላቅ ያለ መሆኑን አስረድተዋል።
የፀረ-ሙስና ትግሉ በቢሮው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘንድ እንዲቀጣጠልና በዋናነት የስነ ምግባር ግንባታው የድርሻውን ተወጥቶ የሚታመንና የሚተማመን ሰራተኛና አመራር መፍጠር እንደሚገባ በመድረኩ ውይይት ተመላክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
ከቴክኖሎጂ ፈጣሪነት እስከ አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት.........
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በተሳተፉበት አለም አቀፍ ውድድር አሸናፊ ሆነዋል::
"የክህሎት ኢትዮጵያ" ፕሮግራም ተሳታፊ የሆኑት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በብሪክስ ቤልት ኤንድ ሮድ የቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ውድድር አገራችንን በመወከል አሸንፈዋል።
በውድድሩ በአጠቃላይ በ15 ዘርፎች በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያ 4 የብር ሜዳልያ እና 3 የነሀስ ሜዳልያ በማምጣት ቀዳሚ ሆናለች።
ከዚህም በተጨማሪ 10 የፈጠራ ሥራዎች የምርጥ ፈጠራ እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በተሳተፉበት የፈጠራ ስራ Advanced Manufacturing Designing Semi-Automatic Animal feed production Machine ዘርፍም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የነሀስ ሜዳልያ በማምጣት ማሸነፍ ችለዋል::
በዚህ ከፍተኛ ውጤት የኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! የኮሌጁ አመራሮች መምህራኖቻችን የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደ መሬት ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት በተሻለ መልኩ ድጋፍ የምናደርግ ይሆናል።
የኮሌጁ ዲን
አቶ ሰለሀዲን አብዱልሀሚድ
በአዲስ የተዘጋጁ የሙያ ደረጃዎች የትውውቅና ምክክር መርሃግብር ተካሄደ፡፡
ለኢንዱስትሪው ተፈላጊውን የሰው ሃይል ለማቅረብ በኢንዱስትሪው የተዘጋጀውን የሙያ ደረጃዎች ለማስተዋወቅ ከሙያ ደረጃ ጋር ተያይዞ የሚነሱና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችል ዘንድ ሙያ ደረጃዎች በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የዘርፍ መሪ መስሪያቤቶች፣ ማህበራት፣ ባለድርሻ አካላት፣ ማሰልጠኛ ተቋማት እና ስልጠናውን ለሚመሩ አካላት ማስተዋወቅ ተችሏል።
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በገበያው ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎች በመደበኛ የስልጠና ፕሮግራም በክህሎት የዳበረ በአስተሳሰብና በስነምግባር የበለጸገ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት አስፈላጊውን ክህሎት በማስጨበጥ ለዜጎች በከተማና ገጠር የስራ ዕድሎች መፍጠር የሚያስችል ሥራዎች በመስራት ላይ ያለውና ለዚሁ ስራ ተግባራዊነት አስፈላጊ የሆኑ የስራ ገበያውን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተዘጋጁ የማሰልጠኛ መሳሪያዎች በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በኩል ለኮሌጆች በማሰራጨት ተግባራዊ እንዲሆኑ እየተደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 12/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአዲስ የተዘጋጁ የሙያ ደረጃዎች የትውውቅና ምክከክር መርሃግብር ተካሄደ፡፡
ለኢንዱስትሪው ተፈላጊውን የሰው ሃይል ለማቅረብ በኢንዱስትሪው የተዘጋጀውን የሙያ ደረጃዎች ለማስተዋወቅ ከሙያ ደረጃ ጋር ተያይዞ የሚነሱና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችል ዘንድ ሙያ ደረጃዎች በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የዘርፍ መሪ መስሪያቤቶች፣ ማህበራት፣ ባለድርሻ አካላት፣ ማሰልጠኛ ተቋማት እና ስልጠናውን ለሚመሩ አካላት ማስተዋወቅ ተችሏል።
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በገበያው ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎች በመደበኛ የስልጠና ፕሮግራም በክህሎት የዳበረ በአስተሳሰብና በስነምግባር የበለጸገ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት አስፈላጊውን ክህሎት በማስጨበጥ ለዜጎች በከተማና ገጠር የስራ ዕድሎች መፍጠር የሚያስችል ሥራዎች በመስራት ላይ ያለውና ለዚሁ ስራ ተግባራዊነት አስፈላጊ የሆኑ የስራ ገበያውን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተዘጋጁ የማሰልጠኛ መሳሪያዎች በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በኩል ለኮሌጆች በማሰራጨት ተግባራዊ እንዲሆኑ እየተደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 12/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአዲስ የተዘጋጁ የሙያ ደረጃዎች የትውውቅና ምክከር መርሃግብር ተካሄደ፡፡
ለኢንዱስትሪው ተፈላጊውን የሰው ሃይል ለማቅረብ በኢንዱስትሪው የተዘጋጀውን የሙያ ደረጃዎች ለማስተዋወቅ ከሙያ ደረጃ ጋር ተያይዞ የሚነሱና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችል ዘንድ ሙያ ደረጃዎች በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የዘርፍ መሪ መስሪያቤቶች፣ ማህበራት፣ ባለድርሻ አካላት፣ ማሰልጠኛ ተቋማት እና ስልጠናውን ለሚመሩ አካላት ማስተዋወቅ ተችሏል።
የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በገበያው ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎች በመደበኛ የስልጠና ፕሮግራም በክህሎት የዳበረ በአስተሳሰብና በስነምግባር የበለጸገ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት አስፈላጊውን ክህሎት በማስጨበጥ ለዜጎች በከተማና ገጠር የስራ ዕድሎች መፍጠር የሚያስችል ሥራዎች በመስራት ላይ ያለውና ለዚሁ ስራ ተግባራዊነት አስፈላጊ የሆኑ የስራ ገበያውን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተዘጋጁ የማሰልጠኛ መሳሪያዎች በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በኩል ለኮሌጆች በማሰራጨት ተግባራዊ እንዲሆኑ እየተደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 12/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ "ጥራት በተለየ እሳቤና ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል 14ኛውን የዓለም ጥራት ሳምንት አስመልክቶ በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ኤግዚቢሽን ላይ እየተሳተፈ ይገኛል::
የISO የጥራት አስተዳደር ተሸላሚነትን ያገኙ ከ150 በላይ ድርጅቶችና ተቋማት በሚሳፉበት በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ ኮሌጃችን አጠቃላይ አገልግሎቶቹን ጨምሮ የተለያዩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎቹን እና ምርቶቹን እያስተዋወቀም ይገኛል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 11/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ የኮንስትራክሽን አሰልጣኝ መምህራን በደረጃ አራት እና አምስት በስትራክቸራል ኮንስትራክሽን ሙያ ምዘና መውሰዳቸው ተገለጸ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 11/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
