Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 067
المشتركون
-224 ساعات
-67 أيام
+430 أيام
أرشيف المشاركات
+5
የድሬዳዋ አስተዳደር በጅፕሰምና በኤሌክትሪክ ስራ ያሰለጠናቸውን ወጣቶች አስመረቀ
የድሬዳዋ አስተዳደር የአካባቢ፣ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን "የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን የመቀነስ ፕሮጀክት" (EAC) አማካኝነት ለ15 ቀናት በጅፕሰምና በኤሌክትሪክ ስራ ሲያሰለጥናቸው የቆዩ ወጣቶችን አስመረቀ።
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ በላይነህ ደስታ እንደገለጹት፤ ስልጠናው ወጣቶችን በሙያ ከማብቃት ባለፈ ለስራ የሚያስፈልጉ ማሽነሪዎችና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። ይህ ቁሳቁስ የተበረከተው ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ሲሆን፣ በተለይም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ለተደራጁ ማህበራት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃላፊ አቶ አብዱ መሐመድ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ይሰጥ የነበረው ዝቅተኛ ግምት ተቀይሮ አሁን ላይ ወጣቶች በዘርፉ ሰልጥነው ራሳቸውን እያበቁ መሆኑን ገልጸዋል። ተመራቂዎች የተመቻቸላቸውን አጋጣሚ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆኑም አሳስበዋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ተወካይ በበኩላቸው፤ ተመራቂ ወጣቶች ራሳቸውንና ሀገራቸውን ለመለወጥ የተሰጣቸውን የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ስልጠናው በሙያም ሆነ በስነ-ምግባር አቅም የገነባባቸው መሆኑን የገለጹት ሰልጣኞች፤ በቀጣይም ስራ በመፍጠር ራሳቸውን ለመለወጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ይህ መሰል የክህሎት ስልጠና ወጣቶች ስራ ፈጣሪ በመሆን የኑሮ ሁኔታቸውን እንዲያሻሽሉና የአየር ንብረት ለውጥ የሚያመጣውን ተጽዕኖ የመቋቋም አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ይረዳቸዋል ተብሏል።
©️️ Diretv አማርኛ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድርን አስመልክቶ በኮሌጁ ምልከታ ተካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ መነሻነት እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በዛሬው እለት ግምገማ ተካሂዷል::
የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትንም ገምግሟል::
የምልከታ ቡድኑ በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርትን የተመለከት ሲሆን ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በሪፖርቱ ተመልክተዋል::
በማስቀጠል ቡድኑ በተቋሙ የሚገኙ የስራ ክፍሎችና የስልጠና ወርክሾፖች ላይ የተከናወኑ የካይዘን ትግበራዎችን ከመመልከት በተጨማሪ የካይዘን ትግበራው ውጤታማነትና የተገኘውን ለውጥ የሚያመላክቱ ሰነዶችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን በኮሌጁ በትግበራ ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮችንም መመልከት ችሏል::
"ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!!
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በከተማ ልማት ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ የተመራ ከፍተኛ ልኡክ ቡድን በአስተዳደሩ እየተገበረ ያለውን የተለያዩ የልማት ስራዎችን እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል የሆነውን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ የድሬዳዋ አስተዳደር በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ መርህ ላይ ተመስርቶ ብቁ የሰው ሀይልና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር በዚህም ውጤቶች እንዲመዘገቡ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን የልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የአስተዳደሩን የልማት ስራዎች ያስጎበኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
ቢሮው በአስተዳደሩ የአገር ውስጥና የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት፣ የኢንተርፕርነር ተቋማትን በመገንባት፣ ከአገር ውስጥና ከውጭ ተቋማት ጋር ጠንካራ አጋርነት በመፍጠር፣ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማዕከላትን በማሳደግ እንዲሁም የTVET ዲጂታላይዜሽንን በማረጋገጥ እና ለኢንዱስትሪዎች ተኪ መለዋወጫዎችን እንዲሁም ለአካባቢው ማህበረሰብ ሊጠቅሙ የሚችሉ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች እንዲሰሩ በማመቻቸትና በማበረታታት ረገድ የተከናወኑ ተግባራትን ጨምሮ የኢትዮ ኮደርስ አፈጻጸምን ለልኡክ ቡድኑ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
ከፍተኛ ልኡክ ቡድኑን የመሩት ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ በተመለከቱት አስተዳደሩ እየተገበረ ባለው ሁለንተናዊ የለውጥ አስገኚ ስራዎች ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስቻለ ነው መሆኑና በተለይ ከስራ ዕድል ፈጠራ፣ የቴክኒክና ሙያ አቅምን በማሳደግ ለኢንዱስትሪዎች እየተመረቱ ያሉትን ተኪ መለዋወጫዎች፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚያገለግሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማምረት ማህበረሰቡ እንዲጠቀም እየተደረገ ያለው ስራ ለሌሎች አርዓያ አካባቢዎች ይሆናል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) ምንነትና አስፈላጊነት
========================
ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ በማዕከላዊ ዲጂታል ሥርዓት ለማስተዳደር ያላትን ፍላጎት ለማሳካት እና ቀደም ሲል የነበረውን ችግር በዘላቂነት መቅረፍ በሚያስችል መልኩ የሰው ሀይል መረጃን ወደ ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር ስርዓት ለመሸጋገር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው።
እንደ ሀገር እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች መካከል አንዱ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን ይህንኑ መሰረት በማድረግም የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በጋራ በመሆን የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪፊኬሽን ስራ ተጀምሯል።
የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪቪኬሽን ስራዎች የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በውስጣቸው ይይዛሉ:-
1. የICSMIS ፍቺ እና አላማ
ይህ ስርዓት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሠራተኞችን ብዛት፣ የሥራ መደብ፣ ዕድሜ፣ ትምህርት ደረጃ፣ ደመወዝ እና ሌሎች መረጃዎች በማዕከላዊ መረጃ ቋት ለማስተዳደር የተዘጋጀ አገር አቀፍ የመረጃ ስብስብ ነው። በአብዛኛው የሚመራው በPublic Service and HR Directorate ወይም በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
2. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት
ከዚህ ቀደም የሠራተኛ ፋይሎች በተቋማት ተበትነው ስለነበር፣ ትክክለኛ ማዕከላዊ መረጃ ቋት አልነበረም። ስለዚህ የሚከተሉትን ለማስፈጸም የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ አስፈለገ፦
· ትክክለኛ የመንግሥት ሠራተኞች ዳታቤዝ መፍጠር
· የደመወዝ ክፍያ ሥርዓት ማሻሻል
· የሰው ኃይል እቅድ ማውጣት
· ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር መሠረት መጣል
· ተደጋሚ ወይም ክፍት የሥራ መደቦችን ለይቶ ለወደፊት ዕቅድ መረጃ ማግኘት
3. የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሚና
ኮሚሽኑ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ በተለያዩ ሕጎች መሠረት የተቋማትን አደረጃጀት እና የሰው ኃይል አስተዳደር በበላይነት ሲያስተዳድር ቆይቷል። ኮሚሽኑ የሲቪል ሰርቪስን የሰው ኃይል መረጃ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት ተግባራዊ ለማድረግና ማዕከላዊ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ለማገልገል ይሠራል።
4. ያጋጠመ ተግዳሮት
ኮሚሽኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ሳዘረጋ በመቅረቱ፣ ከአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና አንጻር ተፈላጊውን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም።
5. መፍትሔ እና ወቅታዊ እንቅስቃሴ
አሁን ላይ ኮሚሽኑ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማስገኘት በርካታ የለውጥ ፕሮግራሞችን በመተግበር ላይ ይገኛል። እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ ሰነድ አዘጋጅቶ እንዲጸድቅ ተደርጓል።
👉የኢስሚስ (ICSMIS) ትግበራ፣ ችግሮች፣ እና የመረጃ ማረጋገጫ (verification) አስፈላጊነት ዋና ዋና ነጥቦች፦
1. የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ አስፈላጊነት
የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ግብ ለማሳካት፣ የሲቪል ሰርቪስ የሰው ኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት እንዲተገበር ዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈለገ። ከፖሊሲው ሰባት አምዶች አንዱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ መገንባት ሲሆን፣ ለዚህም የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል።
2. የICSMIS ትግበራ ታሪክና ተግዳሮት
· ከ2004 በጀት ዓመት ጀምሮ ሥርዓቱን ማስፋፋት ተጀምሯል።
· ነገር ግን በቂ ክትትልና ተግባራዊነት ባለመኖሩ በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ሊተገበር አልቻለም።
· ከ2006 ጀምሮ በፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ደረጃ ተቋቁሞ ሥራዎችን ማከናወን ጀምሯል።
3. እስካሁን ያሉ ሥሪቶች (Versions)
· 1ኛ ሥሪት (1st version ICSMIS) – በአንዳንድ የክልልና የፌዴራል ተቋማት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
· 2ኛ ሥሪት (2nd version ICSMIS) – በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እየተጠቀመ ይገኛል።
· አዲሱ ሥሪት – ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ)ን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ ለመተግበር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ እየተከወነ ነው።
4. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት
ሥርዓቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ የሚከተሉት ችግሮች ተፈጥረዋል፦
· የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ በአንድ ቦታ ባለመደራጀቱ ለፖሊሲ ጥናት የሚሆን ግብአት ማቅረብ አልተቻለም።
· በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና በገንዘብ ሚኒስቴር መካከል ስለ መንግሥት ሠራተኞች ቁጥር ጉልህ ልዩነት አለ።
ለዚህም መፍትሔ እንዲሆን አገር አቀፍ የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) በመካሄድ ላይ ነው። ግቡም ትክክለኛውን የሠራተኞች ቁጥርና ተጓዳኝ መረጃ በኦንላይን ወደ ICSMIS ማስገባት ነው።
በለውጥ ዓመታት የተመዘገበው የሥራ ዕድል ፈጠራ ስኬት፦ 19.8 ሚሊዮን ዜጎች ተጠቃሚ ሆነዋል
ኢትዮጵያ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ብቁ የሰው ሀብትና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር በጀመረችው ጉዞ ታላቅ ውጤት አስመዝግባለች።
ከለውጡ በኋላ ባሉት ዓመታት በሀገር ውስጥ፣ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እንዲሁም ዜጎች ባሉበት ሆነው በሚሰሯቸው የፈጠራ ሥራዎች አማካኝነት ለ19,872,846 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።
ለዚህ ታላቅ ስኬት መመዝገብ ደግሞ የኢንተርፕርነር ተቋማትን መገንባት፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ተቋማት ጋር ጠንካራ አጋርነት መፍጠር፣ የቢዝነስ መስፋፋትና የልህቀት ማዕከላትን ማሳደግ እንዲሁም የቲቬት (TVET) ዲጂታላይዜሽንን ማረጋገጥ መቻሉ ዋነኛ ምሰሶዎች ሆነዋል።
ይህ ውጤት ሀገራችን ለዜጎቿ አስተማማኝና ዘላቂ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የያዘችውን ራዕይ በተግባር እያረጋገጠች መሆኑን ያሳያል።
ዘገባው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ነው።
በአስተዳደሩ በሚገኙ የግል ኮሌጆች መካከል የምርጥ ተሞክሮ ልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሄደ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት የግል እና የመንግስት ኮሌጅ ዲኖች፣ ም/ዲኖች እና የውስጥ ጥራት ኦዲት ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእርስ በእርስ ተመክሮ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በዚህም የሪፍት ቫሊ ኮሌጅ ምርጥ ተሞክሮ የቀረበ ሲሆን የስልጠና ጥራትን ለማምጣት በኮሌጁ የውስጥ ጥራት ኦዲት የተሰሩ ስራዎች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሞን የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ቀጣይነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችላቸውን አቅም እንዲያጎለብቱ የሚያስችል “Strategy in an Era of Deep Technological Transfformation” በሚል ርዕስ ሰፋ ያለ ትምህርታዊ ሰነድ በዶ/ር ነስረዲን ቀርቧል፡፡
የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በተለይም የግል ኮሌጆች መሰል የልምድ ልውውጥ መድረኮችን በማስፋት በአስተዳደሩ ያለውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ከፍ የማድረግ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ፈጡም አክለው ኮሌጆቹ በትብብር መንፈስ የተቃኘ ውድድር እንዲያደርጉ ያሳሰቡ ሲሆን በመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ የመንግስት ተቋማትም ያላቸውን የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማካፈል ዝግጁ መሆናቸውን በማረጋገጥ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 26/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
👷🏾♂️ወደ ውጭ አገር የምሥራት ህልም አሎት?👷🏾♂️
✈️✈️🌏🌎 በተለያዩ ተፈላጊ በሆኑ የሙያ መስኮች ላይ እየተጠየቀ ባለው የሥራ እደሎች ላይ E-LMIS በኩል ተጠቃሚ ይሁን።
ከታች በተዘረዘሩት በርካታ የስራ መስኮች ላይ በማመልከት ዛሬዎኑ የስራውን ዓለም በመቀላቀል ዕውቅዎቶንና እና ልምዶን ወደ ገንዘብ ይቀይሩት:-
🔹 የግንባታ ሰራተኛ/Carpenter / Construction Worker
🔹 የብረታ ብረት ባለሙያ/ Steel Fixer
🔹 ቴክኒሻን / Technician
🔹 ሲቪል ሱፐርቫይዘር / Civil Supervisor
🔹 ምግብ አብሳይ / Chef
🔹 የግንባታ ረዳት ሰራተኛ / Construction Helper
🔹 አጠቃላይ ግንበኛ / General Mason
🔹 የጽዳት ሰራተኛ / Cleaner
🔹 የኤሌክትሪክ ባለሙያ /Electrician
🔹 የቧንቧ ሰራተኛ /Plumber
🏫 ስለሆነም ይሆንን እድል ለትጠቀሙ የምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/uae-new-2/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎችን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
📞 ለተጨማሪ መረጃ፡ በስልክ መስመር 9138 ይደውሉ ።
የስራ ባለቤት እርስዎ ነዎት !
የ🇪🇹 የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓትን (lmis.gov.et) እንዴት እንጠቀም?
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ጨምሮ ከ23 በላይ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሀገር አቀፍ የሥራ ዲጂታል የመረጃ ስርዓት ነው።
🔑ቁልፍ ፋይዳዎች
✅የሥራ ስምሪት ሥራን ማዘመን፦ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን እንዲሁም የርቀት ሥራዎችን በአንድ ላይ አጣምሮ አገልግሎት ጊዜውን በዋጀ መልኩ መስጠትና ማግኘት ያስችላል፣
✅ፍትሃዊ ተደራሽነት፦ ስርዓቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ እና ከሰው ንክኪ ነፃ እንዲሆን ተደርጎ የበለፀገ በመሆኑ፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩል አገልግሎት መስጠት ያስችላል፣
✅መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ፦ የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከሀገራዊ የልማት ፍላጎት ጋር እንዲጣጣም ፓሊሲ አውጪዎች ወሳኝ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፣
ሆኖም አንድ ትልቅ እውነትን መረዳት ይኖርብዎታል፦
✅ምዝገባ ወደ ሥርዓቱ መግቢያ የመጀመሪያው እርምጃ እንጂ የጉዞው ማብቂያ አይደለም።
ስርዓቱ ከሚሰጠው አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን እነዚህን 6 ወሳኝ ደረጃዎች ይከተሉ፦
1️⃣ምዝገባ (Online Registration)
• በመጀመሪያ lmis.gov.et ድረ-ገጽን በመጎብኘት በስልክዎ ወይም በኮምፒውተርዎ መሠረታዊ መረጃዎን በትክክል ይሙሉ፡፡
2️⃣የባዮሜትሪክ ምዝገባን ማጠናቀቅ
• ከምዝገባው በኋላ በስልክዎ የሚላክልዎትን የአንድ ጊዜ የይለፍ ቃል በመያዝ፣ በአቅራቢያዎ በሚገኝ ማዕከል በመሄድ የጣት አሻራ መረጃዎን ይስጡ።
3️⃣ይፋዊ ማስታወቂያዎችን መከታተል
• የሥራ ዕድሎች በየጊዜው ይፋ ይደረጋሉ። ስለዚህ ሁልጊዜ የሥራና ክህሎትን ድረ-ገጽና ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በንቃት ይከታተሉ።
4️⃣መስፈርቶችን በጥንቃቄ መፈተሽ
• እያንዳንዱ የሥራ መደብ የራሱ የሆነ መስፈርት አለው። ከማመልከትዎ በፊት መስፈርቶቹን ማሟላትዎን ያረጋግጡ።
5️⃣ራስን ለሥራ ማዘጋጀት
• ክህሎትዎን ያሻሽሉ፣ አስፈላጊ የሆኑ ስልጠናዎችን ይውሰዱ እና በማንኛውም ሰዓት ለሥራ ዝግጁ ሆነው ይጠብቁ።
6️⃣በይፋዊ ሊንኮች ብቻ ማመልከት
• ሁልጊዜ በሥርዓቱ ላይ በሚቀመጡ ይፋዊ የሥራ ማመልከቻ (Vacancy) ሊንኮች ብቻ ይጠቀሙ። ከአጭበርባሪዎች ራስዎን ይጠብቁ!
⚡ መዘንጋት የሌለብዎት ቁልፍ ነጥቦች
• የሥራ ዕድሎች የጊዜ ገደብ ስላላቸው፣ ማስታወቂያ ሲወጣ በፍጥነት ምላሽ መስጠት ለስኬትዎ ወሳኝ ነው።
• የእርስዎ ዕድል የሚወሰነው በምዝገባዎ ብቻ ሳይሆን በሚወስዱት ንቁ እርምጃ ጭምር ነው! 🌟✨
• ዛሬውኑ lmis.gov.et ን ይጎብኙ እና ለወደፊት ህይወትዎ ንቁ እርምጃ ይውሰዱ። 🌟✨
•
📌የመመዝገቢያ መስፈርት:
👉 ዕድሜ፦ ከ15-65 ዓመት ( ዕድሜው ለሥራ የደረሰና ሥራ ያለውም የሌለውም)
👉 የትምህርት ደረጃ፡ በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ያለ ሰው መመዝገብ ይችላል
⚠️ማስታወሻ
✅ ስርዓቱ ይዞ የሚመጣውን ዕድሎች ሁሉ ለመጠቀም ግላዊ መረጃ፣ የትምህርት እና የሥራ ልምዶችን በአግባቡ ማያያዝዎን ልብ ይበሉ!
መመዝገብ ስርዓቱ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማግኘት ብቁ የሚያደርግዎ የመጀመሪው ጉዳይ ነው። ከስርዓቱ ለመጠቀም የሚወጡ ማስታወቂያዎችን መከታተልና ማመልከት ይኖርብዎታል።
ሚያዚያ 25/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ቢሮው የሠራተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ
የድሬዳዋ አስተዳደር 137ኛው የዓለም የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) "የሠራተኞች መብት መከበር ለኢንዱስትሪ ሰላምና ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ አክብሯልል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይባስተላለፉት መልዕክት፤ ቢሮው የሠራተኞችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎችን ተግባራዊ እያደረገ ነው ብለዋል።
የሠራተኞች ቀን መከበሩ የሀገርን ኢኮኖሚ ለሚገነቡ የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ያለንን ክብር የምንገልጽበት ነው ያሉት ኃላፊው፤ የሥራ ስነ ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ ቢሮው በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን የምስራቅ ቅርንጫፍ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንዳለ በበኩላቸው፤ ምርታማነትን ለማረጋገጥ የሠራተኛው መብትና ደህንነት መከበር ቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞች በሰጡት አስተያየት፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የሠራተኛው መብትና ደህንነት መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዕለቱ የሠራተኛ መብትና ደህንነት ለኢንዱስትሪ ሰላም ያለው ፋይዳ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሂዶበታል። መረጃው የድሬ ቲቪ ነው።
ሚያዚያ 23/2018 ዓ.ም
#አሁን
#Happeningnow
ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) " የሠራተኛ መብት መከበር፤ ለኢንዱስትሪ ሰላምና ለምርታማነት መሠረት ነው” በሚል መሪ ሀሳብ በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከበረ ነው።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከድሬዳዋ ሠራተኞች ማህበራት ኮንፈዴሬሽንና አሠሪዎች ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በዓሉን አዘጋጅቷል።
የአስተዳደሩ የሥራ ድርጅቶች እንዲሁም የማህበራቱ ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎችና ተወካዮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዕለቱ "ምቹ የሥራ ሁኔታ ለዘላቂ ልማት" በሚል ርዕስ የሚካሄደውን የፓናል ውይይት ጨምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
ሚያዚያ 23/2018 ዓ.ም፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የ2018 ዓ.ም ገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠና አስመልክቶ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት የአፈጻጸም ሂደት ምልከታ እና ውይይት አደረገ።
በዚህም በ2018 ዓ.ም ስራ ፈላጊ ዜጎችን በገበያ ተኮር አጫጭር የክህሎት ስልጠና ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ስራ ስምሪት በማብቃት ከስራ ጋር እንዲተሳሰሩ በማድረግና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ በከተማና በገጠር ቀበሌዎች ስራ ፈላጊ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
