ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
الذهاب إلى القناة على Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
إظهار المزيد3 309
المشتركون
-224 ساعات
-97 أيام
-3630 أيام
أرشيف المشاركات
✨💧🥀ዜና መጽሐፍ
📖ከቅዱስ_ጳውሎስ 📖
#በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው «አባቶችህን እወቅ »ብሎ የነበረው አኹን አንድ በአንድ ሊያሳውቀን ቆርጦ ሣይነሳ አልቀረም።#ጌታ_ምርጥ_ዕቃ_ከቅዱስ _ጳውሎስ ጀምሮታል እንግዲህ አለማንበብብ ሳይኾን ለማዘግየት ማሰብ ራሱ ግፍ ነው ......
#በእውነቱ መምህራችን ያኑርልን!🙏
ከደረስንበት በወፍ በረር እናድርሳችኹ ,,,,
‹‹ቅዱስ ሉቃስ ሐዋርያው ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ ድውይ የፈወሰበትን፣ በእጆቹም እጅግ የሚያስገርም ተአምራት ያደረገበትን ታሪክ ብቻ ሳይሆን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ እና ክርስቲያኖችን ያሳድድ እንደ ነበር መጻፉ ለእኛ ለኃጥአን መጽናኛ እና ትልቅ የተስፋ ስንቅ ነው፡፡ ንስሐ የማያጥበው ሰውነት፣ የማያነጻው ማንነት የለም፡፡ እኛ የቱንም ያህል ብንበድል እና በኃጢአት ያደፍን ብንሆን፣ የእኛ መቆሸሽ እግዚአብሔር ከሚያጥብበት የንስሐ ሳሙና በላይ ሊጠነክር አይችልም፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ የመጠራት ታሪክ የንስሐን ኃያልነት እና የእግዚአብሔርን ምሕረት ያለ ማቋረጥ የሚያሳይ ዘመን አይሽሬ መስታወት ነው፡፡ ስለዚህም አሳዳጁን ሳውል ወደ ሐዋርያነት ያሸጋገረችውን ንስሐ ከአባ ዮሐንስ ሳባ (አረጋዊ መንፈሳዊ) ጋር በመሆን እንዲህ እያልን እናመስግናት፦
[ከገጽ 149]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
#በመምህር አቤል ካሳሁን
✨ቅዳሜ በመደብራችን ያገኙታል።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
💥✨እነኾ አዲስ_ምግብ📚
📖#ሐመረ_ነፍስ📖
...✍️በተለይም እንዲህ የሚሉት ጥያቄዎች ከብዙ ወጣቶች በተደጋጋሚ ይሰማሉ... ➮እውነት ያለዉ በኦርቶዶክስ ክርስትና ውስጥ መሆኑን እንዴት እርግጠኛ መሆን እንችላለን? ➮ሰው በተወለደበት ማኅበረሰብ ባገኘው እምነት ወደ እውነትና ዘለዓለማዊ ሕይወት መድረስ አይችልምን? ➮በሁሉም ሃይማኖት ውስጥ ያለ አስተምህሮና መዳረሻስ አንድ አይደለምን?➮ በሂንዱይዝም ውስጥ እሉ የሚባሉት ታላላቅ ሰዎች (ጉሩዎች) የሚያደርጓቸው አስገራሚ ነገሮች ከእግዚአብሔር ኃይል የተገኙ አይደሉም ማለት እንዴት ይቻላል?➮ ዮጋ የሚባለው የተመስጦ ልምምድስ ከሃይማኖት ጋር ይገናኛልን? ➮ክርስቲያን ሆኜ ዮጋን ብለማመድ ምን ችግር አለው?
#ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎችም መልስ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ ከግሪክ ተነሥቶ ወደ ህንድ አገር ሄዶ በዚያ ካለ የሂንዱይዝም ታላላቅ ጉሪዎች ጋር ተገናኝቶ ያየውንና በራሱ ላይ በተጨባጭ የደረሰበትን ነገር የጻፈው እንደ እርሱ ያለ ጥያቄ ያላቸው ሰዎች በእርሱ የደረሰው ችግር ይደርስባቸውና ራሳቸውን ለአደጋ ማጋለጥ ሳያስፈልጋቸው ከእርሱ የድካም ፍሬ ትምህርት መውሰድ ይችሉ ዘንድ ነው። ስስዚህ ከዚህ ዓይነቱ ተግባራዊ ሙከራና ውጤት መማር ጠቃሚም ተገቢም ነው። ወንድማችን ዲ/ን ሁነኛው ተሾመም ይህን መጽሐፍ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ስላቀረበልን ከልብ አመሰግነዋለኹ።#እግዚአብሔር ለወንድማችን መልካም ዋጋ ይክፈልልን እኛንም አንብበን ለመጠቀም ይርዳን! በማለት በዚሕ መልኩ #ዲ/ን_ያረጋል_አበጋዝ የጋበዙን ሲኾን #ግዮን ደግሞ በልዩ ቅናሽ እነኾ....!
📚#ግዮን_መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
#ሰዎች በአጠቃላ በተለይም ደግሞ በዘመናችን ያሉ ወጣቶች ስስዩ ዩ ተጽዕኖዎች ከመጋስጣቸው የተነሣ የተሰያዩ ጥያቄዎች በአእምሯቸው ይመሳስሳሉ። በተለይም እንዲህ የሚሉት ጥያቄዎች ከብዙ ወጣቶች በተደጋጋሚ ይሰማሱ፡ እውነት ያስሙ በኦርቶዶክስ ክርስትና ውስጥ መሆኑን እንዴት እርግጠኛ መሆን እንችላስን? ሰው በተወስደበት ማኅበረሰብ ባገኘው እምነት ወደ እውነትና ዘለዓለማዊ ሕደወት መድረስ አይችልምን? በሁሉም ሃይማኖት ውስጥ ያስ አስተምህሮና መዳረሻስ አንድ አይደለምን? በሂንዱይዝም ውስጥ እሱ የሚባሉት ታላላቅ ሰዎች (ጉሩዎች) የሚያደርጓቸው አስገራሚ ነገርች ከእግዚአብሔር ኃይል የተገኙ አይደሉም ማስት እንዴት ይቻሳል? ዮጋ የሚባሰሙ የተመስጦ ስምምድስ ከሃይማኖት ጋር ይገናኛልን? ክርስቲያን ሆኜ ዮጋን ብሰማመድ ምን ችግር አስው?
ምናልባት እርስዎም እነዚህንና እነዚህን የመሰሱ ጥያቄዎች በአእምሮዎ የሚመሳስሱ ከሆነ ወይም ጉዳዮቹ የሚያሳስቡዎት ከሆነ፣ ይህ መጽሐፍ ስእርስዎ ነው። የዚህ መጽሐፍ ጸሐፌ ራሱ በእንደዚህ ያሉ ጥያቄዎችና ፈተናዎች ውስጥ ያለፈ ሰው ነው። በእነዚህ ጥያቄዎች ውስጥ ያስፈ ብቻ ሳይሆን ስፕያቀዎቹ መሰስ ለማግኘት ሲስ የራሱን ሕይወት ስለደጋ እስከ ማጋለጥ ደርሶ በጣም ሩቅ በሆኑ ቦታዎችና ፈታኝ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ራሱን አስገብቶ በራሱ ላይ ሙከራ አድርጎ መልሱን ያገኘ ሰው ነው።
#የዚህ መጽሐፍ ደራሲ ከግሪክ ተነሥቶ ወደ ህንድ አገር ሄዶ በዚያ ካስ የሂንዱይዝም ታላላቅ ጉሪዎች ጋር ተገናኝቶ ያየውንና በራሱ ላይ በተጨባጭ የደረሰበትን ነገር የጻፈው እንደ እርሱ ያስ ጥያቄ ያሳቸው ሰዎች በእርሱ የደረሰው ችግር ሳይደርስባቸውና ራሳቸውን ስለደጋ ማጋስፕ ሳያስፈልጋቸው ከእርሱ የድካም ፍሬ ትምህርት መውሰድ ይችሉ ዘንድ ነው። ስስዚህ ከዚህ ዓይነቱ ተግባራዊ ሙከራና ውጤት መማር ጠቃሚም ተገቢም ነው። ወንድማችን ዲ/ን ሁነኛው ተሾመም ይህን መጽሐፍ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ስሳቀረበልን ከስብ አመሰገነቸስሁ። እገዚአብሔር ወንድማችን መልካም ዋጋ ይክፈልልን እኛንም አንብበን ስመጠቀም ይርዳን! በዚሕ መልኩ መምህረ መምህራን #ዲ/ን_ያረጋል_አበጋዝ የጋበዙን ሲኾን #ግዮን ደግሞ በልዩ ቅናሽ ይዘን መተናል..!
📚#ግዮን_መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
https://t.me/GhionBookStore1623
ነገረ ክርስቶስ ክፍል፬
፦የምሥጢረ ሥላሴ መሠረቱ ዘለዓለማዊ ሀልዎት ነው።
፦የከዊት መሠረቱ ህልውና መረዳት ነው።
፦ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድን ሰው ሆነ የማለት መሠረቱ ምሥጢረ ሥላሴን መረዳት ነው።
፦የተዋህዶ መሠረቱ ዘለዓለማዊ ተዓቅቦን መጠበቅ ነው።
፦የአካላት በአካላት ህልውና መሠረቱ ሀልወትን ማወቅነው።፦የዘለዓለማዊ ሀልዎት መሠረቱ ርቱዕ ሃይማኖት ነው።፦የሃይማኖት መሠረቱ ፈጥሮ የማይጥል የእግዚአብሔር ቸርነታዊ ፈቃዱና የህሊና መሻት ጠባይዕ ነው።፦የጠባይዕ መሠረቱ ግብረ ፈቃድ ዘቅድስት ሥላሴ ናት።
፦በአንዲት የሥላሴ ፈቃድ ፍጥረቱ ሁሉ ካለመኖር ወደ መኖር እና በግብር እምግብር ተፈጥሯልና።፦ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር-ሥላሴ ደግሞ ድንቅ፣ግሩም፣ልዑል ናቸው።
፦ሥላሴ በባሕርይ አንድ ናቸው።
ባህርይ ማለት፡- ያልተፈጠረ፣የማይመረመር ፣የማይታወቅ፣ኅቡዕ፣ረቂቅ፣ቅድስት ሥላሴን አንድ የሚያደርግ፣የፈጣሪ ባሕርይ፣አምላክነት ማለት ነው፡፡ አማ.መዝ.ቃላ.ዘአ.ደስ.ገጽ.፻፷፮
፦በባሕርይ አንድነት፦የሥላሴ መለኮትነት፣ጌትነት፣ክቡርነት፣ንጹሕነት፣ልዑልነት፣ጽኑዕነት፣ፈቃድ፣ሥምረት፣..ይነገርበታል።
፦በሁሉም ሲነገር ባሕርይ የነገር ሁሉ ስር መሰረት ምንጭ ማውጫ መፍለቂያ መገኛ ጠባይዕ ክዋኔ ማለት ነው፡፡
፦ባሕር ለታውጽእ ተብላ ብዙ ስነ ፍጥረትን እንዳስገኘች ባሕርይም መገኛ ማስገኛ ስለሆነ የአካል የስም የህላዌ ጥንት የስራ ምንጭ የግብር መሰረት ይባላል ኪዳ ወል ገጽ.፪፻፷፫
፦ "ባሕርይ ማለት የአካል መገኛ ስር አካል ስራውን የሚሰራበት መሰሪያ ነው።"መድ.አሚ.ገጽ.፪፻፵፯
ባሕርይ ኋኝነትን የምንገልጽበት ምሥጢር ነው።
፦ቅድስት ሥላሴ በአንዲት ባሕርይ አንድ ናቸው።
፦ወይም በኩነት ግብር በሚነገር ተዋሕዶ ሥላሴ አንድ ናቸው።
፦በአንዲት የባሕርይ ግብራቸው ፈጽሞ መለያየት የለባቸውም።
፦ርቀትን መሠረት አድርጎ ለመንፈስ ቅዱስ የሚነገሩ ኅብረ አምሳላዊ ምሥጢሮች አሉ፦
፦መንፈስ ቅዱስ ርግብ ተብሏል። ማቴ. ፫፥፲፮ ፦ደመናም ተብሏል። ራዕ. ፱፥፫ ፦በረድ የተባለበት ጊዜም አለ። መዝ. ፻፵፯፥፲፯ ፦እሳት የተባለበት ጊዜም አለ። ማቴ. ፫፥፲፩ ፦ነፋስ የተባለበት ጊዜም አለ። ሐዋ. ፪፥፩፦ብእሲት ሠናይተ ላህይ (መልከ መልካም ሴት) ተብሏል። ፊልክስዩስ ተስእሎ ፶፩፦ንሥር የተባለበት ጊዜም አለ። ፊልክስዩስ ተስእሎ ፺፥፩፦ፀሐይ የተባለበት ጊዜም አለ። ሃይ. አበው ባስል. ፴፫፥፵፰፣ አረ. መንፈ. ድር. ፳፩፦ሰገኖ የተባለበት ጊዜ አለ። ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ፦ሁከተ ማይ (የውኃ መታወክ) የተባለበት ጊዜም አለ። አረ. መንፈ. ድርሳን ፳፪
፦ለወልድም እንዲሁ በተለያዩ ኅብረ ምሥጢሮች ይነገርለታል፦
፦"ዘውእቱ ህሊናሁ ለአብ-የአብ ህሊናው እርሱ ነው።" ሃይ.፯፥፬፦፣እዱ መዝራእቱ-ቀኝ ክንዱ፣፦ጥበቡ ለአብ-የአብ ጥበቡ፣፦ምክሩ ለአብ-የአብ ምክሩ፣፦ኃይሉ ለአብ-የአብ ኃይሉ፣፦ጸዳሉ ለአብ ጸዳለ ስብሐቲሁ-የጌትነቱ መታወቂያ፣
፦ውሳጣዊ ተገናዝቢንና አፍአዊ ግብረ ባህርይን መሠረት ያደረገ ምሥጢር ነው እንጂ የአካል ባሕርይ ግብር አደለም።
፦የወልድ የአካል ግብር አንድ ነው ያውም መወለድ ብቻ።
፦የኩነት ግብሩም አንድ ነው ያውም ቃልነት ብቻ ነው። ፦የአብም የአካል ግብሩ መውለድ ማሥረጽ ብቻ ነው።
፦የኩነት ግብሩ ልብነት ነው።
፦የመንፈስ ቅዱስም የአካል ግብሩ መሥረጽ ብቻ ነው።
፦የኩነት ግብሩ ሕይወትነት ብቻ ነው።
፦ሌሎች ግን የአንዲት የሥላሴ ባሕርይ የፈቃድ ግብራት መገለጫዎች ናቸው፡፡
ከኔታ ገብረ መድኅን እንየው
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
...መምህራችን #ዲያቆን_አቤል እጅጉንን አጓጉተውን ሳይደስርስ በመቅረቱ ሌላ ጉጉት ጥሎብን ሳይሄድ አልቀረም .... 😔
#ውድ_ግዮናውያን እስከዚያው ማቆያ ትኾን ዘንድ #የክርስቶስ_ምርጥእቃ_ስለተሰኘው_ዓምደ_ቤተክርስትያን_ንዑድ_ክቡር_ጳውሎስ እራሳቸው መምህራችን ጦማር እናቃምሳችኹ ዘንድ ወደድን .......👇
📜"ለእኔ ሕይወት #ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና" [ፊል 1፥21]
እነኾ ምሳሌ፦
በምንኩስና ይኖር የነበረ አባት ከዕለታት በአንዱ ቀን ወደ ገነት ሄደ። ከውጭም ቆሞ እንዲከፈትለት ደጁን ያንኳኳ ጀመር። ወዲያውም "ማን ነኽ?" የሚል ድምጽ ከውስጥ ሲወጣ ሰማ። መነኩሴውም "እኔ ነኝ" ሲል መለሰ። ይኹን እንጂ ያንኳኳው በር ግን ሊከፈትለት አልቻለም። ከተወሰኑ ዓመታት በኋላም እንደ ገና ተመልሶ ወደ ገነት በመምጣት ደጁን አንኳኳ። እንዳለፈውም ጊዜ ከውስጥ "ማን ነኽ?" የሚል ድምጽ ሰማ። እርሱም እንደ ለመደው "እኔ ነኝ" አለ። አኹንም በሩ ሳይከፈትለት ቀረ።
መነኩሴው በዚህ ተስፋ አልቆረጠም። ይኽ ከኾነ ከብዙ ዓመታት በኋላ እርሱም በመንፈሳዊው ጥበብ ጎልምሶ ተመልሶ ወደ ገነት ሄዶ በሩን አንኳኳ። እንደ ከዚኽ በፊቱም "ማን ነኽ?" የሚል ድምጽ ሰማ። ያም አባት የቀድሞው መልሱን ተወና "በእኔ ውስጥ የምትኖረው አንተ ነኽ" ሲል ለጠየቀው አካል መለሰ። በዚህ ጊዜ ተዘግቶ የነበረው በር ተከፈተለት ይባላል።
#ክርስትና ምንድር ነው? ለሚለው ጥያቄ የተለያዩ ማብራሪያዎች ሊሰጡ ይችላሉ። በአጭሩ ግን እንመልሰው ካልን፣ ክርስትና ማለት " #ክርስቶስ የሚያድርበት መቅደስ መሆን " ማለት ነው። ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ሲገልጽልን "እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም #ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል" ይለናል።(ገላ 2፥20) #ክርስቲያን ማለት "አንተ ማን ነኽ?" ተብሎ ሲጠየቅ ልክ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "በእኔ የሚኖር #ክርስቶስ ነው"፣ "አነ #ዘክርስቶስ" - "እኔ #የክርስቶስ ነኝ" ብሎ መመለስ የሚችል ነው።
#ጌታችን በወንጌል ለደቀ መዛሙርቱ "በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ" ሲል እንደ ተናገረ፣ እኛ #ለክርስቶስ መኖር ስንጀምር እርሱ ደግሞ በእኛ ይኖርብናል፤ እኛ #ለክርስቶስ ማደር ስንጀምር እርሱ ደግሞ በእኛ ያድርብናል። (ዮሐ 15፥4)
እንዲህ ያለውን ሕይወት የሚኖር እውነተኛ ክርስቲያን የሥጋን ሞት አይፈራም። ስለ ሃይማኖቱ መከራ መቀበልን አይሰቀቅም። #ክርስቶስን ከሚያሳጣው ሕይወት ይልቅ ወደ #ክርስቶስ የሚወስደውን ሞት ይመርጣል። ፈጣሪው ከሌለበት ምቾት ይልቅ ፈጣሪን ይዞ መሰቃየት ለእርሱ ያስደስተዋል።
ሰይፍ ይዘው በሚያስፈራሩትም ጨካኝ ወታደሮች ፊት "ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና" እያለ በሐሴት ይዘምራል። (ፊል 1፥21)
=======
በሰይፍ ለሚገድለው ወታደር በኩራት የልብሱን ኮሌታ ከፍ አድርጎ አንገቱን ስለ #ክርስቶስ በደስታ ለሰጠ፣ ለታላቁ ሐዋርያ #ለቅዱስ_ጳውሎስ የሰማዕትነት በዓል እንኳን በሰላም አደረሰን!
የአገልግሎቱ ድካም፣ በረከት በሁለችን ላይ ይደርብን!!!
✍️ዲያቆን አቤል ካሳሁን
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
ከእርሱ ጋር ኀብረት ፍጠሩ!
እግዚአብሔርን ለማወቅ ለመውደድ ከእርሱ ጋር መተባበር አለባችሁ። ንባብ ብቻውን በቂ አይደለም። ንባብ የሚከፍትላችሁ መዝጊያውን ብቻ ነው። ከዚህ በኋላ እናንተ ትገቡና ከእግዚአብሔር ጋር ትኖራላችሁ ከዚያም ከእርሱ ጋር መኖር ጣፋጭ መሆኑን እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ።
ስለሆነም ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን ሕይወትን ትሞክሩታላችሁ እርሱ በሁሉም ነገር ውስጥ ተካፋይ እንዲሆንም ትፈቅዳላችሁ።
እንደ ባልጀራችሁ አድርጋችሁ ልትወዱት ሞክሩ አሳቦቻችሁንና ሚስጥሮቻችሁን ለእርሱ ንገሩት። ከዚህ በኋላ የሚሆነውን ጠብቁና እርሱ ምን ያህል ከእናንተና ለእናንተ እንደሚሰራ ታያላችሁ። ከዚህ በተጨማሪ በአሳቦቻችሁና በተሰጥኦዎቻችሁ ከመተማመን የበለጠ በእርሱ ላይ መተማመንን ታውቃላችሁ።
#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
ብርሃናተ ዓለም
የሚገርም ጥሪ፣ አስደማሚ ተልእኮ፣ የሚያበራ ሰማዕትነት!
በረከታችሁ ይደርብን!
ብርሃናተ ዓለም
የሚገርም ጥሪ፣ አስደማሚ ተልእኮ፣ የሚያበራ ሰማዕትነት!
በረከታችሁ ይደርብን!
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
" ለራስ ጥቅም ሌሎችን ማስቀደም "
በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
በዚህ ጽሑፍ አንድ ሰው ራሱን ለመጥቀም እንዴት ማድረግ እንዳለበት ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር ለማየት እንሞክራን።ለዚህ ጉዳይ አስተማሪ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንዳስሳለን
ራዕየ ኒፎን
የይቅርታ ፏፏቴ የርኅራኄ ባለጠጋ የሆንክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፊትህን ከእኔ አትመልስ፤ ማረኝ፤ ይቅርም በለኝ፡፡
ጌታ ሆይ “አላውቅህም አትበለኝ!' ጌታ ሆይ እስከዛሬ የት ነበርክ?' ብለህም አትቆጣብኝ፡፡ በኃጢአት የቆሸሽሁ፧ በበደል እንደ ጢስ የጠቆርሁ፤ ሕግህን በመተላለፍ የበሰበስሁ፤ ፍቅርህን በመርሳት የተዋረድሁ፤ በርኵሰት የሽተትሁ፤ በዲያብሎስ ምክር የጠፋሁ፤ ሰዎች በሚሠሩት አስነዋሪ ሥራም ዋነኛ የሆንኩ የማልጠቅም ትቢያና ጉድፍ ልጅህን አትናቀኝ፤ ከፊትህም አፍሬ አልመለስ፡፡
መምህሬ ሆይ! ከእኔ አትራቅ፤ ራራልኝ፤ አድነኝም፡፡ ሰው ወዳጅ ሆይ “አንተ የኃጢአተኛን በንስሐ ከክፉ መንገዱ መመለሱን እንጂ መጥፋቱን እንደማትሻ' አውቃለሁና ተመልሰህ እስክትረዳኝና ምሕረትህን እስካገኝ አላርፍም፡፡"
(ራእየ ኒፎን ገጽ 59)
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
ዝይን- በአለማየሁ ገላጋይ
በቅርብ ቀን !
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
