ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
الذهاب إلى القناة على Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
إظهار المزيد3 309
المشتركون
-224 ساعات
-97 أيام
-3630 أيام
أرشيف المشاركات
📖#መጽሔተ_ወራዙት_ዘኦርቶዶክስ📖 [የኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች መስታወት]
#ቅዱስ የሐንስ አፈወርቅ የወጣትነትን ክብደት ለመግለጥ፥ "የወጣትነት ዕድሜ የአውሬነት ጊዜ ነው። በመኾኑም ብዙ ተቆጣጣሪዎች፣ መምህራን ርእሳነ መምህራን፣ አገልጋዮችና የግል መምህራን ያስፈልጉታል። እነዚህ ሁሉ ተደርገውለት የአውሬነቱ ጠባይ ከቆመ ደስታ ነው። ያልተገራ ፈረስ ወይም ለማዳ ያልኾነ የዱር አውሬ ማለት ነው ወጣትነት። ነገር ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ ከልጅነት እድሜው አንሥቶ ከመልካም ሕግጋት ጋር እንዲጣበቅ ካደረግነው ብዙ ደካሞ ላይጠይቀን ይችላል። መልካም የኾኑት ልማዶቻቸው እንደ ሕግ ይቆጥራቸውና ጥሩነት የሕይወታቸው መመሪያ ና ሕግ ይኾናል።'' በማለት ይገልጻል።
[ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ]
#ይህ መጽሔተ_ወራዙት_ዘኦርቶዶክስ በሚል ርዕስ #በዲያቆን_ዮሐንስ_ጌታቸው የተዘጋጀ በኦርቶዶክሳዊ ወጣትነት ላይ የሚያጠነጥን መጽሐፍ በፊት ከነበረው ተሻሽሎ ቀድሞ ያልተካተቱ አንዳንድ ጉዳዮችን በማካተት በድጋሚ ታትሟል!#ውድ ወጣቶች እንዲኹም ተተኪው ትውልድ የሚያሳስባችኹ ኹሉ ብታነቡት ታተርፉበታላችኹ!
#ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ...!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+1
📖#ተአምረ_ማርያም📖
#ተአምረ_ማርያም በአማርኛ እና በግእዝ ለምእመናን ጭምር ለንባብ እንዲመች ተደርጎ በጥሩ ኹኔታ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።በውስጡም ወደ 202 የሚደርሱ #የታመነችው_ብጽዕት_እናታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ያደረገቻቸውን ተአምራት የያዘ እንዲኹም ወረቀቱ በጥራት የተጠረዘ ሲኾን ሊኖረን ደግሞ ይገባል ..!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
💔🖤💔
በብዙዎች ዘንድ "የሀገር ዋርካ" እና "የሁሉም አባት" በመባል የሚታወቁት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር አርፈዋል።፣ በሀይማኖት አባትነታቸውና በአገር ሽማግሌነታቸው ከፍተኛ መከበርን ያገኙ ታላቅ መሪ ነበሩ። ህልፈታቸውም በመላው የሀገሪቱ የእስልምና እምነት ተከታዮችና በሌሎችም ኢትዮጵያውያን ዘንድ ጥልቅ ሀዘንን ፈጥሯል።
በሚዲያ በልዩ ልዩ መድረክ መልእክት ሲያስተላልፉ ንግግራቸው ስለሚስብ የሚሰሙ ክርስቲያን የሆኑ ወገኖች እንዳሉ አውቃለሁ። በክርስቲያኑ ማኅበረሰብ እንኳን ተወዳጅ የሃይማኖት አባት ናቸው።
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ በኢትዮጵያ የሃይማኖቶች መቻቻልና አብሮነት እንዲጎለብት ባደረጉት አስተዋጽኦ ሲታወሱ ይኖራሉ። ለመላው ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
+1
📚ተወዳጆች ...
#አኮቴተ_ቁርባን
#ቅዱስ_ጳውሎስ
በድጋሚ ታትመው ገበያ ላይ ውለዋል..!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
✨
...✍️#ለእግዚአብሔር የገባሁት ቃል ኪዳን የመረጋጋት እና የዝምታ ሕይወት ነበር ::እንደ ቃሌ ይህንን ሕይወት እየተለማመድኩ ሕሊናየ ከፍ ያለውን ነገር በሚመለከትበትና የሕይወት ፍልስፍናዬ ትክክል እንደሆነ እያመንኩ በመጣሁበት በዚህ ወራት ባልጠበቅኩት ጊዜና አጋጣሚ የተጫነብኝን ቀንበር ልሸከምበት የምችለውትከሻ አልነበረኝም :: ለእኔ አስፈላጊ የነበረው ነገር የስሜት ሕዋሳቶቼን በር ዘግቼ ከሥጋዊ እና ዓለማዊ ነገር ሁሉ ሸሽቼ ከራሴ ጋር ብቻ መሆንን ነው :: ከራስ ጋ ከመነጋገር የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ምን ነገር አለና ከማውቀው ከራሴ ጋር መወሰንን ወደድኩ :: ለራሴ እና ለእግዚአብሔር ነገርን እየተናገርኩ ከሚታይ እና ከሚዳሰሱ ነገሮች ሁሉ በላይ ትልቅ የሆነ ሕይወትን መኖርን ወደድኩ በልቡናዬ ውስጥ የምጫረውን ሰማያዊ ነገር ::
ከምድራዊ ሐሳብ ጋር ሳልቀላቅል መንፈሳዊ የሆነ ነገር በውስጤ እንዲያድር ማድረግ የዘወትር ፍላጎቴ ነበር ይህ ሐሳብ ንጹሕ መስታወት የሰውን መልክ እንዲያሳይ እግዚአብሔርን እንድንመለከት የሚያደርግ የልቡና መስታወት ነው ::በብርሃን ላይ ብርሃንን የሚጨምር በእውቀት ላይ እውቀትን የሚጨምር በተስፋ የሚጠብቁት የሚደሰቱበት ከቅዱሳን መላእክት ጋር ሆነው እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ስሜት ነው ::
"ከራስ ጋ ከመነጋገር የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ምን ነገር አለና ከማውቀው ከራሴ ጋር መወሰንን ወደድኩ ::"
[ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ]
📚ግዮን መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል]
[አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ!]
📖📖📖
ታሪከ ነገሥት
[ከምኒልክ፩ይ እስከ ምኒልክ ፪ይ]
#ይህ የመምህር ደሴ ሃይማኖትን አገናዝቦ የያዘ የምርምር ውጤት ነው:: ውጤቱም የጥንት የግእዝ ጽሑፎች ተርጉሞ ፣ የየዘመኑን ነገሥታት ታሪክ ያቀረበ ስለሆነ በሙያው ለተሰለፉ ሁሉ ጥሩ መረጃ ሊሆን ይችላል:: ከጥንት ጀምሮ የተጻፈው የሀገራችንን ታሪክ አንብቦ ለመረዳት ፣ የተጻፈበት ቋንቋ ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነው:: መምህር ደሴ ከፍተኛ የሆነ የግእዝ ዕውቀትን ተጠቅሞ የተለያዩ በግእዝ የተጻፉ የብራና መጻሕፍትን በመተርጎም እና ይዘታቸውን በማነጻጸር ይህን መጽሐፍ ታሪክ ነገሥት በሚል ርዕስ ለአንባብያንና ለተመራማሪዎች አበርክቷል:: ሌሎችን የሚያበረታታ ጥሩ ተግባር ነው::
✍️ባየ ይማም ( ፕሮፌሰር )
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
[ቻናላችንን ሼር ማድረግ አይርሱ!]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
💧አስገብተናል💧..
📖"#የዐዲሱ_ዓለም_ክርስትና_እና_የስሕበት_ሕግ_ከዐዲሱ_ዘመን_እንቅስቃሴ_እና_እሳቤ_ጋር"📖
"ይህንን መጽሐፍ የምጽፈው የኢትዮጵያ ልጆች በሥራ እንዲያምኑ ነው።" ያሉት የመጽሐፉ አዘጋጅ #ቀሲስ ዘበነ ለማ [ዶ/ር]፤ መጽሐፉን ጽፎ ለማጠናቀቅ ኹለት ዓመት የወሰደ መሆኑንና ከአንድ ዓመት በፊት ተጽፎ አልቆ አንዱን ዓመት ለመጽሐፍ ዝግጅት በሚሆን መልኩ ሥራዎች ለመሥራት እንደወሰደ ገልጸዋል።
"ለኢትዮጵያ የኒው ኤጅ እምነት አራማጆች ባለማወቅ ከሆነ ትምህርት ይሰጣል፤ አውቀውት ከሆነ ግን እንደ ፈረንጆቹ በግልጽ ወጥተው አምላኬ ሉሲፈር ነው በሉ።" በማለት ፀሐፊው ሃሳባቸውን ገልጠው መጽሐፉን ባርከው መርቀዋል።እኛም ከቡራኬው በኋላ አስገብተናል ብቅ በሉ ተሰናድቷል..!
ሼር...
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ራእየ_ኒፎን
የይቅርታ ፏፏቴ የርኅራኄ ባለጠጋ የሆንክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፊትህን ከእኔ አትመልስ፤ ማረኝ፤ ይቅርም በለኝ፡፡
ጌታ ሆይ “አላውቅህም አትበለኝ!' ጌታ ሆይ እስከዛሬ የት ነበርክ?' ብለህም አትቆጣብኝ፡፡ በኃጢአት የቆሸሽሁ፧ በበደል እንደ ጢስ የጠቆርሁ፤ ሕግህን በመተላለፍ የበሰበስሁ፤ ፍቅርህን በመርሳት የተዋረድሁ፤ በርኵሰት የሽተትሁ፤ በዲያብሎስ ምክር የጠፋሁ፤ ሰዎች በሚሠሩት አስነዋሪ ሥራም ዋነኛ የሆንኩ የማልጠቅም ትቢያና ጉድፍ ልጅህን አትናቀኝ፤ ከፊትህም አፍሬ አልመለስ፡፡
መምህሬ ሆይ! ከእኔ አትራቅ፤ ራራልኝ፤ አድነኝም፡፡ ሰው ወዳጅ ሆይ “አንተ የኃጢአተኛን በንስሐ ከክፉ መንገዱ መመለሱን እንጂ መጥፋቱን እንደማትሻ' አውቃለሁና ተመልሰህ እስክትረዳኝና ምሕረትህን እስካገኝ አላርፍም፡፡"
(ራእየ ኒፎን ገጽ 59)
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ራእየ_ኒፎን
የይቅርታ ፏፏቴ የርኅራኄ ባለጠጋ የሆንክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ፊትህን ከእኔ አትመልስ፤ ማረኝ፤ ይቅርም በለኝ፡፡
ጌታ ሆይ “አላውቅህም አትበለኝ!' ጌታ ሆይ እስከዛሬ የት ነበርክ?' ብለህም አትቆጣብኝ፡፡ በኃጢአት የቆሸሽሁ፧ በበደል እንደ ጢስ የጠቆርሁ፤ ሕግህን በመተላለፍ የበሰበስሁ፤ ፍቅርህን በመርሳት የተዋረድሁ፤ በርኵሰት የሽተትሁ፤ በዲያብሎስ ምክር የጠፋሁ፤ ሰዎች በሚሠሩት አስነዋሪ ሥራም ዋነኛ የሆንኩ የማልጠቅም ትቢያና ጉድፍ ልጅህን አትናቀኝ፤ ከፊትህም አፍሬ አልመለስ፡፡
መምህሬ ሆይ! ከእኔ አትራቅ፤ ራራልኝ፤ አድነኝም፡፡ ሰው ወዳጅ ሆይ “አንተ የኃጢአተኛን በንስሐ ከክፉ መንገዱ መመለሱን እንጂ መጥፋቱን እንደማትሻ' አውቃለሁና ተመልሰህ እስክትረዳኝና ምሕረትህን እስካገኝ አላርፍም፡፡"
(ራእየ ኒፎን ገጽ 59)
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
# ተወደጆች ...!
#እንኳን ለተባረከው ለወርኃ ጽጌ አደረሳችኹ...!
በዚህ ብሩክ ወቅት የጌታችንን እና የእመቤታችንን ስደት በተመስጦ እንድናጤን የተከፈለልንን ዋጋም ተመልክተን ከክፉ ፈቃዳት እንድንሰደድ ይገባናል!...ለዚህም የሚያግዙንን
በየሳምንቱ 3 መጻሕፍት ልጠቁም ወደድኹ....!
ለአኹኑ ሳምንት ....
#1 ማሕሌተ ጽጌ ግእዝ እና አማርኛ በማሕሌቱ ተመስጦ ምሥጢር እያስፈታ ከግብጽ በረሃ ኢትዮጽያ እያደረሰ የሚያነጉድ ነው !አስፈላጊ መጽሐፍ !
#2 ሰቆቃወድንግል የአባ ጽጌ ድንግል ፍሬ አንብቦ ልቡ የማይነካ እንባ የማይቀድመው የግብጽን በረሃ የእናታችንን እንባ በምናብ የማይቃኝ ልቡ የማይሰበርም አይኖርም ..! ወሳኝ ነው!
#3 ድርሳነ ቴዎፍሎስ ፦ በርግጥ በመጠን አነስ በቁምነገር ገዘፍ የሚል በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተዘጋጀ ስለ ሥደቷ ብቻ የሚተርክ ጥዑም መጽሐፍ! ይነበብ!
#የበረከት ጾም እንዲሁም ቁመት ያድርግልን...!
#ወዳጆቻችንን ሼር እያደረግን እንጋብዛቸው .!
📚ግዮን መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
✨ዜና መጽሐፍ
📖ክስብኤል📖
"በ451 ዓ.ም በኬልቄዶን ጉባኤ የንስጥሮስን እርሾ በመያዝ ወልድ ዋሕድ ሐዋርያት የኋላ ሊቃውንት ያስተማሩትን ትምህርት በሚፃረር በማስተማር ወይም በመወሰን ለቤተ ክርስቲያን መለያየት ዛሬ ድረስ እጅግ ተስፋፍቶ ለመገኘቱ ምክንያት ይህ ጉባኤ ነው፡፡ ይህ የንስጥሮስን ትምህርት ኹለት ባሕርይ በማለት ምንም አንድ አካል ቢሉም ባሕርይ በመነጠል ባሕርይ ያለ አካል አካል ያለ ባሕርይ የማይኖር በመኾኑ ኹለት አካል አስኝቶባቸዋል :: ”በኹለት ባሕርያት ካመኑስ ባሕርይ ያለ አካል ይገኝ ዘንድ አይችልም፤ አካልም አካልን በሚመስል ባሕርይ ነው እንጂ ያለ ባሕርይ ሊገኝ አይችልም:: ይኸውም ባሕርይ ነው፡፡ እነርሱ ኹለት ባሕርያት ካሉና ኹለት አካላት ናቸው። ይኸውም በክህሕደታቸው ካስተማረ ጋር አንድ ከሓዲ ንስጥሮስን መምሰላቸው ነው” (ሃይማኖተ አበው ዘዘካርያስ ም 91÷21)"
(ከውስጥ ገጽ የተወሰደ)
➮ይህ አዲሱ #ክስብኤል የተሰኘው መጽሐፍ አምላክ ወሰብእ በሚል ማእከላዊ አጀንዳ እግረመንገዱን በነገረ ሃይማኖት ና በነገረገረ ድኅነት እያሳለጠ የቅብዐቶች ሐሳብ በማንሳት ልከኛ ዕቅበት የሚሰጥ ጥሩሩ መጽሐፍ ነው።
#ጽሑፎችን በማንበብ እየተጠቀምን ጸሐፊያንን እናበረታታ !
#ተወዳጆች_ቻናላችንን_ሼር_በማድረግ_አይርሱ..!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ተወዳጆች...! መጽሐፈ ስንክሳር ለልጆች በእኔነት አተራረክ አጠር መጠን ብሎ የተዘጋጀ፥እንዲኹም በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረበ ሰናይ መጽሐፍ ነው ፤አዘጋጁን ዘኤልያስ እያመሰገንን ፥ተሻምተን ልጆቻችንን እንመግብ እንላለን ..!
#ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ...!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#የበገና መማሪያ ተሻሻሽሎ የቀረበ📖
ከዚህ መጽሐፍ ላይ ያለው የማስተማር ዘዴ መምህሬ መምህር ሲሳይ እኔን ያስተማረበትና እኔ የማውቀው ብቻ ከ750 በላይ በገና ደርዳሪዎች ያፈሩበት /የተገኙበት/ ነው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፉ ተማሪዎች ለብዙ ዓመታት ሲገጥማቸው የነበረውን የበገና አደራደር መለማመጃና መማሪያ መጽሐፍ ችግር የሚፈታ ሲሆን ይህን መጽሐፍ በትክክል አንብቦና ተረድቶ ለሚለማመድ ሁሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ በገና መደርደር ይችላል የሚል እምነት አለኝ።
ቀለል ባለ ዘዴ በገናን የመማሪያ መጽሐፍ ችግር ባለበት በአሁኑ ወቅት ይህ መጽሐፍ አንዲዘጋጅ የረዳን እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡
አቤል ተክዑ ኢንጂነር የበገና መምህር
📚ግዮን መጻሕፍት @GhionBookStore1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
t.me/GhionBookStore1623
‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል።
ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል እመቤታችንም በአበባው እንመስላታለን ጉድፍ የሌለባት ለነፍስም ለስጋም ደስ ምትል ውበት የስጋ ድንግልና የነፍስም ድንግል ናትና በእሷ መልክ ይሰየማል።
በነገረ ማርያምም እደተፃፈው እመቤታችን መውለጃዋ ቀን ሲደር በአረጋዊው ዮሴፍ ማረፊያ ቦታ ፈልጎ ከብዙ ድካም በኋላ በከብቶች በረት በሚያርፉበት ግርግም ተወለደ በጨርቅ ጠቅልላም አስተኛችው።
ጌታችን ኢየሱስም ሁለት አመት ሲሞላው ኄሮድስ ህፃኑን ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ "ተነስተህ እናቱን ና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ "ብሎ ለዮሴፍ ነገረው።
እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ ከመስከረም-26-ህዳር-6 ተሰደደች።
ፆመ ፅጌ የአዋጅ ፆም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ያለው ሰው በውዴታ ስደቷን ስቃዮዋን ለማስታወስ የፈለገ ብቻ በውዴታ የሚፆመው ፆም ነው።
ፆመ ፅጌ የድንግልን ስደት ለምለም አካላቷ ያልጠና ሰውነቷ ጥፍሯ እስኪነቀል ድረስ በሀሩሩ በውርጭኝ ያለ ሀጢያቷ እንግልት በማየቷ በረከትን ለማግኘት እንፆማለን ማለት ነው።
የተባረከ ፆም እንዲሆን ፍቃዷ ይሁንልን🙏
‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል።
ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል እመቤታችንም በአበባው እንመስላታለን ጉድፍ የሌለባት ለነፍስም ለስጋም ደስ ምትል ውበት የስጋ ድንግልና የነፍስም ድንግል ናትና በእሷ መልክ ይሰየማል።
በነገረ ማርያምም እደተፃፈው እመቤታችን መውለጃዋ ቀን ሲደር በአረጋዊው ዮሴፍ ማረፊያ ቦታ ፈልጎ ከብዙ ድካም በኋላ በከብቶች በረት በሚያርፉበት ግርግም ተወለደ በጨርቅ ጠቅልላም አስተኛችው።
ጌታችን ኢየሱስም ሁለት አመት ሲሞላው ኄሮድስ ህፃኑን ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ "ተነስተህ እናቱን ና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ "ብሎ ለዮሴፍ ነገረው።
እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ ከመስከረም-26-ህዳር-6 ተሰደደች።
ፆመ ፅጌ የአዋጅ ፆም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ያለው ሰው በውዴታ ስደቷን ስቃዮዋን ለማስታወስ የፈለገ ብቻ በውዴታ የሚፆመው ፆም ነው።
ፆመ ፅጌ የድንግልን ስደት ለምለም አካላቷ ያልጠና ሰውነቷ ጥፍሯ እስኪነቀል ድረስ በሀሩሩ በውርጭኝ ያለ ሀጢያቷ እንግልት በማየቷ በረከትን ለማግኘት እንፆማለን ማለት ነው።
የተባረከ ፆም እንዲሆን ፍቃዷ ይሁንልን🙏
📚#መዝሙረ፡ዳዊት፡ንባቡና፡ትርጓሜው
#መዝሙረ፡ዳዊት፡ መነኮሳት፡ካህናት፡መዘምራንም፡በዜማ፡ በንባብ ፡ በቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ በመዓልትም ፡ በሌሊትም ፡ ሳያቋርጡ ፡ እን ዲጸልዩበት፤ ምእመናንም ፡ ከሌላው ፡ ጸሎት፡ይልቅ፡እሱን፡መላልሰው፡ እንዲጸልዩ ፡ የታዘዙ ፤ ኤፌ ፡ ፭ ፡ ፲፱ ። መዝሙር ፡ ፴፫ ፡ ፩ ። በሰማይና በምድር ፡ ያሉ ፡ ሁሉ ፡ በዳዊት ፡ ቃል ፡ ይዘምራሉ ፡ ተብሎ ፡ የተነገረለት፡ በመሆኑ ፡ ከሁሉ ፡ ይበልጥ ፡ ተፈላጊ ፡ መሆኑ ፡ ሲታወቅ ፡ የትርጓሜውም ፡ ዋና ፡ ጥቅሙ፡ ምስጢሩን ፡ ሳያውቁ ፡ የሚጸልዩበት ምእመናን ፡ ምስጢሩን ፡ ዐውቀው ፡ እንዲጸልዩ ፡ ማድረግ ፡ ነው ።-ስለዚህ ፡ ይኸ ፡ መዝሙረ ፡ ዳዊት ፡ ከጥንት ፡ አባቶች ፡ እንደ ፡ ተረ ጐሙትና ፡ ሲወርድ ፡ ሲዋረድ ፡ እንደ ፡ መጣው ፡ ንባቡና ፡ ትርጓሜው ፡ ተጽፎና ፡ ታርሞ ፡ በግርማዊ ፡ ጃንሆይ ፡ ቀዳማዊ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ ፡ ትእ ዛዝ ፡ በብፁዕ ፡ አቡነ ፡ ባስልዮስ ፡ ፈቃድ ፡ ባ፲፱፻፶ (1950)፡ ዓ ∙ ም ፡ ታተመ ▪
[''አባ ፡ ቴዎፍሎስ ፡
የሐረር ፡ ጳጳስና ፡ የኢትዮጵያ ፡ ሊቀ ፡ ጳጳሳት ፡ ዋና ፡ እንደራሴ "]
📚ግዮን መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
✨✨✨✨#ውድ_የግዮን_ቤተሰቦች_እንኳን_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ወርኃዊ መታሰቢያ በዓል አደረሳችኹ ፤ እያልን
#ገድለ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ወንጌላዊ) መጥቷልና ብቅ በሉ..!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ዜና_አበው 📖
[ዘውእቱ መጽሐፈ ገነት ካልዕ]
#የአባቶች ንግግር የመንፈሳዊ ሕይወት ትርጉም ነው፡፡ በቅድስና አኗኗር ውስጥ የሚነገሩ ቃላቶች የመንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ፍሬዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን ማደሪያዎቹ በሆኑ በቅዱሳን ኑሮ ላይ እናገኛቸዋለን፡፡ ያ የመንፈስ ፍሬም ነገረ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቢሰሙት የማይሰለቹት ቢያወሩት የማይጠግቡት ሁልጊዜ መንፈስን የሚያድስ ህሊናን የሚያለመልም ንግግር ነው። በመምህር አብርሃም ፈቃዴ ተተርጉሞ የቀረበልን ዜና አበዊነ ቅዱሳን የሚለው መጽሐፍም ይሄው የአባቶች ጥልቅ ድንቅ የሕይወት ጣዕመ ንግግር ነው᎓᎓ በዘመናቸው ደርሰን በአካለ ሥጋ የማናያቸው አባቶቻችን ዕለት ዕለት እንዲመክሩን የሕይወት ጣዕማቸው ይሄው ደርሶናል፡፡ ወንጌል በሕይወት ስትገለጥ ምን እንደምትመስል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው፡፡በጣዕመ መንፈስ ቅዱስ ከታሹ አባቶች ጋራ ማውራት ምን ያህል ጥቅም እንዳለው ለመረዳት እስከ መጨረሻው ማንበብ ነው።
#የኔታ_ገብረ_መድኅን_እንየው
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+2
♦ነፍሳችሁ በደጋጎች በፃድቃን ጎን እንዲያርፍ የእግዚአብሔር ፍቃድ ይሁን 🙏
🖤 #ነፍስ_ይማር 🖤🖤
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን አመታዊ ክብረበዓልን አስመልክቶ ከጠዋቱ 1:45 ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ሰዓት ለፊኒሺንግ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ በርካታ ምእመናን ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል ።
የቅዱሳኑ አምላክ ነፍሳቸዉን በቅዱሳን #ዘንድ_በሰላም_ያሳርፋቸዉ 🤲
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
