ar
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

الذهاب إلى القناة على Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

إظهار المزيد
3 310
المشتركون
-324 ساعات
-87 أيام
-3530 أيام
أرشيف المشاركات
📚«#ድርገት»📚 #መጽሐፉን ለማዘጋጀት ያነሣሣኝ ምክንያት ከዚህ ቀደም በቅዳሴ እና በሥርዓቱ ዙሪያ ለተሠሩ ሥራዎች ላዘጋጆቹ መምህራን ከፍተኛ አክብሮት የምሰጥ መኾኑን እየገለጥኩ ኾኖም በተዘጋጁ መ
📚«#ድርገት»📚 #መጽሐፉን ለማዘጋጀት ያነሣሣኝ ምክንያት ከዚህ ቀደም በቅዳሴ እና በሥርዓቱ ዙሪያ ለተሠሩ ሥራዎች ላዘጋጆቹ መምህራን ከፍተኛ አክብሮት የምሰጥ መኾኑን እየገለጥኩ ኾኖም በተዘጋጁ መጻሕፍት ውስጥ ይህ ቢከታተት ጥሩ ይኾን ነበር ያልኳቸውንና በአገላለጥ ስወር ያሉትንና ያልተዳሰሱ ጉዳዮችን ከመጻሕፍትና ዐበይት መምህራን ካስተማሯቸው ትምህርት እንዲሁም ካቀረቧቸው ጥናታዊ ጽሑፎች በማጠናቀር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው ድረስ ያለውን የቅዳሴን ሥርዓትና የያዘውን መለኮታዊ ምስጢር ለመቃኘት ይህቺን «ድርገት» የተሰኘች አነስተኛ መጽሐፍ ለማዘጋጀት በቅቻለሁ:: ✍️ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምጸ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#የቅዳሴ_ሥርዐት_አፈጻጸም ....በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ዋናው የአምልኮት ሥርዓት የሚፈጸምበት ሥርዐተ ቅዳሴ ነው፡፡ ቅዳሴ ታላቅ የክርስትና ምሥጢር ነው፡፡ የሁሉም ዕውቀትና አገልግሎትም
📚#የቅዳሴ_ሥርዐት_አፈጻጸም ....በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ዋናው የአምልኮት ሥርዓት የሚፈጸምበት ሥርዐተ ቅዳሴ ነው፡፡ ቅዳሴ ታላቅ የክርስትና ምሥጢር ነው፡፡ የሁሉም ዕውቀትና አገልግሎትም መጠቅለያና ማሳረጊያው ቅዳሴ ነው፡፡ ኅብረታዊት ቤተ ክርስቲያን በአንድነት የምትገለጥበት፣ በምድር ተጋድሏችን ያልጨረስን በጉዞ ላይ ያለን ክርስቲያኖች ከጌታችን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም በመሳተፍ ዘለዓለማዊ ሕይወትን የምናገኝበት የድኅነታችን በር ነው፡፡ ይህ ቀሲስ አያሌው ጎበዜ ያዘጋጁት “የቅዳሴ ሥርዓት አፈጻጸም” የተባለ መጽሐፍ የቅዳሴን አጀማመር፣ ታሪካዊ እድገቱን፣ የቅዳሴውን አፈጻጸም...የሚያስረዳ ድንቅ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ ስለዚህ አንብበን፣ ዐውቀን፣ ሥርዓቱን ጠንቅቀን፣ በቅዱስ ቊርባን ታትመን ዘለዓለማዊ ሕይወትን እናገኝ ዘንድ እነሆ ብለውናል፡፡ ቅዱስ መጻሕፍትን አንብቦ የሚጠግባቸው የለም ይልቁንም ጥበብን የሚሹና የማዳንን ዕውቀት ገንዘብ ላደረጉ እንዲል ሊቁ ቄርሎስ! እነሆ ጥበብና የመዳንን ዕውቀት ገንዘብ እናደርግ ዘንድ ይህን መጽሐፍ እንመገብ! ✍️ መ/ር ሰሎሞን ላመስግን [የብሉያት እና ሐዲሳት መጻሕፍት መምህር] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

ጥንተ ስቅለተ ክርስቶስ መጋቢት ፳፯ ቀን ነው።በዚህችም ዕለት በዕለተ ዓርብ ከሦስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት የተቀበላቸው መከራዎችም እጅግ በጣም ብዙዎች ናቸው፡፡ ጥቂቶቹን ለማስታወስ ያህል፣ በሚያሰቅቅና
ጥንተ ስቅለተ ክርስቶስ መጋቢት ፳፯ ቀን ነው።በዚህችም ዕለት በዕለተ ዓርብ ከሦስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት የተቀበላቸው መከራዎችም እጅግ በጣም ብዙዎች ናቸው፡፡ ጥቂቶቹን ለማስታወስ ያህል፣ በሚያሰቅቅና በሚዘገንን ሁኔታ በጅራፍ ተገርፎአል፤ መስቀሉን ተሸክሞ በቀራንዮ ተራራ እየወደቀ እየተነሣ፣ የገዢው የጲላጦስ ወታደሮችም እያዳፉት፣ ርኩስ ምራቃቸውንም እየተፉበትና እያፌዙበት ወደ ተራራው እንዲወጣ ተደርጎአል፡፡ ስለእሱ የተጻፈው የነቢያት ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ልብሱን ገፈው ከለሜዳ አልበሰውታል፡፡ በልብሱም ላይ ዕጣ ተጣጥለው ተካፍለውታል፤ የእሾህ አክሊል ጕንጕን በራሱ ላይ በማድረግ የሰማይና የምድር ንጉሥ እንዳልሆነ ሁሉ “ንጉሥ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን” እያሉ ተሳልቀውበታል፡፡ በመጨረሻም ጐኑን በጦር ወግተውታል፡፡ እጆቹን እና እግሮቹን በአምስቱ ችንካሮች (ቅንዋት) ቸንክረው በመስቀል ላይ ተሰቀለ ፡፡ የማይሞተው ሞተ!ዘንድሮ ደግሞ ኹለቱ ታላላቅ የጌታችን በዓላት አንድ ቀን ገጥመዋል። #ጥንተ_ስቅለቱ_እና_በዓለ_ሆሳዕና መድኃኔዓለም በቸርነቱ ይማረን፤ከበዓላቱ ረድኤት ይክፈለን!
«የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::» (፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭)

📚#ልማድና_ክርስትና «…ከንስሐ አንጻር ቀኖና ማለት ኃጢአታችንን ከተናዘዝን በኋላ ካህኑ የሚሰጠን እና የምንፈጽመው ድርጊት ማለት ሲሆን እኛ በተለምዶ ቅጣት የምንለው ነው፡፡ ቅጣት ግን አይባልም ሕ
📚#ልማድና_ክርስትና «…ከንስሐ አንጻር ቀኖና ማለት ኃጢአታችንን ከተናዘዝን በኋላ ካህኑ የሚሰጠን እና የምንፈጽመው ድርጊት ማለት ሲሆን እኛ በተለምዶ ቅጣት የምንለው ነው፡፡ ቅጣት ግን አይባልም ሕክምና እንጂ ምከንያቱም ማንም ወደ ሆስፒታል ሔዶ ተመርምሮና መድኃኒት ታዝዞለት ወደ ሰፈሩ ሲመጣና የሰፈሩ ሰዎች “አንዴት ሆንክ” ብለው ሲጠይቁት “ታከሜ መጣሁ” ይላል እንጂ ተቀጥቼ መጣሁ አይልም፡፡ የነፍሳችን ሐኪም የሆነው ካህንም አክሞ ይልከናል እንጂ እየቀጣን አይደለም ካህኑ ለሕከምና የሚያዝዝልን መድኃኒቶች እንደ አፈጻጸም አቅማችን ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ ምጽዋት ሊሆን ይችላል ይህንን በጥንቃቄና በፍፁም እምነት ኃጢአታችንን እያሰብንና እያለቀስን መፈጸም ይገባል…» [ከውስጥ ገጽ የተወሰደ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ሰው_ግብረገብና_ሥነ_ምግባር የዘመናችን ቁልፍ ጉዳዮች ኢትዮጵያና ዓለም- አቀፍ ግብረገብ የኢትዮጵያ ታሪክ ሲመረመር ለዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ምቹ ሆና የቆየች ሀገር መሆኗን ያሳያል፡፡ ከተለያዩ
📚#ሰው_ግብረገብና_ሥነ_ምግባር የዘመናችን ቁልፍ ጉዳዮች ኢትዮጵያና ዓለም- አቀፍ ግብረገብ የኢትዮጵያ ታሪክ ሲመረመር ለዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ምቹ ሆና የቆየች ሀገር መሆኗን ያሳያል፡፡ ከተለያዩ ሀገሮችና መንግሥታት ጋር የሰላም፣ የወዳጅነትና የትብብር ግንኙነት የነበራትና ያላት ሀገር ናት:: ካልመጡባት በቀር ለጠብ የሄደችባቸው ሀገሮች ወይም መንግስታት የሉም ማለት ይቻላል። እንዲደረግባት የማትፈቅደውን ነገር በሌሎች ሀገሮች ላይ ለማድረግ ተነሳስታ አታውቅም:: የዐበይት አለም አቀፍ ድርጅቶች መሥራችና አባል ሀገርም ናት:: የገባችባቸውን ውሎች አቅም በፈቀደ መሠረት ታከብራለች:: የተሰጣትን የተለያዩ የዓለም አቀፍ ተልዕቿዎች ተወጥታለች:: ለነፃነት፣ ለእኩልነትና ሉአላዊነት ለታገሉ ሀገሮችና ሃይሎች ረድታለች:: የሚጠበቅባትን ዓለም _ አቀፋዊና _ ግበረገባዊ ግዴታዋን ተወጥታለች፡: ግን ከተወጣቻቸው ግብረገባዊ ግዴታዎቿ አንጻር የራሷ ግብረገባዊ መብትስ ተከብሮላት ይሆን? (ከውስጥ ገጽ) 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ቅዱስ_አትናቲዎስ_ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ “የእግዚአብሔርን ርቱዕ ፍርድ መጠበቅና ቃሉን መፈጸም በአንድ በኩል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ጥፋትን በሕይወት መለወጥ - ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ማድረ
📚#ቅዱስ_አትናቲዎስ_ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ “የእግዚአብሔርን ርቱዕ ፍርድ መጠበቅና ቃሉን መፈጸም በአንድ በኩል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ጥፋትን በሕይወት መለወጥ - ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ማድረግ የሚቻለው እርሱ (እግዚአብሔር) ብቻ ነውና። … ሕግን በማፍረስ ምክንያት በሰው ላይ የመጣው የሞት ዕዳ ይከፈል ዘንድ ስለሁሉም ተገብቶ የሚሞት፣ እርሱ ግን ከሞት ዕዳ ነጻ የሆነ እንዲሁም ሞትን ማሸነፍ የሚችል ቤዛ ያስፈልግ ነበርና። ... ሆኖም ቃል በባሕርዩ ኢመዋቲ በመሆኑ ሞት ስለማይስማማው ስለሁሉ ተገብቶ ይሞት ዘንድና የሁላችንንም በደል ተሸክሞ መሥዋዕት ሆኖ ይቀርብ ዘንድ ሞት የሚስማማውን የእኛን ባሕርይ ገንዘብ አደረገ።” (ከውስጥ ገጽ) 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

#ኢቮሊዩሺን የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት? ይህ “ኢቮሊዮሺን - የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ ሃይማኖት?” የሚለው ድንቅ መጽሐፍ፣ ሳይንስ መስለው የሚነገሩትንና እንደ ዶግማ የሚታዩትን የኢቮሊዩሺን ቲ
#ኢቮሊዩሺን የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት? ይህ “ኢቮሊዮሺን - የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ ሃይማኖት?” የሚለው ድንቅ መጽሐፍ፣ ሳይንስ መስለው የሚነገሩትንና እንደ ዶግማ የሚታዩትን የኢቮሊዩሺን ቲዎሪ እሳቤዎችን ከመሠረታቸው በመመርመርና በቂ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ፣ እነዚህ መላ-ምቶች ሳይንስ እንዳልሆኑ ግልጽ አድርጎ አቅርቦልናል። ይህ የመምህራችን የመምህር ያረጋል አበጋዝ ለትውልድ የሚተላለፍ ድንቅ ሥራቸው፣ በተለይ ትንሽ አስኳላ ትምህርት ለዘለቀው ማኅበረሰብ ሕሊናውን የሚያነቃበትና ራሱን የሚፈትሽበት ጠቃሚ መጽሐፍ እንደሆነ አምናለሁ። መምህራችን ከዚህ በፊት “ሳይንሰ እና ሃይማኖት” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ያቀረቧቸውን ግሩም ሐሳቦች አጣጥመን ሳንጨርስ ይህን ጥልቅና የብዙዎቻችንን ጥያቄ የመለሱበትን ጠቃሚ መጽሐፍ በማበርከታቸው እግዚአብሔር ይስጥልን፣ በዕድሜ በጸጋ ይጠብቅልን፣ በቀጣዩስ ምን እንጠብቅ? እያልኩ ለአንባብያን መልካም ንባብ እላለሁ። ዲ/ን ዶ/ር ዮሴፍ አጥላው - የሥነ-ኬሚካል ተመራማሪ፣ በአስትራዜኒካ ፋርማሲቲካል የመድኃኒት ምርምርና ማጎልበቻ ድርጅት 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ማርያምን ያኮረፈው አያ ተክለ ሥላሴ አያ ተክለ ሥላሴ እመቤታችንን ከልብ የሚወዳት ከመሆኑ የተነሣ በየዓመቱ ጥር 21 ቀን አስተርዮ ማርያምን ቤት ሙሉ በመደገስ ሰንጋ እያረደ
📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ማርያምን ያኮረፈው አያ ተክለ ሥላሴ አያ ተክለ ሥላሴ እመቤታችንን ከልብ የሚወዳት ከመሆኑ የተነሣ በየዓመቱ ጥር 21 ቀን አስተርዮ ማርያምን ቤት ሙሉ በመደገስ ሰንጋ እያረደ ይዘክራት ነበር፡፡ በመካከሉ ሐሳቡን የሚገታ ነገር ገጠመው፤ ታቦተ ማርያም ከታች ደለማ አብዛኛው ሕዝብ ወዳለበት ወደ ላይ ደለማ በመውጣቷ የተነሣ ከገደል በታችና ከገደል በላይ ያሉት ሕዝቦች አምርረው ተጣልተው ነበር፡፡ ታች ደለማዎች “ታቦታችንን ከነበረበት ትመልሳላችሁ" የሚል ክስ አቅርበው ክርክሩ እስከ አቡነ ባስልዮስ ደርሶ ነገሩ በእርቅ ሲያልቅ አያ ተክለ ሥላሴ እመቤታችን እስከ መጨረሻው ወደ ታች ደለማ የማትመለስና ለታችኛው ሕዝብ ታቦተ መድኃኔ ዓለም ተሰጥቶ ነገሩ በዚሁ ማክተሙን ተረዳ፡፡ ይህ ሁኔታ ያስከፋው በመሆኑ ምርር ብሎ “እመቤቴ ማርያም፤ የኔን ወዳጅነት ትተሸ ጓያ የሚያመርቱትን ደጎች (ከደጋው የሚኖሩ) መርጠሸ ከሄድሽ በምን እንደሚያስቀድሱሽ አያለሁ፡፡ ከእንግዲህ እነርሱ ያዋጡሽ፣ ከኔ ጋር ተለያየን" በማለት ከታች ደለማ ተነሥቶ በርቃቶ ከተባለው ቀበሌ ቤት ሠርቶ ተቀመጠ።            (ከውስጥ ገጽ) 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ኦርቶዶክሳዊ_የጸሎት_ሕይወት #ትርጉም ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📚#ኦርቶዶክሳዊ_የጸሎት_ሕይወት #ትርጉም ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ኦርቶዶክሳዊ_የጸሎት_ሕይወት #ትርጉም ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📚#ኦርቶዶክሳዊ_የጸሎት_ሕይወት #ትርጉም ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

ጌታችን ከደቀ መዛሙርቱ ኹሉ ቅዱስ ዮሐንስን አብልጦ ይወድዳል። ከፍጥረት ኹሉ ከተባለ ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እጅግ አብልጦ ይወድዳል። የእግዚአብሔር የኾኑት በፍቅሩ ዕቅፍ ያረፉ ኹ
ጌታችን ከደቀ መዛሙርቱ ኹሉ ቅዱስ ዮሐንስን አብልጦ ይወድዳል። ከፍጥረት ኹሉ ከተባለ ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እጅግ አብልጦ ይወድዳል። የእግዚአብሔር የኾኑት በፍቅሩ ዕቅፍ ያረፉ ኹሉ ደግሞ እርሷን በጣም ይወድዳሉ። ድንግል ሆይ እንወድድሻለን !!! የድንግል ልጆች መስክሩ።

የቤተ ክርስቲያን ታሪክ #የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በራሷ ቋንቋ የምትመሰክረው ከራሷ ማንነት (Identity) ጋር የሚመሳሰል እምነት እያላት እንደ ሌላት በመቊጠር የገዛ ልጆቿን
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ #የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በራሷ ቋንቋ የምትመሰክረው ከራሷ ማንነት (Identity) ጋር የሚመሳሰል እምነት እያላት እንደ ሌላት በመቊጠር የገዛ ልጆቿን ከጉያዋ እየነጠቁ እየወሰዱ በእርሷ እንዲነሡባት የጥላቻን ትምህርት የሚያስተምሩ አያሌ ናቸው:: ታዲያ ይህ ተንኮል ያልገባው የእኔ አገር ልጅ እውነት የሚናገሩ እየመሰለው እንደ ጠፍ ከብት ወደ ነዱት ይሔዳል፡፡ እነርሱ ግን ዓላማቸው የእግዚአብሔር መንግሥት አይደለም፤ የላካቸውም እግዚአብሔር አይደለም፡፡ አምጣ የወለደቻቸው ልጆቿ በመጤ ሃይማኖትና ባህል ሲበከሉ ቤተ ክርስቲያናችን ዝም ብላ መመልከት አይገባትም፡፡ እነርሱ ዛሬ ብዙ የመስበኪያና የመሳቢያ ስልት እንዳላቸው የታወቀ ነው። የእኛም ቤተ ክርስቲያን “እሾህ በእሾህ ይነቀሳል” እንደሚባለው በተመሳሳይ ዘዴ ልጆቿን ከያሉበት መሰብሰብ ይገባታል፤ እነርሱም ቃሏን ሰምተው ነገ ዛሬ ሳይሉ ይመለሱ፤ የሰው ቤት የራስ አይሆንምና፡፡ [ከውስጥ ገጽ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

"ዐራተኛው ሰው" ማን ነው? መጋቢት ፲፱ ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ  በዓል በቤተክርስቲያን ታሪክ "የሠለስቱ ደቂቅ" በዓል ተብሎ ይከበራል። ታሪኩ የጥንቷ ባቢሎን ቢሆንም፣ መልእክቱ ግን የዛሬው የሁላችንም የዕለት ተዕለት የሕይወት ትግል ነው። ዛሬም እንደ ባቢሎን ሜዳ፣ በዙሪያችን የሚነዱ "የእሳት እቶኖች" ሞልተዋል። ​🔥 የዘመናችን እቶኖች፦ ሲነዱ የማናያቸው እሳቶች ​የባቢሎኑ እሳት ቁሳዊና የሚታይ ነበር፤ የዛሬው እሳት ግን ረቂቅና የሚሰማ ነው። የጭንቀት እቶን፦ "ነገ ምን እሆናለሁ?" የሚል ስጋት፣ የኢኮኖሚ ጫና እና የቤተሰብ ኃላፊነት ልክ እንደ ሰባት እጥፍ እሳት ትውልዱን እየለበለቡት ይገኛሉ። የብቸኝነት እቶን፦ በሰው መካከል እየኖሩ "ሰው ማጣት"፣ ማንም የማይረዳው ውስጣዊ ስቃይና የሐዘን ነበልባል ብዙዎችን እያቃጠለ ነው። የጥላቻና የክፋት እቶን፦ በሥራ ቦታ፣ በማኅበራዊ ሕይወትና በምንኖርበት ዓለም ውስጥ በቅናትና በክፋት የሚለኮሱ እሳቶች ሕይወታችንን ፈታኝ አድርገውታል። ​📜እሳቱ ለምን አልጠፋም? ​ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አንድ ድንቅ ምስጢር ይነግሩናል። ቅዱስ ገብርኤል ወደ እቶኑ ሲወርድ እሳቱን አላጠፋውም፤ ይልቁንም "ባሕርዩን ለወጠው" እንጂ። ለሕፃናቱ እሳቱ ወደ በረድነት ተቀየረላቸው፤ ለገዳዮቻቸው ግን እንደነደደ ነበር። ​ይህ ለሕይወታችን ትልቅ ትርጉም አለው፦ እግዚአብሔር መከራውን ከዓለም ላይ ላያጠፋው ይችላል፤ ነገር ግን በመከራው ውስጥ እንድንጸና፣ መከራው እንዳያቃጥለንና እንዲያውም መከራው ለበረከት እንዲሆንልን "ባሕርዩን የመለወጥ" ኃይል አለው። ​✨ "አራተኛው ሰው" — የድላችን ምሥጢር ​ናቡከደነጾር እቶኑን ሲመለከት ደነገጠ። "የጣላቸው ሦስት ሰዎች ነበሩ፤ አሁን ግን አራተኛው በመካከላቸው ይታየኛል" አለ። በሕይወትህ ውስጥ ብቻህን አይደለህም ፤ በደረሰብህ መከራና በወደቅክበት እቶን ውስጥ ብቻህን አይደለህም። ያ "አራተኛው ሰው" — ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል — በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ከጎንህ ቆሟል። መከራው መሸጋገሪያ ነው፦ ሦስቱ ሕፃናት ወደ እሳቱ ባይጣሉ ኖሮ፣ የመልአኩን ተራዳኢነት ባላዩ ነበር። ዛሬ የሚያቃጥልህ መከራ ነገ የምስክርነትህ መድረክ ይሆናል። የእምነት ጽናት፦ "አምላካችን ቢያድነንም ባያድነንም..." የሚለው የሕፃናቱ ቃል፣ ዛሬ ላለን ሰዎች ትልቅ ትምህርት ነው። ለእውነት ስትቆም እሳቱ የበረድ ጠል የመሆን ግዴታ አለበት። ​✍️ ወደ በረድነት የሚለወጥ ሕይወት ​የመጋቢት ፲፱ ወርሐዊ በዓል መልእክቱ ግልጽ ነው፦ "እሳቱ ይነዳል፤ ገብርኤል ግን ያበርደዋል።" ዛሬ በኑሮህ፣ በጤናህ ወይም በሐሳብህ እቶን ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። በባቢሎን ሜዳ የደረሰው መልአክ፣ ዛሬም በቤትህና በልብህ አለ። ​ጭንቀታችን ወደ ደስታ፣ መከራችን ወደ በረከት የሚለወጥበት የመጋቢት የብሥራት ወር ይሁንልን ​📜ሰላም ለከ ገብርኤል ኃይለ እግዚአብሔር ልዑል፤ ዘአድኃንኮሙ ለሠለስቱ ደቂቅ እም እሳተ ነበልባል!" ​እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ​----------------------- ©️ደምፀ በቀለ ፥ የጉባኤ ደብረ ምጥማቅ የሐዲስ ኪዳን ደቀመዝሙር

"ዐራተኛው ሰው" ማን ነው? መጋቢት ፲፱ ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ  በዓል በቤተክርስቲያን ታሪክ "የሠለስቱ ደቂቅ" በዓል ተብሎ ይከበራል። ታሪኩ የጥንቷ ባቢሎን ቢሆንም፣ መልእክቱ ግን የዛሬው የሁላችንም የዕለት ተዕለት የሕይወት ትግል ነው። ዛሬም እንደ ባቢሎን ሜዳ፣ በዙሪያችን የሚነዱ "የእሳት እቶኖች" ሞልተዋል። ​🔥 የዘመናችን እቶኖች፦ ሲነዱ የማናያቸው እሳቶች ​የባቢሎኑ እሳት ቁሳዊና የሚታይ ነበር፤ የዛሬው እሳት ግን ረቂቅና የሚሰማ ነው። የጭንቀት እቶን፦ "ነገ ምን እሆናለሁ?" የሚል ስጋት፣ የኢኮኖሚ ጫና እና የቤተሰብ ኃላፊነት ልክ እንደ ሰባት እጥፍ እሳት ትውልዱን እየለበለቡት ይገኛሉ። የብቸኝነት እቶን፦ በሰው መካከል እየኖሩ "ሰው ማጣት"፣ ማንም የማይረዳው ውስጣዊ ስቃይና የሐዘን ነበልባል ብዙዎችን እያቃጠለ ነው። የጥላቻና የክፋት እቶን፦ በሥራ ቦታ፣ በማኅበራዊ ሕይወትና በምንኖርበት ዓለም ውስጥ በቅናትና በክፋት የሚለኮሱ እሳቶች ሕይወታችንን ፈታኝ አድርገውታል። ​📜እሳቱ ለምን አልጠፋም? ​ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አንድ ድንቅ ምስጢር ይነግሩናል። ቅዱስ ገብርኤል ወደ እቶኑ ሲወርድ እሳቱን አላጠፋውም፤ ይልቁንም "ባሕርዩን ለወጠው" እንጂ። ለሕፃናቱ እሳቱ ወደ በረድነት ተቀየረላቸው፤ ለገዳዮቻቸው ግን እንደነደደ ነበር። ​ይህ ለሕይወታችን ትልቅ ትርጉም አለው፦ እግዚአብሔር መከራውን ከዓለም ላይ ላያጠፋው ይችላል፤ ነገር ግን በመከራው ውስጥ እንድንጸና፣ መከራው እንዳያቃጥለንና እንዲያውም መከራው ለበረከት እንዲሆንልን "ባሕርዩን የመለወጥ" ኃይል አለው። ​✨ "አራተኛው ሰው" — የድላችን ምሥጢር ​ናቡከደነጾር እቶኑን ሲመለከት ደነገጠ። "የጣላቸው ሦስት ሰዎች ነበሩ፤ አሁን ግን አራተኛው በመካከላቸው ይታየኛል" አለ። በሕይወትህ ውስጥ ብቻህን አይደለህም ፤ በደረሰብህ መከራና በወደቅክበት እቶን ውስጥ ብቻህን አይደለህም። ያ "አራተኛው ሰው" — ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል — በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ከጎንህ ቆሟል። መከራው መሸጋገሪያ ነው፦ ሦስቱ ሕፃናት ወደ እሳቱ ባይጣሉ ኖሮ፣ የመልአኩን ተራዳኢነት ባላዩ ነበር። ዛሬ የሚያቃጥልህ መከራ ነገ የምስክርነትህ መድረክ ይሆናል። የእምነት ጽናት፦ "አምላካችን ቢያድነንም ባያድነንም..." የሚለው የሕፃናቱ ቃል፣ ዛሬ ላለን ሰዎች ትልቅ ትምህርት ነው። ለእውነት ስትቆም እሳቱ የበረድ ጠል የመሆን ግዴታ አለበት። ​✍️ ወደ በረድነት የሚለወጥ ሕይወት ​የመጋቢት ፲፱ ወርሐዊ በዓል መልእክቱ ግልጽ ነው፦ "እሳቱ ይነዳል፤ ገብርኤል ግን ያበርደዋል።" ዛሬ በኑሮህ፣ በጤናህ ወይም በሐሳብህ እቶን ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። በባቢሎን ሜዳ የደረሰው መልአክ፣ ዛሬም በቤትህና በልብህ አለ። ​ጭንቀታችን ወደ ደስታ፣ መከራችን ወደ በረከት የሚለወጥበት የመጋቢት የብሥራት ወር ይሁንልን ​📜ሰላም ለከ ገብርኤል ኃይለ እግዚአብሔር ልዑል፤ ዘአድኃንኮሙ ለሠለስቱ ደቂቅ እም እሳተ ነበልባል!" ​እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ​----------------------- ©️ደምፀ በቀለ ፥ የጉባኤ ደብረ ምጥማቅ የሐዲስ ኪዳን ደቀመዝሙር

📚#ጉባኤያተ ቤተ ክርስቲያን ከ50-380ዓ.ም .....የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ «የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡
📚#ጉባኤያተ ቤተ ክርስቲያን ከ50-380ዓ.ም .....የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ «የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ከኢየሩሳሌሙ የሐዋርያት ጉባኤ እስከ ቊስጥንጥንያ የነበሩትን ጉባኤያት በግሩም አቀራረብ ቃኝቶ በመልካም ትርጓሜ አቅርቦልናል። መልካም ንባብ!      በአማን ነጸረ [ደብተራና የሕግ ባለሙያ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623