ar
Feedback
ሰበዝ ሥልጠና እና ማማከር አገልግሎት Sebez Training and Consultancy services

ሰበዝ ሥልጠና እና ማማከር አገልግሎት Sebez Training and Consultancy services

الذهاب إلى القناة على Telegram

የአለም አቀፍ ( የአስመጪና ላኪነት) ንግድ Import Export 📝ሥልጠና 🖍Training 💼ማማከር 📒Consultancy 👷‍♀️ሙሉ ስራ 👷‍♂️Outsource ስለ ስልጠናችን ለማወቅ @sebeztrainingbot www.sebeztraining.com/courses www.sebeztraining.com

إظهار المزيد
2 630
المشتركون
+224 ساعات
+207 أيام
+9730 أيام
أرشيف المشاركات
በ2018 በጀት ዓመት 11 ወራት ከ3.1 ሚሊዮን በላይ የንግድ ፍቃድ ምዝገባ ፣እድሳት ፣ አዳዲስ ፍቃድ ማውጣት እና ልዩ ልዩ የፍቃድ ነክ አገልግሎቶች በኦንላይን አገልግሎት መስጠቱን ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በማበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆቹ አሳው ቋል፡፡

ከቱርክ ወደ ኢትዮጵያ በ9 ቀናት ብቻ! የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከቱርክ ወደቦች የሚነሱ ገቢ ጭነቶችን በቀጥታና በፍጥነት ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባበትን ታሪካዊ አዲስ አገልግሎት
ከቱርክ ወደ ኢትዮጵያ በ9 ቀናት ብቻ! የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከቱርክ ወደቦች የሚነሱ ገቢ ጭነቶችን በቀጥታና በፍጥነት ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባበትን ታሪካዊ አዲስ አገልግሎት ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ከ40 ቀናት በላይ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ አሁን ወደ 9 ቀናት ብቻ ዝቅ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፥ ይህም የአሠራር ማሻሻያዎችንና አዳዲስ የአጋርነት ስምምነቶችን በመተግበር የመጣ ትልቅ ስኬት ነው። ይህ አዲስ አቅጣጫ በተለይ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች የሚያስፈልጉ ጥሬ ዕቃዎችን በፍጥነትና በአስተማማኝ ሁኔታ ለማቅረብ ቁልፍ መፍትሔ ሆኗል። ባለፉት 3 ወራት ብቻ 150 ሙሉ ኮንቴይነር (FCL) ጭነቶችን በሁለት ዙር በተሳካ ሁኔታ ማጓጓዝ የተቻለ ሲሆን፥ አገልግሎቱ የትራንዚት ጊዜን በእጅጉ በመቀነስ የሀገሪቱን የንግድ ፍሰት ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ተወዳዳሪና ተደራሽ እያደረገው ይገኛል ተብሏል።

መንግስት የታክስ እፎይታን በማንሳት 78.9 ቢሊዮን ብር አዲስ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱ ተሰማ ​የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማ ባቀረበው የ2019 ረቂቅ በጀት ላይ እንዳመለከተው፥ ከቀረጥ ነፃ እና የግብር እፎይታ አሰራሮች ከመጪው በጀት ዓመት ጀምሮ ይቀራሉ። በዚህም ቀደም ሲል ከቀረጥ ነፃ ይገቡ የነበሩ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች፣ የህክምና እና የአካል ጉዳተኞች መርጃ መሣሪያዎች በቅናሽ ምጣኔ እንዲስተናገዱ ተደርጎ 22.5 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል። ​በተጨማሪም የገቢ ግብር እፎይታን በማንሳት ሌላ 22.5 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም አዲስ የኤክሳይዝ ታክስ የቴምብር ሥርዓት በመዘርጋት 33.8 ቢሊዮን ብር፤ በድምሩ 78.9 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ የሀገር ውስጥ ገቢ ለማግኘት ታቅዷል። በአጠቃላይ መንግስት ከተለያዩ የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ ከታክስ እና ታክስ ካልሆኑ ምንጮች በመጪው ዓመት 1.6 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዷል። ምንጭ: ሸገር ራዲዮ

ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ ቀጥተኛ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (በፍራን
ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ ቀጥተኛ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (በፍራንኮ-ቫሉታ) ነዳጅ እንዲያስገቡ የሚፈቅደውን አዲስ መመሪያ ተግባራዊ አድርጓል። በማዕከላዊ ገዢው እዮብ ተካልኝ ፊርማ ባለፈዉ ሳምንት የጸደቀው ይህ መመሪያ፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት በማቃለል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር ያለመ ሲሆን፤ የሚገባው ነዳጅ ለተቋማቱ የራስ አገልግሎት ብቻ እንዲውል፣ ለንግድ እንዳይቀርብ እና በዲጂታል ሥርዓት በጥብቅ እንዲከታተል ይደነግጋል። ባለፉት ዓመታት የነዳጅ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ በብቸኝነት የማስገባት መብት የነበረው የመንግሥት ይዞታ ለሆነው ለኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነበር። ይሁን እንጂ ነዳጅ የሀገሪቱ ትልቁ የገቢ ምርት መሆኑ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት መኖሩ አቅርቦቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ ቆይቷል።

የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ .pdf9.44 KB

የጉምሩክ አዋጁ ያሻሻላቸው ተጨማሪ ጉዳዮች ምንድናቸው? አስመጪዎችና ላኪዎች በባህር እንዲሁም በየብስ የሚያስገቧቸው ዕቃዎች በመጋዘን የሚቆዩበት ጊዜ ከ15 ወደ 45 ቀናት ፣ በአየር የሚገቡ ደግሞ ከ10 ወደ 30 ቀናት እንዲያድግ ተደርጓል።   በተጨማሪም አስመጪዎች በአንድ ዲክላራሲዮን ላስገቧቸው ዕቃዎች ሙሉ ቀረጥ በአንዴ ለመክፈል የገንዘብ እጥረት ካጋጠማቸው፣ ቀረጥ የከፈሉበትን የዕቃ መጠን ብቻ ለይተው በክፍልፋይ እንዲያወጡ የሚፈቅድ አዲስ አሰራር ተዘርግቷል። የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማገዝም፣ ሶፍትዌር ወደ አገር ሲገባ የሚታሰበው ቀረጥ በውስጡ ባለው መረጃ ዋጋ ላይ ሳይሆን፣ ሶፍትዌሩ በተጫነበት መሣሪያ (Carrier Medium) ዋጋ ላይ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል። የውጭ ምንዛሬ ተመን አወሳሰን ላይም የቀረጥ ስሌት የሚከናወነው ዲክላራሲዮኑ በጉምሩክ ተመዝግቦ ተቀባይነት ባገኘበት ቀን ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው ጠቋሚ (Indicative) የምንዛሬ ተመን መሠረት እንዲሆን ተደንግጓል። በገዥና በሻጭ መካከል ግንኙነት ባለበት ሁኔታ ደግሞ፣ አስመጪው ዝምድናው በዋጋው ላይ ተጽዕኖ አለማሳደሩን ማረጋገጥ ካልቻለ ጉምሩክ የቀረበውን ዋጋ ውድቅ የማድረግ ሥልጣን ተሰጥቶታል። ረቂቅ አዋጁ ኮንትሮባንድ ለመከላከል የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ ተብለው ተሻሽለው የተሠሩ ወይም ከፍተኛ መጠን ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች፣ የዕቃው ዋጋ ግምት ውስጥ ሳይገባ በቀጥታ እንዲወረሱ ይደረጋል። በኮንትሮባንድ ተግባር ላይ የተገኘ እንስሳ ባለቤት፣ የእንስሳውን ወቅታዊ የገበያ ዋጋ 100 በመቶ እኩል የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍል ተደንግጓል።   በተጨማሪም መረጃ ለሚሰጡ እና ለሚተባበሩ አካላት የገንዘብ ወሮታ እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ ከኮንትሮባንድ ዕቃ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም ለኮሚሽኑ አቅም ግንባታ እንዲውል ይደረጋል። ሌላው፣ አንድ አስመጪ በጉምሩክ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ካለው ይግባኝ ማለት የሚችለው፣ ክርክር የተነሳበትን ቀረጥና ታክስ 50 በመቶ አስቀድሞ መክፈሉ ሲረጋገጥ ብቻ ነው። በተጨማሪም አስመጪዎች ለጉምሩክ የሚሰጡት የዋጋ መረጃ እንደ ምስጢር ተጠብቆ እንዲቆይ ሕጋዊ ዋስትና ተሰጥቷል። መረጃው ሊገለጽ የሚችለው ለፍርድ ቤት ክርክር ሲፈለግ ብቻ ይሆናል።   Source ቲክቫህ ኢትዮጵያ

Repost from Addis Chamber
የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ .pdf9.44 KB

Repost from Addis Chamber
የጉምሩክ አዋጁ ያሻሻላቸው ተጨማሪ ጉዳዮች ምንድናቸው? አስመጪዎችና ላኪዎች በባህር እንዲሁም በየብስ የሚያስገቧቸው ዕቃዎች በመጋዘን የሚቆዩበት ጊዜ ከ15 ወደ 45 ቀናት ፣ በአየር የሚገቡ ደግሞ ከ10 ወደ 30 ቀናት እንዲያድግ ተደርጓል።   በተጨማሪም አስመጪዎች በአንድ ዲክላራሲዮን ላስገቧቸው ዕቃዎች ሙሉ ቀረጥ በአንዴ ለመክፈል የገንዘብ እጥረት ካጋጠማቸው፣ ቀረጥ የከፈሉበትን የዕቃ መጠን ብቻ ለይተው በክፍልፋይ እንዲያወጡ የሚፈቅድ አዲስ አሰራር ተዘርግቷል። የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማገዝም፣ ሶፍትዌር ወደ አገር ሲገባ የሚታሰበው ቀረጥ በውስጡ ባለው መረጃ ዋጋ ላይ ሳይሆን፣ ሶፍትዌሩ በተጫነበት መሣሪያ (Carrier Medium) ዋጋ ላይ ብቻ እንዲሆን ተወስኗል። የውጭ ምንዛሬ ተመን አወሳሰን ላይም የቀረጥ ስሌት የሚከናወነው ዲክላራሲዮኑ በጉምሩክ ተመዝግቦ ተቀባይነት ባገኘበት ቀን ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣው ጠቋሚ (Indicative) የምንዛሬ ተመን መሠረት እንዲሆን ተደንግጓል። በገዥና በሻጭ መካከል ግንኙነት ባለበት ሁኔታ ደግሞ፣ አስመጪው ዝምድናው በዋጋው ላይ ተጽዕኖ አለማሳደሩን ማረጋገጥ ካልቻለ ጉምሩክ የቀረበውን ዋጋ ውድቅ የማድረግ ሥልጣን ተሰጥቶታል። ረቂቅ አዋጁ ኮንትሮባንድ ለመከላከል የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ለመደበቅ ተብለው ተሻሽለው የተሠሩ ወይም ከፍተኛ መጠን ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሽከርካሪዎች፣ የዕቃው ዋጋ ግምት ውስጥ ሳይገባ በቀጥታ እንዲወረሱ ይደረጋል። በኮንትሮባንድ ተግባር ላይ የተገኘ እንስሳ ባለቤት፣ የእንስሳውን ወቅታዊ የገበያ ዋጋ 100 በመቶ እኩል የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍል ተደንግጓል።   በተጨማሪም መረጃ ለሚሰጡ እና ለሚተባበሩ አካላት የገንዘብ ወሮታ እንዲከፈል የተወሰነ ሲሆን፣ ከኮንትሮባንድ ዕቃ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም ለኮሚሽኑ አቅም ግንባታ እንዲውል ይደረጋል። ሌላው፣ አንድ አስመጪ በጉምሩክ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ካለው ይግባኝ ማለት የሚችለው፣ ክርክር የተነሳበትን ቀረጥና ታክስ 50 በመቶ አስቀድሞ መክፈሉ ሲረጋገጥ ብቻ ነው። በተጨማሪም አስመጪዎች ለጉምሩክ የሚሰጡት የዋጋ መረጃ እንደ ምስጢር ተጠብቆ እንዲቆይ ሕጋዊ ዋስትና ተሰጥቷል። መረጃው ሊገለጽ የሚችለው ለፍርድ ቤት ክርክር ሲፈለግ ብቻ ይሆናል።   ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የግብርና_ቢዝነስ_ኩባንያዎች_ረቂቅ_አዋጅ.pdf4.00 KB

የግብርና ቢዝነስ ኩባንያዎች ለሥራቸው የሚያስፈልጓቸውን የግብርና ግብዓቶች፣ መሣሪያዎችና፣ ተሽከርካሪዎችን ከውጭ "ከታክስ ነፃ" እንዲያስገቡ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የግብርና ዘርፍን ከተለምዶአዊ አሰራር ወደ ቢዝነስ መር ስርአት ለማሸጋገር ያግዛል ያለውን "የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያ አዋጅ" ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ይታወቃል። ይህ አዋጅ ኋላ ቀር የግብርና አሠራር ተወስነው የቆዩ አነስተኛ አርሶ አደሮችን፣ አርብቶ አደሮችንና ከፊል አርብቶ አደሮችን ወደ ዘመናዊና ተወዳዳሪ የንግድ ሥርዓት ለማሸጋገር ያለመ ነው። የዚህ ሪቂቅ አዋጅ ዋነኛ ትኩረት አነስተኛ ይዞታ ያላቸውን አምራቾች በ "ክላስተር" በማደራጀት ወደ ግብርና ቢዝነስ ኩባኒያነት መለወጥ ነው። አዲሱ ሕግ አርሶ አደሩ ያለውን መሬት የመጠቀም መብት፣ የእንስሳት ሀብትና ጉልበት ወደ ካፒታል በመለወጥ የኩባኒያ ባለቤትና ባለድርሻ እንዲሆን ዕድል ይከፍታል። ይህም አርሶ አደሩ በግል ከመልፋት ይልቅ በጋራ በመደራጀት በገበያ ላይ የመደራደር አቅሙን እንዲያሳድግ፣ ምርቱን እንዲያሰባስብና እሴት በመጨመር የተሻለ ዋጋ እንዲያገኝ እንደሚያስችለው አዋጁ ያስረዳል። በአዋጁ መሠረት አንድ የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያን ለመመስረት ዝቅተኛ የአባላት ቁጥር ተቀምጧል። በአዝርዕት ዘርፍ የተሰማሩ ከሆኑ ቢያንስ 300 አባላት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ወይም በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ከሆነ ደግሞ ቢያንስ 150 አባላት ሊኖሩት ይገባል። ኩባኒያዎቹ ሲመሰረቱ ዝቅተኛ የተከፈለ ዋና ካፒታላቸው ከ1.5 ሚሊዮን ብር ማነስ የለበትም። እያንዳንዱ አባል በኩባኒያው ውስጥ ሊኖረው የሚችለው የአንድ ድርሻ (Share) ዋጋም ከ1,000 ብር በታች እንዳይሆን ተደንግጓል። የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያዎቹ እንደ ማንኛውም ዘመናዊ የንግድ ተቋም በጠቅላላ ጉባኤ፣ በሥራ አመራር ቦርድ እና በዋና ሥራ አስኪያጅ የሚመሩ ይሆናሉ። ከዚህ በተጨማሪ ኩባኒያዎቹ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙና ሙያዊ ምክር የሚሰጡ፣ "የአማካሪ ቦርድ" እንዲኖራቸው አዋጁ ይፈቅዳል፣ የአማካሪ ቦርድ የስራ አባላት ዘመንም ሦስት አመት ነው። ይህም የኩባኒያዎቹ አመራር በሳይንሳዊና በዘመናዊ የቢዝነስ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ለማድረግ ነው። ይህንን ሽግግር ለማገዝም ልዩ ልዩ ማበረታቻዎችን ረቂቅ አዋጁ አካቷል። የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያዎቹ ለሥራቸው የሚያስፈልጉ የግብርና ግብዓቶችና ቴክኖሎጂዎችን፣ የእርሻ መሣሪያዎችንና ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም መለዋወጫዎችን ከውጭ ሲያስገቡ "ከታክስ ነፃ" የመሆን መብት ይኖራቸዋል። የግብርና ቢዝነስ ኩባኒያ አባላት ያመረቱተትን የግብርና ምርት ሲሽጡ ወይም ከኩባኒያው በሚያገኙት የትርፍ ክፍፍል ላይ የገቢ ግብር አይከፍሉም፡፡ ሆኖም ኩባንያው ከሚያገኘው ገቢ ላይ በገቢ ግብር አዋጁ መሰረት ግብር ይከፍላል፡፡ በተጨማሪም ኩባንያዎቹ ግብዓቶችን ለማስገባት ለሚያስፈልጋቸው የውጭ ምንዛሬ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ለሥራ አመራር ቦርድና ለአባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እንደሚመቻቹ እንደሚደረግ ረቂቅ መመሪያው ያሳያል። ግንቦት 18 በተካሄደው 55ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ፣ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቶታል።

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች። በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል። ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል። የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። ዝርዝሩን ከካፒታል ያንብቡ https://capitalethiopia.com/2026/05/31/ethiopia-approves-first-national-trade-policy-after-years-of-fragmentation/

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባለፉት 11 ወራት • አዲስ የንግድ ምዝገባ 217,114 ፣ • አዲስ የንግድ ሥራ ፈቃድ 407,047 ፣ • የንግድ ፈቃድ ዕድሳት 1,440,846 ፣ • የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ማሻሻያ 461,619 አገልግሎት መስጠቱን በማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆቹ አሳውቋል፡፡ ይህም ለንግዱ ማኅበረሰብ ምቹና ቀልጣፋ ምኅዳርን መፍጠር እንዳስቻለው እና የዕቅዱን 100 በመቶ ያሳካ መሆኑን ግልፃል፡፡ እናንተስ ምን ትላላችሁ በተለይ etrade.gov.et ስትጠቀሙ የገጠማችሁ የቴክኒክ ችግር ምን ይመስል ነበር ??

AMENDMENT TO FOREIGN EXCHANGE DIRECTIVE NO. FXD/01/2024 DIRECTIVE NO. FXD/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ እና የሠበዝ ቤተሰቦች እንኳን ለዒድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!! ኢድ ሙባረክ !!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ እና የሠበዝ ቤተሰቦች እንኳን ለዒድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!! ኢድ ሙባረክ !!

መግለጫ | ወደ ቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ የሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ (EXPORT) ፈቃድ በሁሉም ባንኮች እንዲሰጥ በተመለከተ የወጣ መግለጫ
መግለጫ | ወደ ቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ የሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ (EXPORT) ፈቃድ በሁሉም ባንኮች እንዲሰጥ በተመለከተ የወጣ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአስመጪና እና ላኪዎች ሰበር ሊባል የሚችል የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ማሻሻያ አድርጓል፡፡ ብሔራዊ ባንክ በዛሪው እለት ይፋ ባደረገው መመሪያ በ LC on Acceptance እና
+1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአስመጪና እና ላኪዎች ሰበር ሊባል የሚችል የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ማሻሻያ አድርጓል፡፡ ብሔራዊ ባንክ በዛሪው እለት ይፋ ባደረገው መመሪያ በ LC on Acceptance እና በ CAD on Acceptance ለሚደረጉ የአለም አቀፍ ግዢ ክፍያዎች በተመለከተ ቀደም ብሎ የወጣውን FXD/01/2024 መመሪያ ነው ማሻሻያ ያደረገው፡፡ በዚህም የውጭ ምንዛሬ ሒሳብ (FCY Account) እና የውጭ ምንዛሪ ማቆያ (Retention Account) ላላቸው ድርጅቶች 1.ባንኮች የብሔራዊ ባንክን ፍቃድ ሳይጠብቁ በተቀባይነት ላይ የተመሠረተ ወይም ቆይቶ የሚከፈል የአለም አቀፍ ንግድ መተማመኛ ሰነድ (LC on acceptance) እና የሰነድ መክፈያ (CAD on acceptance) ማጽደቅ ይችላሉ። 2.አስመጪዎች ከባንክ ቅድመ ፈቃድ ሳይጠብቁ በCAD አሠራር የዕቃ ጭነት ማዘዝ ይችላሉ ፡፡ ክፍያው ግን የሚፈጸመው ሰነዶች ባንክ ሲደርስ እና ሲረጋገጥ ይሆናል የLC ክፍያ በተመለከተ 1.የውጭ ምንዛሬ ሒሳብ (FCY Account) እና የውጭ ምንዛሪ ማቆያ (Retention Account) ላላቸው ድርጅቶች የአለም አቀፍ ንግድ መተማመኛ ሰነድ (LC ) ክፍያዎች በአመታዊ እንዲከፈሉ እና ክፍያው ተመጣጣኝ እንዲሁም በ LCው ቆይታ እንዲከፈል 2.ሆኖም ክፍያ ተፈጻሚ የሚሆነው ከአሁን በፊት ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን ከፍተኛ ገደብ ማለፍ የለበትም

ብሔራዊ ባንክ ነገ may 19 2016 ,የ$500 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያጫርት አሳውቌል
ብሔራዊ ባንክ ነገ may 19 2016 ,የ$500 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያጫርት አሳውቌል

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ ከ8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ ግንቦት 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የንግድና ቀጠናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ከወጪ ንግድ ከ8.7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን አስታውቋል። የንግድና ቀጠናዊ ትሥሥር ሚኒስትር አቶ ካሳሁን ጎፌ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አካዳሚ የሰልጣኞች ምረቃ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ የወጪ ንግድ ገቢ ካለፉት ዓመታት አንጻር መጨመሩን ተናግረዋል። ባለፉት 10 ወራት ከ8.7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ እስከ በጀቱ ዓመት መጨረሻ ከወጪ ንግድ 10 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት መሥራት እንደሚገባና ይህንንም ለማስቀጠል አጫጭር የክህሎት ስልጠናዎችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል። በአካዳሚው የሚሰጡ ስልጠናዎች ከፍላጎት አንጻር ገና ብዙ የሚቀራቸው መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ ተጨማሪ የስልጠና ሥርዓቶችን ማስፋፋት እንደሚገባም ገልጸዋል። የጥራት ማረጋገጫና የምርቶች ደረጃ ውሳኔ ለግብርና ምርቶች ተወዳዳሪነት መጨመር ወሳኝ መሆናቸውን አመላክተዋል። በተጨማሪም በ4.4 ቢሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ማዕከል በቀጣይ ሁለት ወራት ሲጠናቀቅ በርካታ ሥራዎች የሚሰሩበት መሆኑን አክለዋል። ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንድትሆን ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሚገባ የገለጹ ሲሆን፤ ከአካዳሚው ባሻገር በዘርፉ ለውጥ እንዲመጣ ሌሎች ተቋማትም በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። __ ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን