ar
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

قناة بسيطة

إظهار المزيد
1 145
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content
+2

ዕለተ ሀሙስ ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም ለኮሌጁ ጥበቃና ፅዳት ሰራተኞችና አሰልጣኞች  ISO  ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተጀመረ። በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር ፈፅሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። በመሆኑም የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ ኮሌጁ የትግበራውን ሂደት ዕውን ለማድረግ ያስችል ዘንድ ለኮሌጁ ጥበቃና ፅዳት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ላይ ያለመ ነው። የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ሚካኤል ጎአ  የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው የISO ትግበራን ዕውን ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀው  ኮሌጁ አንጋፍና ስመጥር ከመሆኑ አንፃር በትግበራው አማካኝነት ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት ዓለማ አቀፋዊ እውቅናን ለማግኘት የጥበቃና የፅዳት ሰራተኞች ሚና የጎላ መሆኑንና በዚህ ስልጠና በቂ ግንዛቤ በማግኘት ተቋማችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል ትግበራ በጋራ ዕውን እናድርግ በማለት መልእክታቸውን በማስተላለፍ  መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል።   ስልጠናው የሰጡት አሰልጣኞች አቶ ደሳለዉ ታደለና አቶ ብርሀኑ ዘገየ ሲሆኑ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚዘልቅ ይሆናል። ስልጠናዉ ትኩረት የሚያደርግባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦ - ISO ምንነት - ISO ትግበራ ጠቀሜታ - የISO መለኪያዎች (standard) ምንድናቸው - ISO የምንተገብርበት ምክንያት - የትግበራው ሂደት ምን ይመስላል - የትግበራው ጠቀሜታና በትምህርት ተቋማት የISO ትግበራ  በዝርዝር ተዳሷል።                                                   ኮሙኒኬሽን ቡድን

የፍቅር እስከ መቃብሩ ሀዲስ አለማየሁ፤ ፐሬዘዳንት ግርማ ወ/ጊዬርጊስ፤ ተስፋዬ ገሠሠ፤መንግስቱ ንዋይ፤ ስብሃት ገ/እግዚአብሄር ሌሎችም ከ 250,000 በላይ ተማሪዎችን ያፈራው ተፈሪ መኮንን በ 90 ዓመት ዕድሜው በ 4 መንግስት አልፎአል፡፡በእነዚህ ዘመናትም ብዙ የዕድገት ደረጃዎችን ማለፉን አስተውሏል፡፡ የኃላው ከሌለ የለም የፊቱ ነውና የት/ቤቶች አባት ተፈሪ መኮንን የወለዳቸውን ልጆች ብሎም ለቁም ነገር ያበቃቸውን እያሰበ የ 99ኛውን የልደት በዓል ሻማ ይለኩሳል፡፡የፍቅር እስከ መቃብሩ ሀዲስ አለማየሁ፤ ፐሬዘዳንት ግርማ ወ/ጊዬርጊስ፤ ተስፋዬ ገሠሠ፤መንግስቱ ንዋይ፤ ስብሃት ገ/እግዚአብሄር ሌሎችም ከ 250,000 በላይ ተማሪዎችን ያፈራው ተፈሪ መኮንን በ 90 ዓመት ዕድሜው በ 4 መንግስት አልፎአል፡፡በእነዚህ ዘመናትም ብዙ የዕድገት ደረጃዎችን ማለፉን አስተውሏል፡፡ የኃላው ከሌለ የለም የፊቱ ነውና የት/ቤቶች አባት ተፈሪ መኮንን የወለዳቸውን ልጆች ብሎም ለቁም ነገር ያበቃቸውን እያሰበ የ 99ኛውን የልደት በዓል ሻማ ይለኩሳል፡፡

photo content

የተፈሪ መኮንን ት/ቤት 99ኛ ዓመት ሚያዝያ 19/ከዕዝራ እጅጉ / ጣሊያን ሀገራችንን ከመውረሩ 16 ዓመት ቀደም ብሎ ነው ‹‹መማር አገር ይለውጣል›› የሚለውን መርህ ያነገቡ የጊዜው የሀገሪቱ መሪዎች አንድ ቁምነገር መስራት እንዳለባቸው አመኑ፡፡ አውሮዻ በጊዜው የዕውቀት ብርሃን የሚገኝበትን ስልት ለዜጎቿ ምቹ አድርጋ ነበርና ኢትዮዽያም ይህ ጠቃሚ የእድገት ስልት ለህዝቧ ለማድረስ የጓጓችበት ጊዜ ነበር፡፡ በጊዜው የዛሬ 99 ዓመት የሀገሪቱ አልጋ ወራሽ ልዑል ተፈሪ መኮንን ት/ቤት መጀመር እንዳለበት ከውሳኔ ላይ ደረሱ፤ አውሮዻ ያቀኑም ጊዜም ባዩት ነገር ተደንቀው እዚያው ሳሉ አንድ ሁነኛ መልዕክት ወደ አገር ቤት ላኩ፡፡የተማሪ ቤቱ ሥራ በፍጥነት እንዲፈጸም ትዕዛዝ አስተላልፈው ነበርና የወቅቱ የሥራ ኃላፊዎች ፊታውራሪ ገብረማርያም እና ግራዝማች ወልደ ዬሀንስ ወልደአብ በብርቱ ትጋት አሠርተው የት/ቤቱ መከፈት ዕውን እንዲሆን አደረጉ፡፡ የዛሬ 99 ዓመት ሚያዝያ 19,1917 በዕለተ ሰኞ በአገራችን በዕድሜ 2ተኛ የሆነው ተፈሪ መኮንን የአዳሪ ት/ቤት ተከፈተ፡፡ በጥር ወር ከአውሮዻ የተገዙት የትምህርት መሳሪያዎችም ወደ ት/ቤቱ መግባት ጀመሩ፡፡ በ53 አንቀጽ የተሰናዳው የተማሪ ቤቱ ደንብም በወጉ ተጽፎ ቀረበ፡፡ መጋቢት 23,1917 ዓ.ም ታትሞ የወጣው ብርሃንና ሰላም ጋዜጣም የት/ቤቱን ማስታወቂያ ለመጀመሪያ ጊዜ አወጣ፡፡ ዛሬ በዚህ ትውስታ መለስ ብዬ የት/ቤቱን 99ኛ ዓመት መሙላት አስመልክቼ ወጎችን ጣል ለማድረግ አስቤአለሁ፡፡ የህግ ምሁሩ አቶ ተሾመ ገ/ማሪያም ከቀድሞዎቹ ተፈሪ መኮንን ተማሪዎች አንዱ ናቸው፡፡ት/ቤታቸው ለህይወታቸው መሠረት የጣለላቸው በመሆኑ ሁልጊዜም ያመሰግኑታል፤፤ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ኢትዬዽያ ውስጥ ሲጀምር ከመጀመሪያዎቹ ምሩቅ ሆኑት አቶ ተሾመ በጃንሆይ ዘመን እስከ ሚኒስትር ማዕረግ የደረሱ ናቸው፡፡አሁን ደግሞ የራሳቸው የጥብቅና ቢሮ አላቸው ። አቶ ተሾመ ስለ ተፈሪ መኮንን ትዝታቸውን እንዲያወጉኝ ስጠይቃቸው እንዲህ አሉኝ‹‹ተፈሪ መኮንን በእኛ ዕድሜ ድንቅ ትምህርት ሰጥቶናል፡፡ለዚህ እንደ ባለውለታ መቆጠር ያለባቸው ካቶሊኮቹ ናቸው፡፡ተፈሪ መኮንን ት/ቤትን ልክ እንደወላጆቼ የምወደው ት/ቤት ነው፡፡ የማልረሳው የሂሳብ ትምህርታችንን ነው፡፡ አንድ በገጽ ብዛቱ ዳጎስ ያለ መጸሀፍ እንደነበር አልረሳውም፡፡ያኔ በሂሳብ ጎበዝ ተማሪዎች መኖራቸውም ትዝ ይለኛል፡፡››ሲሉ አቶ ተሸመ ተፈሪ መኮንን ት/ቤትን እንደ ትልቅ ባለውለታ ይቆጥሩታል፡፡ በ53 አንቀጽ የተዋቀረው የተፈሪ መኮንን የዛን ጊዜው የአስተማሪዎችና የተማሪዎች ደንብ ብዙ ዝርዝር ጉዳዬችን አካቷል፡፤ለዋቢነት እስቲ አንቀጽ 26 ምን እንደሚል እናስታውስ፡፡ ሃያ ስድስተኛ አንቀጽ ከተማሪዎቹ መካከል ሁከተኛና ከሰው ጋር የማይስማማ ተማሪ የተገኘ እንደሆነ አስተማሪዎቹ ሁለትና ሶስት ጊዜ እየመከሩና እየተቆጡ ያሳልፉታል፡፡ምክራቸውን የማይሰማ ከሆነ በት/ቤቱ ደንብ ይቀጡታል፡፡ነገር ግን ከቅጣቱ በኃላ ሁከተኛነቱን የማይተው የሆነ እንደሆነ ለዳይሬክተሩ በጽህፈት አስታውቀው ዳይሬክተሩ መርምሮ ያስወጣል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር ሀይማኖት ዓለሙ በህይወት በነበረበት ጊዜ እነዚህ የት/ቤት ደንቦች ለህይወቱ መሠረት እንደጣሉለት ተናግሮ ነበር፡፡ የትያትር ባለሙያው ሀይማኖት ከዚህ ጹሁፍ አቅራቢ ጋር ጭውውት ባደረገበት ጊዜ የነገረው ት/ቤቱ ሥነ-ሥርዓት በማስተማር ይታወቃል፡፡ እንዲህ ብሎ ነበር ሀይማኖት ‹‹ተፈሪ መኮንን ለእኔ ሥነ-ሥርዓት ምን እንደሆነ የቀሰምኩበት ነው፤ቅጣት አለ፤ መገረፍ አለ፤ የምንገረፈው ደግሞ እጃችንን ነው፡፡ዳይሬክተር ቢሮ ገብቶ ሁሉ መገረፍ አለ፤ከጥናት በኃላ ደግሞ አዳሪ ት/ቤት ስለሆነ እንተኛ ነበር፡፡ በጥቅል አነጋገር የአዳሪ ት/ቤት ዲሲፒሊንን ያስተምራል››በማለት ሀይማኖት ትዝታውን አውግቶኝ ነበር፡፡ የዛሬ 99 ዓመት ተፈሪ መኮንን ሲጀመር የተማሪዎቹ ቁጥር 30 ነበር፡፡ በተመላላሽነትም ደግሞ ቁጥራቸው ከ 50 አይበልጥም ፤ዛሬ እንጦጦ የቀለምና የቴክኒክ ከተባለ በኃላ የቀንና የማታ ተማሪዎቹ ከ 4800 በላይ ደርሰዋል፡፡ በ 95,000 ብር የሥራ ማስኬጃ የተጀመረው ተፈሪ መኮንን ዛሬ በ 16 ሚልዬን ብር ይንቀሳቀሳል፡፡ ሲጀመር 10 ብቻ የነበሩት መምህራን ዛሬ 250 ተጠግተዋል:: ት/ቤቱ ሲጀመር ዋና ሹሙ ክቡር ሐኪም ወርቅነህ እሸቴ ነበሩ፡፡የግዕዝና የአማርኛ መምህር መርስዔ ሀዘን ወ/ቂርቆስ፤ ሙዚቃ ነርሲስ ናልባንዲያን እንደነበሩ ታሪክ ላይ ሰፍሯል:: በዛን ጊዜ ልጁን ወደ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ማስገባት የሚፈልግ ሰው በመጀመሪያ ወደ ት/ቤቱ መጥቶ ስፍራ መኖር አለመኖሩን ይጠይቃል፡፡ፈቃድ መጠየቂያ ወረቀት ተቀብሎም ሙሉ ስሙን ስራውን መኖሪያውንና የልጁን ስም በመሙላት ያሰፍራል፡፡ በተጨማሪም በተፈሪ መኮንን ት/ቤት ነዋሪ ሆኖ ወይም እየተመላለሰ እንዲማር እፈልጋለሁ፤ሥፍራ ፈልጉልኝ ለልጄ የሚል ከሆነ ፊርማውን አድርጎ ለእንደራሴው ቅጹን ይልካል፡፡ አቶ ተሾመ የተፈሪ መኮንን ተማሪ የሆኑበትን አጋጣሚ ሲያስታውሱ፤-‹‹ተፈሪ መኮንን ስመዘገብ ሚያዝያ 1937 ነበር፡፡በጊዜው ለእኔ የሚሆን ቦታ አልተገኘም፡፡ጃንሆይ እኛን ውጪ ሀገር ለመስደድ ነበር ፍላጎታቸው፡፡በሌሎች ት/ቤቶች ቦታ ሲያፈላልጉ ፈጽሞ ሊገኝ አልቻለም፡፡ያኔ የምንኖረው ገነተ-ልዑል ውስጥ ነው፡፡ከዛ አንድ ቀን ጃንሆይ ወደ ት/ቤት ይወስዷችኃል ተብለን ሄድን፡፡ያን ጊዜ የት/ቤቱ ዳይሬክተር ስቴፋን ራይት የሚባል ነበር፤፤ ጃንሆይም እነዚህን ልጆች ውጪ ሀገር ልልካቸው ስለሆነ ለጊዜውም ቢሆን ቦታ ፈልግላቸው አሉት ፡፡ ዳይሬክተሩ ‹‹አልጋ የለኝም ››ሲላቸው እርሳቸው ቆመው አልጋ አስገዙልን ፤፤ በዚሁ የተፈሪ መኮንን ት/ቤት ተማሪ ለመሆን ቻልን፡፡የልጅነት ስሜታችንም ደስ የሚል ነበር››በማለት የህግ ምሁር አቶ ተሾመ ያስረዳሉ፡፡ ጊዜው 1934 ዓ.ም ነበር ኢትዬዽያም ከጣሊያን ወረራ ነጻ ሆና ሉአላዊነቷን ያረጋገጠችበት ዘመን ነበር፡፡ በመስከረም ወር በመጀመሪያዎቹ ቀኖች ት/ቤቱን የሚመራ ሚስተር ሲሃ ሄንሪ የተባለ አሜሪካዊ ዳይሬክተር ተሾመ፤፤ በወቅቱ የት/ቤቱ 17ኛ ዓመት ሲከበር 700 ተማሪዎችን ተቀብሎ ት/ቤቱ ያስተምር ነበር፡፡ የአስተማሪዎቹም ቁጥር 31 መድረሱን የያኔ ሰነዶች መስክረዋል፡፡ በ1934 ይሰጥ የነበረው የትምህርት ዓይነትም አማርኛ,፤ እንግሊዘኛ,፤ ሂሳብ,፤ ፈረንሳይኛ፤ የአረብኛ፤ መዝሙር ፤ስዕልና ጅምናስቲክ ነበሩ፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር ሀይማኖት በህይወት በነበረበት ሰዓት ከዚህ ጹሁፍ አቅራቢ ጋር ባደረገው የ1 ሰዓት ቆይታ ተፈሪ መኮንን ሁለገብነትን የሚስተምር ተማሪ ቤት ነው ሲል አጫውቶታል፤‹‹ለምሳሌ አናጢነት ትማራለህ፤ ይህንንም ትምህርት መሴ ሻርፓንት የሚባል ሰው ያስተምረን እንደነበር አልዘነጋውም፤፤ ቦይ ስካውት የጀመርነው ተፈሪ መኮንን ነው››ሲል ሀይማኖት ሀሳቡን አውግቶኝ ነበር፡፡ የተፈሪ መኮንን ት/ቤት የዛን ጊዜ አስተማሪዎች ከእሁድና ከትልቅ በዓላት በቀር ጧት በ 2 ሰዓት ገብተው በ 5 ሰዓት ይወጣሉ፡፡ በድጋሚ በ 7 ሰዓት ገብተው በ 11 ሰዓት ይወጣሉ፡፡ በጊዜው በት/ቤት የደንብ ቁጥር 23 ላይ እንደሰፈረው የትቤቱ መምህራን ዕረፍት የሚያደርጉበት ቀን በዝርዝር ተቀምጧል፡፡

photo content

photo content
+3

ዕለተ ሐሙስ ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም     የኮሌጁን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረገው                       የሌማት ትሩፋት። ያለ አቅምን አሟጦ በመጠቀም ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት ያለ ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም የከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የኮሌጁን ማህበረሰብ የሌማት ትሩፍት ተጠቃሚ ለማድረግ ብሎም የኮሌጁን የውስጥ ገቢ ማሳደግ የቀጣይ አቅጣጫ መሆኑ ተጠቁሟል።   በኮሌጁ የሚገኙ ማሽነሪዎችን እና አቅምን በማቀናጀት ለረጅም ዓመታት ያለስራ የተቀመጡ የዳቦ መጋገርያ ማሽኖችን አስጠግኖ ወደስራ በማስገባት በተመጣጣኝ ዋጋ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ዳቦ ማቅረብ ተችሏል። የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆኑ የዝግጅት ክፍላችን ካነጋገራቸዉ የኮሌጁ ሰራተኞች መካከል የሬጀስትራል ባለሙያ የሆኑት ወ/ሪት መስከረም መኮንን በአገልግሎቱ ደስተኛ እንደሆኑና ውጪ ካለው ዋጋ፣ መጠን እና ጥራት አንፃር የተሻለ ሆኖ እንዳገኙት ገልፀው ነገር ግን የአቅርቦት መጠኑ ዝቅተኛ በመሆኑ የፈለጉትን ያህል መግዛት እንዳልቻሉና ይህም ትኩረት ተሰጥቶ ቢሰራበት መልካም ነው ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል። ተጨማሪ አስተያየት ከሰጡን የኮሌጁ ማህበረሰብ መካከል በኮሌጁ ፍይናንስ ሰነድ ክፍል ባለሙያ ወ/ሮ ብርሀኔ ዘርይሁን መውጫም ሆነ መግቢያ ሰዓት ላይ ሰርቪስ እንዳያመልጣቸው ሲሉ ለልጆቻቸው ዳቦ መግዣ ግዜ አጥተው እንደነበርና ኮሌጁ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስላደረጋቸው ግዜያቸውን ሆነ ገንዘባቸውን መቆጠብ ያስቻለ የተሻለ ጥራት ያለው ትኩስ ዳቦ መግዛት እንደቻሉ ገልፀዋል። አክለውም የዳቦው መጠን ማለትም ግራሙ ላይ ማስተካከያ ቢደረግ መልካም ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።                                   ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+3

ዕለተ ረብዕ ሚያዝያ 16/2016 ዓ.ም    በሆቴልና ቱሪዝም የስልጠና ዘርፍ የቱር ጋይድ            ት/ት ክፍል ሠልጣኞች ጉብኝት አካሄዱ። ቱሪዝም  ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ በተለያዩ ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ይታወቃል። በማህበራዊ እና አካባቢያዊ ዕድገት ውስጥም አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥር ዘርፍ ነው። ለውጪ ሀገር እና ለሀገር ውስጥ  እንግዶች በሀገሪቱ  ስላለው የተፈጥሮና ሰውሰራሽ መስህቦችን በማስተዋወቁ ረገድ የቱርጋይድ ሚና የጎላ ነው ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ይህንን ወሳኝ ሚና በሚጫወተው በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የሚሰማራውን የሰው  ሀይል እውቀትና ክህሎት ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና በሆቴልና ቱሪዝም የስልጠና ዘርፍ ቱር ጋይድ ት/ክ የሚሰጥ ሲሆን በቀደሙት ግዚያት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ ታሪካዊና የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች ላይ በመሄድ በቲዎሪ የተማሩትን በተግባር ቦታው ላይ በመገኘት ልምምድ የሚያደርጉና በተግባር የተደገፈ ት/ት የሚወስዱ መሆኑ ይታወቃል። በዘንድሮው ዓመት  በአዲስ አበባና በዙሪያው ሰፊ የመስህብ ስራዎች የተሰሩ በመሆናቸው በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ በቱር ጋይድ ትምህርት ክፍል በደረጃ ሁለት እና በደረጃ ሶስት ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች ለሁለት ቀናት የዘለቀ ጉብኝት አደርገዋል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በመዲናችን አዲስ አበባ የሚገኙን የቱሪስት መዳረሻ ሰፍራዎችን በመጎብኘት በንድፈሀሳብ የተማሩትን ወደ ተግባር መለወጥ ላይ ያለመ ነው። በከተማችን የቱሪስት መዳረሻ ከሆኑት ስፍራዎች መካከል፦ - እንጦጦ ማርያም ሙዝየም - እንጦጦ ፖርክ - አንድነት ፖርክ - አድዋ ፖርክ - አዲስ አበባ ሙዝየምን  ያካተተ ጉብኝት በአሰልጣኞቻቸው በመታገዝ  አድርገዋል።                                    ኮምንኬሽን ቡድን

photo content

የተከበራችሁ አሰልጣኞች የእንጦጦ ፖሊ ቴኬኒክ የቋሚ ሠራተኛ መሆናችሁን በሚመለከተው ሃላፊ ብቻ የተፈረመ ደብዳቤ እን ቤት ያለው የሌለው የሚለውን ደግሞ በወረዳው ዋና ሥራ አስፈጻሚ የተፈረመ ደብዳቤ ብቻ ይዛችሁ ሂዱ። ይሄንን ካልያዛችሁ የክፍለከተማው ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ስለማያስተናግዳችሁ እንዳትለፉ። እነዚህን መረጃዎች እንድታሟሉ በማሰብ ምዝገባችሁ ዛሬን ጨምሮ እስከ አርብ ድረስ ሆኗል ።

photo content

ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም ከእቴጌ መነን የልጃገረዶች ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች ኮሌጁን ጎበኙ። እቴጌ መነን የልጃገረዶች ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ከ7-12ኛ ክፍል የተውጣጡ
+3
ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም ከእቴጌ መነን የልጃገረዶች ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች ኮሌጁን ጎበኙ። እቴጌ መነን የልጃገረዶች ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ከ7-12ኛ ክፍል የተውጣጡ 64  ተማሪዎች  በኮሌጁ የተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝት አካሂደዋል ። የጉብኝቱ ዓላማ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ  ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል አልሞ ነው።  በኮሌጁ ካሉ ስልጠና ዘርፎች ኤስቴቲክስ ፣ ቴክስታይል ጋርመንት ፣ ሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፎችን በአሰልጣኞች በመታገዝ ተዘዋውረው ጉብኘኘት አድርገዋል።                                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኞች ISO ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተጀመረ። በ"ISO 21001:2018 Educational quality managem
+3
ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኞች  ISO  ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተጀመረ። በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር ፈፅሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። በመሆኑም የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ ኮሌጁ የትግበራውን ሂደት ዕውን ለማድረግ ያስችል ዘንድ ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ላይ ያለመ ነው። የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው የISO ትግበራን ዕውን ለማድረግ በታስክ ፍርሱ አማካኝነት ወደ ስራ መገባቱን ገልፀው ኮሌጁ 100ኛ ዓመቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናን አግኝቶ ማክበር ያስችል ዘንድ ስለ ISO ምንነት ወጥነት ያለው የጋራ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ አመላክተዋል። አክለውም በዚህ ስልጠና በቂ ግንዛቤ በማግኘት ተቋማችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል ትግበራ በጋራ ዕውን እናድርግ በማለት መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል።   ስልጠናው ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚዘልቅ ሲሆን  ትኩረት የሚያደርግባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦ - ISO ምንነት - ISO ትግበራ ጠቀሜታ - የISO መለኪያዎች (standard) ምንድናቸው - ISO የምንተገብርበት ምክንያት - የትግበራው ሂደት ምን ይመስላል - የትግበራው ጠቀሜታና በትምህርት ተቋማት የISO ትግበራ  በዝርዝር ተዳሷል።                           ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+5

ዕለተ ሐሙስ ሚያዚያ 10/2016ዓ.ም ለእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠልጣኞች ስለ ሮተሪ ኢንተር ናሽናል ክለብ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ የግንዛቤ መፍጠሪያ ፕሮግራሙ መልካም ስምና ዝና ባላቸው የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ማህበር አባላት የተዘጋጀ ነው፡፡ የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የሮተሪ ኢንተርናሽናል ክለብ ትብብር ሁለቱ የ99 ዓመት አዛውንቶች ጉድኝት በሚል በ2015ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን የዚህ ቀጣይ ክፍል የሆነው በዛሬው ዕለት ለተማሪዎች የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩን ያዘጋጁት ከማህበሩ አባላት መካከል የቀድሞ የሮተሪ ኢንተርናሽናል ዲስትሪክት 9212 መሪ በድርጅቱ ታሪክ የመጀመሪያ ሴት መሪ /ገዢ /ሆነው ያገለገሉት ወ/ሮ አዜብ አስራት፣ አርቲስት ልኡል ሰገድ ረታ እና ሮትሪክተር ሚኪያስ መንገሻ ሲሆኑ እነዚህ አባላት በክለቡ የተለያ ደረጃ ተሰይመው የነጻ አገልግሎት እየሰጡ ከመሆናቸው ባሻገር አገልግሎቱን ለማስፋት የዳበረ የስራ ልምዳቸውን ጨምረው ለሠልጣኞች አጋርተዋል ፡፡ በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም የክለቡ አመሰራረትና ስያሜ የተገኘበት መንገድ ማህበሩን የመሰረቱት አራት አባላት ውይይታቸውን በዙር ከማድረጋቸው ጋር የሚያያዝ ስለመሆኑ ከአዘጋጆቹ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ክለቡ የተመሰረተበት ዋና ዓላማም ዓለማቀፍ ግኑኝነትን በማዳበር የሰው ልጆች ህይወትን የተሻለ ለማድረግና የተሻለ ዓለም በመፍጠር ለሰላም የሚደረገውን ጥረት መደገፍ እንዲሁም የፖሊዮ በሽታን ማጥፋት የሚል ስለመሆኑ ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡ የአባልነት መስፈርቱም ዓላማውን ተረድቶ ለማስፈፀም ቁርጠኛ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለያየ የእድሜ ክልል የሚገኙ የተለያየ የአባልነት ደረጃ እና ዓይነት እንደሚኖራቸው ተነግሯል፡፡ ለምሳሌ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እድሜ ክልል ያሉ Interact/መስተጋብር ፣በዩኑቨርስቲ ትምህርት እድሜ ክልል ያሉ Rotary act እና ከዩኑቨርስቲ አድሜ ክልል በላይ ያሉ ደግሞ Rotary እንደሚባሉ ተጠቅሷል፡፡ ከአባልነት የሚገኘው ጥቅምም በመስጠት ውስጥ እራስን ማሳደግ፣ከሰዎች ጋር መግባባት እውቅና ማግኘት፣ሃሳብን በሰዎች ፊት መግለጽ፣ፈጠራ የታከለበት የስልጠና እድል ማግኘት ወ.ዘ.ተ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ፕሮግራሙን አስመልክቶ በአዘጋጆቹ በሚገባ ከተገለፀ በኋላ ግንዛቤውን የበለጠ ለማዳበር በጥያቄና መልስ የታገዘ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በመጨረሻም ሠልጣኞች ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው በአባልነት በመመዝገብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማድረግ መልሰው እራሳቸውን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ የሚችሉበት ሁኔታ /አቅጣጫ የተመቻቸላቸው ስለመሆኑ ከፕሮግራሙ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ኮሙኒኬሽን ቡድን