1 145
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
1 145
+2
ዕለተ ሀሙስ ሚያዝያ 10/2016 ዓ.ም
ለእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የISO ትግበራ ሂደት ሪፖርት ቀረበ።
ኮሌጁ በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር ፈፅሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። በመሆኑም በትግበራው ሂደት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ሪፖርት(progress report) ለማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ቀርቧል። ሪፖርቱ በአቶ ሚካኤል ጎአ የቀረበ ሲሆን ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦
- የትግበራው የድርጊት መርሀ-ግብር ምን
እንደሚመስል
- ትግበራው እየተፈፀመባቸው ያሉ የስራ
ክፍሎች
- የመጀመሪያ ደረጃ የISO ትግበራ ዕቅድ
አፈፃፀም
- በትግበራው የተቋሙን የስራ ቅደም ተከተል
የመለየትና የማስቀመጥ ስራ እየተከወነ
መሆኑን
- ትግበራው ያለበት ደረጃ
- የታዩ ጠንካራ ጎኖች
- ያጋጠሙ ችግሮች
- ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ
- የትግበራው መዋቅር እና የሰው ሀይል
አደረጃጀት እንዲሁም የስራ ሂደቱ ምን
እንደሚመስል የታየበት ሲሆን ትግበራውን
ተቋማዊና ሁሉን አካታች ለማድረግ በቀጣይ
መከናወን ስላለባቸው ተግባራት ምክክር
ተካሂዷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+5
ዕለተ ሀሙስ ሚያዝያ 10/2016 ዓ.ም
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሠልጣኞች
ጉብኝት አደረጉ።
የኮሌጁ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና የክፍል አስተባባሪዎች በኢትዮጵያ በዓይነቱ የተለየ ነው በተባለው በሳይንስ ሙዝየም ጉብኝት አደረጉ።
ሙዚየሙ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣አርተፊሻል ኢንተለጀንስን (ሰው ሰራሽ ልህቀት) በግንባር ቀደምትነት የሚቀመጥ ሲሆን በውስጡ የተለያዩ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶች ለእይታ ቀርበውበታል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማ አሠልጣኞች በፍጥነት እያደገ ካለው ቴክኖሎጂ ጋር አብሮ ለመሄድ ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳደግና የቀደመውን፣ የአሁኑንና የወደፊት ሁኔታን በሳይንሳዊ ጥበብ በማጣመር የፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ስራዎችን ለመስራት ማስቻል ላይ ያለመ ነዉ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 8/2016 ዓ.ም
ለተመራቂ ሠልጣኞች ሲሰጥ የነበረዉ ሁለተኛ ዙር ሶፍት እስኪልና ዲጂታላይዜሽን ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኪፕለር ኢትዮጵያ በተሰኘ ተቋም አማካኝነት ከ60 በላይ ለሚሆኑ በተለያየ የስልጠና ዘርፍ የሰለጠኑ ተመራቂ ሠልጣኞች ለአንድ ወር ሲሰጥ የቆየው soft skill, professional job application document preparation, communication, professional skill, digital skill ስልጠና የመዝጊያ ስነ- ስርዓት ተከናወነ፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኪፕለር ኢትዮጵያ አካዳሚክ ፕሮግራም ማኔጀር ወ/ሮ ፍሬሂወት የማነህ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው የስልጠናው ሂደትና ቆይታቸው ሲከታተሉ እንደነበር ገልጸው ይህ የመጀመሪያው ሂደት እንደሆነና በቀጣይ በዋናነት ተከታታይነት የለዉ የተጠናከረ ስራዎችን በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
በተያያዘም በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴኪኒክ ኮሌጅ በኪፕለር ኢትዮጵያ ሠልጥነው በሰለጠኑበት ሞያ ወደ ስራ ዓለም የተቀላቀሉት ረድኤት እና መታሰቢያ የራሳቸዉን ስራ ለመስራትና ስራ በማፈላለጉ ሂደት እንዴት ዉጤታማ እንደሆኑና በስራ ቦታ ላይ ያላቸውን ገጠመኝ እንዲሁም የገጠማቸውን ተግዳሮት እንዴት እንደተሻገሩት ለአዲሶቹ ሠልጠኞች አጋርተዋቸዋል፡፡
በተመሳሳይ የማዘር ላንድ ፍርማኩሌቲክስ ማርኬቲንግ ማኔጀር አቶ ዬናታን ሳሙኤል ሠልጣኞች ወደ ስራ ዓለም ሲቀላቀሉ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ተግዳሮቶችን እና በስራው ዓለም ሊላበሷቸው ስለሚገባ ባህርያት ካላቸው ሰፊ የስራ ልምድ በመነሳት ገለጻ አድርገዋል፡፡
ተጨማሪም የኮሌጁ አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ዬናስ ሀይለየሱስ ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ንቁ ተሳትፎ እንደነበራቸው ገልፀው ስልጠናው በባህሪው ልምምድን የሚጠይቅ በመሆኑ በየግዜዉ ልምምድ ማድረግና በህይወት ዘመናቸው ሁሉ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አመላክተዋል።
የስልጠናው ተሳታፊ የነበሩት ተማሪ አባይነህ እና ተማሪ ቃልኪዳን ለስልጠናው መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው ዘመኑን የሚመጥን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ስራቸውን መስራት እንደሚችሉ እና በራስ የመተማመን መንፈሳቸው የጎለበተ ስልጠና እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም ስልጠናቸውን በአግባቡ ላጠናቀቁ ሠልጣኞች የኮሌጁ ICT ስልጠና ዘርፍ ተጠሪና የኪፕለር ኢትዮጵያ አካዳሚክ ፕሮግራም ማኔጀር አማካኝነት ሰርተፍኬት የመስጠት መርሀ-ግብር ተከናውኗል፡፡
ኮሙኒኬሽን ክፍል
1 145
+4
ሰኞ ሚያዚያ 7/2016ዓ.ም
የ2016ዓ.ም 3ተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን
ሪፖርት ቀረበ።
በዕቅድ የተመራ ስራ መከናወኑ ለውጤታማነት ወሳኝ ሚና የሚጫወት በመሆኑ በዚህ መሰረት ለኮሌጁ ማህበረሰብ የ3ተኛ ሩብ ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ቀረበ።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ
ግብ ተኮር ተግባራት፣ ከዕቅድ ውጪ የተከናወኑ ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተቀመጡ የመፍትሄ ሀሳቦችናንና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ከዕቅድ ክንውኑ አኳያ የተሻለ አፈፃፅም ያላቸው ተግባራት እንዳሉና ከዚህም ባሻገር ወደ ኋላ የቀረንባቸው ስራዎች ላይ ትኩረት አድርገን መስራት እንደሚጠበቅብን ገልፀዋል።
በተያያዘም በከሌጁ ም/ዲኖች የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል፦
- በቀጣይ ለተመራቂ ሰልጣኞች መከወን ያለባቸው
ተግባራት
- ከአሰልጣኝ ምዘና ጋር በተያያዘ መከናወን ስላለባቸው
ተግባራት
- ከክበባት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ
- ከክህሎት ውድድር ጋር በተያያዘ
- የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ዝግጅትን አስመልክቶ የተለያዩ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን ከዚህም ባሻገር ለሰራተኛ ማህበሩ የቁጥጥር ኮሚቴ የ3 አባላት ምረጫ ተካሂዷል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዋና ዲን በቀጣይ ስለሚከናወኑ ተግባራት አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን ከተቀመጡት የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል ተቋማዊ ሪፎርም ከመፍጠር አንፃር መከናወን ስላለባቸው ተግባራትና ከ100ኛ ዓመት አከባበር የማስጀመርያ መርሀ-ግብር ጋር በተያያዘ ሁሉም የነቃ ተሳትፎ እዲያደርግ ጥሪያቸውን በማስተላለፍ መርሃ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+9
ዕለተ ቅዳሜ ሚያዝያ 5/2016ዓ.ም
በተለያዩ የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድር ተካሄደ።
ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር መሆኑ ይታወሳል። ለ14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የተለያየ ዝግጅት እየተከናወነ ሲሆን ከነዚህ ዝግጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የክህሎት ውድድር ነው በትላንትናው ዕለት በሠልጣኞች እና በአንቀሳቃሾች በተለያዩ የሙያ መስኮች ተካሂዷል በተመሳሳይ በዛሬው ዕለትም በአሠልጣኞች መካከል ውድድሩ ተካሂዷል። የዚህ ውድድር ዋና ዓላማ የስልጠና ጥራትን ማሻሻል፣ አሠልጣኙና ሠልጣኙ ያሉበትን የክህሎት ደረጃ ለመለየትና ለማገዝ እንዲያስችል እንዲሁም ተነሳሽነትን በመፍጠር ስራ ፈጣሪነትና ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ላይ ያለመ ነው።
በዚህ ውድድር የመወዳደርያ መስፈርቱን ያሟሉ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና አንቀሳቃሾች በተለያየ የሙያ መስክ ለሁለት ቀናት የዘለቀ ውድድር በዛሬው እለት ተጠናቋል።
የዝግጅት ክፍላችንም ለተወዳዳሪዎች መልካም
ዕድልን ይመኛል!!
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ሰላም የኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ 👋
👉 ዘንድሮ የሚከበረው 14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ከእግር ኳስ እና ከመረብ ኳስ ውድድር በተጨማሪ ሌሎች የስፖርት ውድድሮችን የሚያካትት እንደሚሆን የአዲስ አበባ የስራ እና ክህሎት ቢሮ አሳውቆናል። በመሆኑም ቀጥሎ በተዘረዘሩት የውድድር አይነቶች መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም የኮሌጁ ሰራተኛ የውድድሩ አስተባባሪዎችጋ እንዲመዘገብ እያሳወቅን የውድድር ተሳታፊዎችን ዝርዝር ለኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ክፍል እንድታሳውቁ መልዕታችን ነው።
1) የእግር ኳስ ውድድር (በአሰልጣኝ እና በሰልጣኝ)
2) የመረብ ኳስ ውድድር (በወንድ እና በሴት)
3) የሩጫ ውድድር (በወንድ እና በሴት)
4) በቴኒስ ውድድር
🙏🙏🙏🙏🙏መልካም ቀን🙏🙏🙏🙏🙏
1 145
+9
ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 1/2016ዓ.ም
ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በኮሌጁ ግምገማ አካሄዱ።
የግምገማው ዓላማ በኮሌጁ የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ በማካሄድ ድጋፍ የሚሹ ዝርዝር ጉዳዮችን በመለየት አወንታዊ ጥምረቶችንና መልካም ተሞክሮዎችን መለየትና መቀመር እንዲሁም ጉድለቶችን ለይቶ በማረም በየደረጃው የሚገኙ ማነቆዎችን በመፍታት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠርና በቀጣይ የተቀናጀ ንቅናቄ በመፍጠር የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ ነው።
በግምገማው ከተዳሰሱት መካከል
- ከISO ትግበራ ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ ስላሉ
ተግባራት
- በኮሌጁ የሚሰሩ የቴክኖሎጂ ስራዎች
- የተቋም ምዘና አፈፃፀም
- ኢንተርፕራይዞችን ከመፍጠር አንፃር እየተከናወኑ
ያሉ ተግባራት
- ከውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ስልጠና ጋር በተያያዘ
የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን የኮሌጁ ዋና ዲን
አቶ ተሾመ ፈይሳ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በቂ
ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከዚህም ባሻገር ከሚኒስቴር
መስሪያ ቤቱ ድጋፍ የሚሹ ተግባራትን በዝርዝር
አስቀምጠዋል።
ቡድኑ በቀጣይ ኮሌጁ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራባቸው ይገባል ያሏቸውን ተግባራት አመላክተዋል። በመጨረሻም በኮሌጁ ዋና ዲን አማካኝነት በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ ተመራቂ ሰልጣኞች የተሰሩ የስዕልና ቅርፃቅርፅ ስራዎች፣ በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት የማሰልጠኛ ክፍሎች እንዲሁም ለኢንተርፕራይዝ የተሰጠ የዶሮ እርባታ ስፍራን ምልከታ በማድረግ የጉብኝት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ብድን
1 145
+5
ዕለተ ሰኞ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም
የኢድ አል-ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ
የማጋራት መርሀ-ግብር ተካሄደ።
ኮሌጁ የበጎ አድራጎት ማዕድ ማጋራት መርሀ ግብርን በተለያዪ ጊዚያት ተግባራዊ እያደረገ የመጣ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በዛሬው ዕለትም አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ የእስልምና እምነት ተከታይ የኮሌጁ ሠራተኞች የኢድ አል-ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ከቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት ጋር በመተባበር የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሂዷል ። በፕሮግራሙ ላይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በበዓል ወቅት የመተሳሰብና ተካፍሎ መብላትን እንዲሁም የአብሮነት ባህልን የሚያዳብር መሆኑን በመግለፅ ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች ኢድ ሙባረክ በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ኮሙኒኬሽን ብድን
1 145
+4
ዕለተ ረብዕ መጋቢት 25/2016 ዓ.ም
የISO 21001:2018 ሰነድ ዝግጅት ሂደት ሪፖርት ቀረበ።
ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘትና ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል ትግበራ መጀመሩ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በISO ትግበራ ቡድን (ታስክ ፎርስ) አባላት የሰነድ ዝግጅት ስራውን አስመልክቶ እየተከናወኑ ሰላሉ ተግባራት ለማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የቀረበ ሲሆን ሪፖርቱን ያቀረቡት በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ አሸናፊ በቀለ በሰነድ ዝግጅት ወቅት የተከናወኑ ተግባራት፣ የሚጠበቁ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፣ በትግበራ ቡድኑ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትና ከማኔጅመንቱ የሚጠበቁ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የኢኒስቲትዩቱን ከፍተኛ ባለሙያዎችና ታክስ ፎርስ አባላትን አመስግነው ከISO ትግበራ ጋር በተያያዘ ከሰነድ ዝግጅት ባሻገር በቀጣይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባና በታቀደው ግዜ ትግበራውን ዕውን ለማድረግ የኮሌጁን ማህበረሰብ ርብርብ እንደሚሻ ገልፀው ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ዕለተ ረብዕ መጋቢት 25/2016 ዓ.ም
የ3ተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን ግምገማ ተካሄደ።
በ2016 ዓ.ም የተግባር ምዕራፍ ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ በመሪ ዕቅዱ መሰረት ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል። በእቅድ የተመራ ስራ መከናወኑ ለውጤታማነት ወሳኝ ሚና የሚጫወት በመሆኑ በዚህ መሰረት ለኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ቢሾፍቱ በሚገኘው የስራ አመራር ኢንስቲቱዩት የ3ተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ቀረበ።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ወ/ሪት ፀዳለ አድማሱ በኮሌጁ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት፣የመልካም አስተዳደር ተግዳሮቶች እና የተቀመጡ የመፍትሄ ሀሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ከ3ተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን አኳያ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ግቦች እንዳሉ ገልፀው በቀሩት ግዜያት ከተቀመጡ ዕቅዶች ባሻገር እንደ ኮሌጅ ተቋማዊ ሪፎርም ለመፍጠር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን መደገፍ እንዲሁም ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘትና ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል ትግበራ እየተከናወነ መሆኑንና ከ100ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ስራዎች ፍሬ የሚያፈሩና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ እንዲሆን እያንዳዱ የኮሌጁ ማህበረሰብ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ እንደሚገባው አመላክተዋል።
በተያያዘም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሃሳብ አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል፦
- ተቋማዊ ሪፎርም ከመፍጠር አንፃር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ምንነት
- ስልጠና ዘርፎች እንዲሁም ዳሬክቶሬቶች የገጠማቸው ተግዳሮቶችና መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን የኮሌጁ ዋና ዲንና ም/ዲኖች ለተነሱ ሀሳብ አስተያቶች ምላሽ ሰጥተዋል። አክለውም በቀጣይ ስለሚከናወኑ ተግባራት አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ከተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል፦
- ዕንደ እቅድ የተያዙና ጅምር ስራዎችን ከግብ ማድረስ
- የቴክኖሎጂ ስራዎችን በትኩረት መስራት
- አሰልጣኞችን ከማብቃትና ከማስመዘን ጋር በተያያዘ መከናወን ስላለባቸው ተግባራት
- ለኢንስፔክሽን ባለሙያዎች የተሟላ መረጃ መስጠት ላይ በትኩረት ለመስራት አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ክፍል
1 145
+6
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም
የቧንቧ መስመር ዝርጋታና ጥገና ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ከኮሌጁ ከGIZ ጋር በመተባበር ለሁለት ወራት የቆየ የቧንቧ መስመር ዝርጋታና ጥገና ስልጠና በኮንስትራክሽን የስልጠና ዘርፍ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።
በመሆኑም ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ 25ሰልጣኞች የማጠቃለያ መርሀ-ግብር የተካሄደ ሲሆን በመርሀ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ለተመራቂ ሰልጣኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተለላልፈው የፕሮጀክቱ ዓላማ በክህሎት የዳበረ ትውልድን በማፍራት ዳቦ ከመብላት ባሻገር ለታናናሾቻቸው ሙያን የሚያስተምሩና አርአያ መሆን የሚችሉ ብቁ ዜጋን ማፍራት መሆኑን ገልፀዋል።
በተያያዘም የGIZ ተወካይ አቶ ቻላቸው ለስልጠናው መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው የወሰዱት ስለጠና ተመራጭ የሙያ ዘርፍ ስለመሆኑ ቀደም ተብሎ ጥናት የተሰራበት መሆኑን ገልፀው ሰፊ የስራ ዕድል ያለው የሙያ መስክ በመሆኑ በየክፍለ ከተማቸው ተደራጅተው ወደ ስራ መግባት አልያም ፍላጎት ያላቸው ስራ ቀጣሪ ድርጅቶችን በማነጋገር የስራ ዕድል እንደሚመቻችላቸው ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዋና ዲንና የGIZ ተወካዮች ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት በማበርከት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
