1 145
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
1 145
ዕለተ ረቡዕ ሚያዝያ 30/2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ጠልሰም ሠዓሊ ሔኖክ መልካምዘር የህይወትና የስራ ልምዳቸውን ለስነ-ጥበብ ት/ክፍል ሰልጣኞች አካፈሉ።
የእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥነ-ጥበብ ትምህርት ክፍል ማስተማር ከተጀመረበት ጊዜ ማለትም 1999 ዓ.ም አንስቶ ከመደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት ባሻገር በሥነ-ጥበብ ዘርፉ አንጋፋ ባለሙያዎችን በመጋበዝ የሕይወትና የሥራ ልምዳቸውን ለሰልጣኞች እንዲያካፍሉ በማድረግ መዝለቁ ይታወሳል። በመሆኑም የዚህ ወር እንግዳ የሆኑት በኢትዮጽያ የጠልሰም ሥዕል ጥበብ አንጋፋ የሆኑት ሠዓሊ ሔኖክ መልካምዘር ናቸው።
በመረሀ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስነ-ጥበብ ስልጠና ዘርፍ መምህር ሀይሉ ክፍሌ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በኢትዮጵያ የጠልሰም ሥዕል ጥበብ አንጋፋ የሆኑት ሠዓሊ ሔኖክ መልካምዘር ለሰልጣኞች የህይወትና የስራ ልምዳቸውን ሊያካፍሉ በመምጣታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ለፕሮግራሙ መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በተያያዘም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ለኮሌጁ 99ኛ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በኢትዮጵያ የጠልሰም ሥዕል ጥበብ አንጋፋ የሆኑት ሠዓሊ ሔኖክ መልካም ዘር የተደረገላቸውን ጥሪ አክብረው በምጣታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም ከዚህ ቀደም የነበ ሩ የስነ-ጥበብ ስልጠና ዘርፍ ሰልጣኞች ከኮሌጁ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ዘመን ተሻጋሪ ሰራዎቻቸውን ለተመልካች የሚቀርቡበትን መንገድ እንደያመቻቹ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በኢትዮጽያ የጠልሰም ሥዕል ጥበብ አንጋፋ የሆኑት ሠዓሊ ሔኖክ መልካምዘር የኮሌጁ ዲኖች፣ ተጋባዥ እንግዶችና ሰልጣኞች በተገኙበት ተወልደው ካደጉበት አዲስ አበባ ልዩ ስሙ ጃን ሜዳ ፣ አስተዳደጋቸውን እና ከልጅነታቸው ጀምሮ ክረምት ላይ ትምህርት ሲዘጋ የቅኔ መምህር የነበሩት አያታቸው ጋር ጎጃም ክፍለ ሀገር እንደሚሄዱና በእርሳቸው አማካኝነት ከስድስተኛ ክፍል ጀምረው የጠልሰም ትምህርት እንደ ጀመሩ እንዲሁም ለ18 ዓመታት ያለማቋረጥ እንደ ተማሩ ገለፀዋል። የመጀመሪያ የጠልሰም ስራቸውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኤግዚቢሽን ማዕከል በ1984 ዓ.ም እንዳቀረቡና ከዘህም ባሻገር በተለያዩ ዓለማት የስዕል ስራዎታቸውን እንዳቀረቡና አሁንም በዶ/ር ኤልሳቤት ወ/ጊዮርጊስ አማካኝነት በሻርጃህ አርት ፋውንዴሽንና ሙዝዬም 120 የስዕል ሥራዎቹ እየቀረቡ እንደሆነ እንዲሁም የተለያዩ ወርክሾፖችን እንደተካፈሉ አመላክተዋል። በተያያዘም ስለ ጠልሰም ምንነት፣ ጠልሰም ለመስራት የሚያስፈልጉ ነገሮች፣ ስለ ጠልሰም አይነቶች ሰፊ ማብራራያ ሰጥተዋል በተያያዘም ከታዳሚዎች ለተነሱላቸው ሃሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎች እንደየ አጠያየቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል።
በመቀጠል በሻርጃህ አርት ፋውንዴሽንና ሙዝዬም የስዕል ስራዎችን ለማቅረብ በር ከፋች የሆነውን በዶ/ር ኤልሳቤት ወ/ጊዮርጊስ የተዘጋጀ የስድስት ደቂቃ ቪዲዮ ለታዳሚ የቀረበ ሲሆን በተያያዘም የበገና መምህር በሆኑት ኤርሚያስ አማረ ስለ በገና ምንነትና አደራደር አጭር ገለፃ በመስጠት ዝማሬ ቀርቧል።
በመጨረሻም በት/ክፍሉ የተዘጋጀውን እና የተሳታፊዎች ፊርማ ያረፈበት ማስታወሻ በሰዓሊያን ማህበር ፕሬዝደንት ሰዓሊ አክሊሉ አማካኝነት በስጦታ መልክ ተበርክቶላቸዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+5
ዕለተ ሀሙስ መጋቢት 24/2016 ዓ.ም
የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ
የማጋራት መርሀ-ግብር ተካሄደ።
ኮሌጁ የበጎ አድራጎት ማዕድ ማጋራት መርሀ ግብርን በተለያዪ ጊዚያት ተግባራዊ እያደረገ የመጣ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በዛሬው ዕለትም አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ የኮሌጁ ሠራተኞች እና በአካባቢው ነዋሪ የሆኑ አቅመደካሞችን በማካተት የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት አማካኝነት የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ ላይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በበዓል ወቅት የመተሳሰብና ተካፍሎ መብላትን እንዲሁም የአብሮነት ባህልን የሚያዳብር መሆኑን በመግለፅ ይህንን መርሀ-ግብር ላዘጋጁ የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ህብረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የትንሳኤ በዓል በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
በተያያዘም የቀድሞ ተማሪ የነበሩ አቶ ፍቅረማርያም ፀሀይ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በውጭ ሀገር ሆነ ሀገር ውስጥ ያሉ የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ይህንን ማዕድ የማጋራት መርሀ-ግብር እንዳዘጋጁ ገልፀው መልካም የፍሲካ በዓል በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ኮሙኒኬሽን ብድን
1 145
+1
የትንሳኤ በዓል ተስፋን፣ ይቅርታ ማድረግንና ሁለተኛ እድል መስጠትን በማሰብ የምናከብረው በዓል በመሆኑ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዬች እንኳን ለብርሃነ ትንሳዔ በሰላም አደረሳችሁ አደረሳችሁ!
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
የእንጦጦ : ፓሊ : ኮሌጅ : ሥነ - ጥበብ : ትምህርት : ክፍል : ማስተማር : ከጀመረበት : ጊዜ : ( 1999 ዓ.ም. ) አንስቶ : ከመደበኛው : የመማር : ማስተማር : ሂደት : በተጓዳኝ : በሥነ - ጥበብ : ዘርፉ : አንጋፋ : ባለሙያዎችን : በመጋበዝ : የሕይወትና : የሥራ : ልምዳቸውን : ይካፈላል ፤ እነሆ : የዚህ : ወር : እንግዳችን ...
በኢትዮጽያ : የጠልሰም : ሥዕል : ጥበብ : አንጋፋው : ሠዓሊ : ሔኖክ : መልካምዘር : ይሁን ፣ ሥራዎቹን : በኢትዮጵያ : በተደጋጋሚ : ጊዜ ፣ በተለያዩ : ዓለማትም : የሥዕል : ትርዒቱን : ያቀረበና ፣ የተለያዩ : ወርክሾፓችን : የተካፈለ : ሲሆን ፤ የፊታችን : ረቡዕ : ሚያዝያ : 30, 2016 ዓ.ም. ከ 8: 00 ሰዓት : ጀምሮ : የሕይወት : ልምዱን : እና : አጠቃላይ : ስለ : ጠልሰም : ጥበብ : ምንነት ፣ ፍልስፍናና : አሰራር ፤ እንዲሁም : ስለ፡ ትምህርት ፡ ሥርዓታችን : የምንወያይ : ሲሆን ፤.. በተጨማሪም : በቅርቡ : በሻርጃህ : አርት : ፋውንዴሽንና : ሙዝዬም : ( SHARJAH ART FOUNDATION, MUSEUM ) የተከፈተውና : እየታየ : ባለው : ሥራዎቹና ፡ ሁነቱ : ዙሪያ : ውይይት : እናደርጋለን ፠
በቦታው : በመገኘት : መታደም : ትችላላችሁ ፠የእንጦጦ : ፓሊ : ኮሌጅ : ሥነ - ጥበብ : ትምህርት : ክፍል : ማስተማር : ከጀመረበት : ጊዜ : 1999 ዓ.ም. አንስቶ : ከመደበኛው : የመማር : ማስተማር : ሂደት : በተጓዳኝ : በሥነ - ጥበብ : ዘርፉ : አንጋፋ : ባለሙያዎችን : በመጋበዝ : የሕይወትና : የሥራ : ልምዳቸውን : ይካፈላል ፤ እነሆ : የዚህ : ወር : እንግዳችን ...
በኢትዮጽያ : የጠልሰም : ሥዕል : ጥበብ : አንጋፋው : ሠዓሊ : ሔኖክ : መልካምዘር : ይሁን ፣ ሥራዎቹን : በኢትዮጵያ : በተደጋጋሚ : ጊዜ ፣ በተለያዩ : ዓለማትም : የሥዕል : ትርዒቱን : ያቀረበና ፣ የተለያዩ : ወርክሾፓችን : የተካፈለ : ሲሆን ፤ የፊታችን : ረቡዕ : ሚያዝያ : 30, 2016 ዓ.ም. ከ 8: 00 ሰዓት : ጀምሮ : የሕይወት : ልምዱን : እና : አጠቃላይ : ስለ : ጠልሰም : ጥበብ : ምንነት ፣ ፍልስፍናና : አሰራር ፤ እንዲሁም : ስለ፡ ትምህርት ፡ ሥርዓታችን : የምንወያይ : ሲሆን ፤.. በተጨማሪም : በቅርቡ : በሻርጃህ : አርት : ፋውንዴሽንና : ሙዝዬም : ( SHARJAH ART FOUNDATION, MUSEUM ) የተከፈተውና : እየታየ : ባለው : ሥራዎቹና ፡ ሁነቱ : ዙሪያ : ውይይት : እናደርጋለን ፠
በቦታው : በመገኘት : መታደም : ትችላላችሁ ፠
1 145
+3
ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እንዲሁም ፅዳትና ጥበቃ
ሠራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናው ከትናንት የቀጠለ እና በጥቅም ግጭት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን በሥነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳሬክቶሬት አማካኝነት የተዘጋጀ ነው።
የስልጠናው ዓላማ በተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉ የጥቅም ግጭቶችን ለመከላከልና ለማስተዳደር የሚያስችል ግንዛቤ በመፍጠር አሰራርን በመርህ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረግ ላይ ያለመ ነው።
ስልጠናውን የሰጡት ከአዲስ የአበባ ሥነ-ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ዳሬክቶሬት አቶ ደረጀ ግርማ ሲሆኑ ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦
- የጥቅም ግጭት መሰረታዊ ሀሳቦች
- የጥቅም ግጭት ለመከላል ህጋዊ መነሻዎች
- የጥቅም ግጭት ሊፈጥሩ የሚችሉ ተጋላጭ መስኮች
- የጥቅም ግጭት መንስኤዎች
- የጥቅም ግጭት መከላከያና ማስተዳደርያ መንገዶች
- የጥቅም ግጭት መከላከል ላይ የተለያዩ አካላት ሚና በዝርዝር ተዳሰዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+2
ዕለተ ማክሰኞ ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ ማኔጅመንና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት
ስልጠና ተሰጠ።
እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር አይሶን ለመተግበር ባደረገው ስምምነት መሠረት በታስክ ፎርሱ /የሥራ ግብረ ኃይሉ አማካኝነት ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል፤ ትግበራውን በተጠናከረ ሁኔታ ለማስኬድ ይረዳ ዘንድ በዛሬዉ ዕለት ለኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ስልጠና ተሰጥቷል።
የዚህ ስልጠናው ዓላማ የሥራ ግብረሀይሉ አባለት ግንዛቤን በማዳበር ለአይሶ ትግበራው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዳያበረክቱ በማስቻል ዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ላይ ያለመ ነው።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+2
ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ አሰልጣኞች ISO ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር ፈፅሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።
በመሆኑም የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ ኮሌጁ የትግበራውን ሂደት ዕውን ለማድረግ ያስችል ዘንድ ለኮሌጁ አሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠት ላይ ያለመ ሲሆን ስልጠናዉ ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦
- ISO ምንነት
- ISO ትግበራ ጠቀሜታ
- የISO መለኪያዎች (standard) ምንድናቸው
- ISO የምንተገብርበት ምክንያት
- የትግበራው ሂደት ምን ይመስላል
- የትግበራው ጠቀሜታና በትምህርት ተቋማት የISO ትግበራ በዝርዝር ተዳሷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+4
ዕለተ ሰኞ ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እንዲሁም ፅዳትና ጥበቃ በሥነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ተሰጠ።
የስልጠናውን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳሬክቶሬት አዘጋጅነት መልካም አርአያነት ያለው ብልሹ አሰራርን የሚጠየፍ የተሻለ ተቋማዊ አፈፃፀም የሚያመጣ ማህበረሰብን ለመገንባት በኮሚሽኑ አማካኝነት ተከታታይነት ያለው ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዉ የተሻለ ተቋምን ለመገንባት የመልካም አስተዳደር ግንዛቤን ይዘን የጥቅም ግጭትን ለማስወገድ ያስችል ዘንድ ስልጠናውን በአግባብ መከታተል እንደሚገባ በማመላከት መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል።
ስልጠናዉ በሥነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳሬክቶሬት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን የስልጠናው ዓላማ መልካም ሥነ-ምግባር ለመልካም አስተዳደር ግንባታ ያለውን ፍይዳና አስፈላጊነት በሚመለከት መሰረታዊ እዉቀትንና ክህሎቶችን ማስጨበጥ እና በኮሌጅ ውስጥ ሥነ-ምግባራዊ አገልግሎት እንዲሁም መልካም አስተዳደርን ማጎልበት ላይ ያለመ ነዉ።
ስልጠናውን የሰጡት ከአዲስ የአበባ ሥነ-ምግባርና ፀረ- ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ዳሬክቶሬት አቶ ደረጀ ግርማ ሲሆኑ ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዬች፦
- የመልካም አስተዳደር መሰረታዊ መርሆች
- የመልካም አስተዳደር አስፈላጊነት
- የመልካም አስተዳደር ተግዳሮቶች
- ሥነ-ምግባርና መልካም አስተዳደር
- ሥነ-ምግባርዊ ፈታኝ ሁኔታዎች እና መልካም አስተዳደር በዝርዝር ተዳሰዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
የተፈሪ መኮንን ት/ቤት 99ኛ ዓመት ልደት በዓል
የዛሬ 99 ዓመት ሚያዝያ 19,1917 በዕለተ ሰኞ በ10 ሰዓት በአገራችን በዕድሜ 2ተኛ የሆነው ተፈሪ መኮንን የአዳሪ ት/ቤት በልዑል አልጋወራሽ ተፈሪ መኮንን ተመርቆ ተከፈተ፡፡ መጀመሪያ የተመዘገቡት 32 አዳሪዎችና 40 ያህል ተመላላሾች ነበሩ። እስካሁንም የተማሪዎች ቁጥር በየቀኑ እያደገ የሚሄድ ሲሆን በእነዚህ ዘመናትም ብዙ የዕድገት ደረጃዎችን ማለፉን የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ ፡፡ ከዚህም ባሻገር በዕድሜ አንጋፋ፣ በተሞክሮ የዳበረ፣ በአሠራር የደረጀው የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዛሬም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልጣኞችን በዕውቀት እና በሙያ እያበቃ ለሃገር በማበርከት 99ኛውን የልደት በዓል ያከብራል።
የ,ኋላው ከሌለ የለም የፊቱ ነውና የተማሪ ቤቱ መስራች ተፈሪ መኮንን የወለዷቸውን ልጆች ብሎም ት/ቤቱ ያፈራቸው አንጋፍ የቀድሞ ተማሪዎችን እያሰበ ሲያከብር የመከበሩ ስኬት የተቋሙ ብቻ ሳይሆን የሀገር ብሎም የቀድሞ ተማሪዎችና ቦርድ አባላት እንዲሁም በኮሌጁ ውስጥ በሰራተኝነት አልፈው የነበሩና እያገለገሉ ያሉ በሙሉ በመሆኑ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+3
ዕለተ ዓርብ ሚያዝያ 18/2016ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኰሌጅ የክዋኔ ኦዲት ተደረገ።
የክዋኔ ኦዲቱ ከፌደራል ስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች መሠራቱ የታወቀ ሲሆን ዓላማውም የኮሌጁን የአሰራር ስርዓቶችና ትግበራዎች በመፈተሽ በትክክለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ከማረጋገጥ ባሻገር መታረም ወይም መስተካከል ያለባቸወን ተግባራት መጠቆም ነው።
በክዋኔ ኦዲቱ ከተዳሰሱት ተግባራት መካከል፦
-በአጠቃላይ ድጋፍና ክትትል ለሚሹ ክፍሎችና አካላት መደረጉንና የዕቅድ ክንውን አፈፃፀሙን
- በፌደራልና አዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና አስፈፃሚዎች መካከል የግንኙነት ስርዓት መዘርጋቱን
- መደበኛ ስልጠና አጠናቃቂዎች በራሳቸው ስራ እንዲፈጥሩ የማድረግ በመሆኑ ዕቅዱንና የአፈፃፀሙን ትክክለኝነት ማረጋገጥ
- በአጫጭር ስልጠና ብቁ የሆኑ ሰልጣኞች ከስራ ጋር እንዲተሳሰሩ የማድረግ እንቅስቃሴ ዕቅዱንና የአፈፃፀሙን ትክክለኝነት ማረጋገጥ የሚሉትን ያካተተ ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ የክዋኔ ኦዲት ባለሙያዎቹ በኮሌጅ ውስጥ ያሉ የተለያዩ የስልጠና ዘርፎችን ተዘዋውረው በስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች አማካኝነት የክዋኔ ኦዲት አድርገዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+2
ዕለተ ዓርብ ሚያዝያ 18/2016ዓ.ም
በስነ-ምግባርና መልካም አስተዳደር ርዕስ ስር
የጥቅም ግጭትን መከላከልና ማስተዳደር ላይ
ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ።
የስልጠናው ዓላማ በተቋም ውስጥ የሚስተዋሉ የጥቅም ግጭቶችን ለመከላከልና ለማስተዳደር የሚያስችል ግንዛቤ በመፍጠር አሰራርን በመርህ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረግ ላይ ያለመ ነዉ።
ይህ ስልጠና ለሁለት ቀናት የዘለቀ ሲሆን በስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳሬክቶሬት አማካኝነት የተዘጋጀ ነው።
ስልጠናዉ ለኮሌጁ አመራሮች፣ ዳሬክቶሬቶች፣ ቡድን መሪዎች፣ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና ወርክሾፕ ቴክኒሻኖች እንደተሰጠ ተረጋግጧል።
ስልጠናውን የሰጡት በስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮምሽን አስቸኳይ ሙስና መከላከል ዳይሬክቶሬት አቶ ደምስ ረጋሳ ሲሆኑ ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦
- ሰነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር
- የመልካም አስተዳደር አስፈላጊነት
- የጥቅም ግጭት ምንነት
- የጥቅም ግጭት አይነት
- የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር ስልቶች
በዝርዝር ተዳሰዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳብ አስተያቶች በአሰልጣኙ ምላሽ በመስጠት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
