ar
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

قناة بسيطة

إظهار المزيد
1 148
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content

ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአራዳ ክ/ከ ስራና ክህሎት ለመጡ በተለያዩ ሙያ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች አቀባበል አደረገ ፡፡ 🇪🇹ህዳር 16/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአራዳ ክ/ከ ጋር በመተባበር 502 ዜጎች በከተማ ግብር ፣ በብረታ ብረትና እንጨት ሰራ ፣ በጋርመንትና ሌዘር እና በንግድ ሰራ ዘርፍ አጫጭር ስልጠና ለመስጠት አቀባበል አደረገ ። የኮሌጁ አካዳሚክ ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፋ ሲሆን ሰልጣኞ የኮሌጅን የሰልጣኞች ሰነምግባር እንዲያከብሩ መልክት አስተላልፈዋል ።የአራዳ ክፍለ ከተማ የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሶፎንያስ ቦጋለ አንጋፋው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ብዙ ምሁራንን ያፈራ ኮሌጅ መሆኑኑ ገልፀው ሰልጣኞች በዚህ ኮሌጅ የሰጣቸውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንደሚኖርባቸው የገለፁ ሲሆን ለኮሌጅ አመራሮች እና በቅበላው ላይ ለተሳተፋ የስራ ዘርፎችን አመስግነዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሠልጣኞች የጥያቄና መልስ ውድድር ተከናወነ፡፡ 🇪🇹ህዳር 16/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በማስመልከት በሰልጣኞች መካከል በተደረገው የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ስልጠና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ 22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ትውልድን በሥነ ምግባር ማነፅ ተቋምን በአሰራር መገንባት እንዲሁም ሙስናና ብልሹ አሰራርን የሚፀየፍ ትውልድ ማፍራት የኮሌጁ አንዱ ተልዕኮ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የኮሌጁ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክተር አቶ መከታው ሹመት በጥያቄና መልስ ውድድሩ ላይ የልዩ ፍላጎት ሰልጣኞች በምልክት ቋንቋ አስተርጓሚዎች በመታገዝ የውድድሩ ድምቀት መሆናቸውን ገልጸው በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 3ኛ የወጡ ሰልጣኞች በነገው ዕለት በኮሌጁ በሚያደርገው የማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ የተዘጋጀላቸውን ሽልማት እንደሚወስዱ ገልፀዋል፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+9

photo content
+1

photo content

ብቃት ዛሬን ለነገ!

photo content

የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን ይቀላቀሉ! 👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https:
+1
የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን ይቀላቀሉ!
👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https://t.me/AABOLS

"ትውልድን በስነ ምግባር፤ተቋምን በአሰራር!" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ፡፡ 🇪🇹ህዳር 15/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶርት "ትውልድን በሥነ ምግባር ፤ተቋምን በአሰራር!"በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ21ኛ ጊዜ እየተከበረ ያለውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን አስመልክቶ ከየዲፓርትመንቱ ለተውጣጡ ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸው ሊያከብሯቸው እና ሊያጎለብቷቸው የሥነ ምግባር መርሆዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል፡፡ የኮሌጁ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክተር አቶ መከታው ሹመት የስልጠናው ዋና አላማ ሰልጣኞች በኮሌጁ በሚቆዩበት የስልጠና ጊዜ ውስጥ ሠልጣኞች የተሻለ ሥነ ምግባር እንዲያዳብሩ የኮሌጁን ህግና ደንብ በማክበር መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡ እና ስልጠናቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ ማስቻል ነው፡፡ አያይዘውም ሰልጣኞች እርስ በእርሳቸው እንዲሁም ከአሰልጣኞችና ከአስተዳደር ሠራተኞች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በመልካም ሥነ ምግባር እሴቶች ላይ የተመሰረተ ለማድረግና በሁሉም የተቀናጀ ሥራ ለመስራት ይረዳል ብለዋል፡፡በመጨረሻም የኮሌጁ አካዳሚክ ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ አዲስ ሰልጣኞች ወቅቱ የሰጣቸውን እድል በመጠቀም የላቀ አፈፃፀም እንዲኖራቸው የራሳቸው ተነሳሽነት እና ጥረት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አስገንዝበዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹ህዳር 15/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለአስራ አምስተኛ ሳምንት ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት ቴክስታይል ጋ/ሌ/ስ/ዘርፍ አቶ ንጉሤ ግርማ '' እንዴት ምርታማ መሆን እንችላለን '' በሚል መሪ ቃል ለኮሌጅ ማህበረሰብ የጊዜ አያያዝ እና ምርታማነት ለሁሉም ሰው በተፈጥሮ አይመጣም ይልቁንስ የስራ ጫናዎን ለመቆጣጠር የስራ ዝርዝርዎን ለማሻሻል እና ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን ለመከላከል በህይወታችን ላይ በጣም ብዙ ነገር ሊኖረን ስለሚችል ሁሉንም ነገር ማከናወን የማይቻል ሆኖ ይሰማናል ። የዓለቶች፣ ጠጠሮች እና የአሸዋ ተመሳሳይነት በትልልቅ እና በትናንሽ ስራዎች መካከል ያለውን ልዩነት በማብራራት እና ቀናትዎን የማቀድን ዋጋ በተሻለ ለመረዳት የሚያስችል ታዋቂ መንገድ ነው። በህይወታችን ላይ ያለውን ሁሉንም ነገር በዓይነ ሕሊና በመመልከት, የስራ ቀናችን ከፍ ለማድረግ ውጤታማ ስራዎችን እንዴት ቅድሚያ መስጠት እንደምንችል ለመማር ያስችላል በማለት ትናንሽ የሆኑትን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይችላሉ ፤ ስራዎችን ማጠናቀቅ ጥሩ ስሜት ይፈጥራል ይህንንም ሲሻገሩ የስኬት ስሜት ይሰጥዎታል በማለት ተሞክሮአቸውን አካፍለዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

ባሳለፍነው ሳምንት

+2

ባሳለፍነው ሳምንት