ar
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

الذهاب إلى القناة على Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Public Service University

تُعد قناة Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 734 مشتركاً، محتلاً المرتبة 15 729 في فئة التعليم والمرتبة 2 648 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 734 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.81‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.95‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 434 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

12 734
المشتركون
+124 ساعات
+187 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+9

photo content

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ --------------------------- በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም እየተሰጠ ባለዉ የ12ኛ ክፍል ሀገርአቀፍ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ (orientation) ሐምሌ 08ቀን2016 ዓ.ም የተሰጠ ሲሆን በዛሬው ዕለት 09/11/2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ቀን ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ። በማስጀመሪያው ዕለት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እና የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት አጠቃላይ የፈተናውን ሂደት በተመለከተ ጉብኝት አድርገዋል። የኢሲሰዮ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለሚኒስትሩ አጠቃላይ ሂደቱን በተመለከተ ገለፃ ያደረጉላቸዉ ሲሆን የመጀመሪያ ዙር የማህበረሰብ ሳይንስ ተፈታኞች ያለምንም እንከን ፈተናቸዉን እንዳጠናቀቁ በመግለጽ የሁለተኛ ዙር የፈተና ሂደት በጥሩ ሁኔታ አየተካሄደ መሆኑን እና ለፈተናው አስፈላጊ ግብአት መሟላቱን ጠቁመው፣ በበይነ መረብ አማካኝነት ፈተናውን ለሚወስዱ ተማሪዎችም በቂ ኮምፒዩተሮች እና ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት እንዳለ ገልፀውላቸዋል።በማጠቃለያም ላይ ክቡር ሚኒስትሩ አረንጓዴ አሻራቸዉን በዩኒቨርስዉ ዋና ግቢ ችግኝ በመትከል አኑረዋል፡፡ በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 9 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

photo content
+7

የጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተጠናቀቀ ፡፡ -------------------------------- በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከሐምሌ 3/11/2016 - 5/11/2016 ዓ.ም ድረስ ሲሰጥ የቆየው የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ያለምንም እንከን ሙሉ በሙሉ ሠላማዊ በሆነ መንገድ ተጠናቋል ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ባስተላለፉት መልዕክት የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ በሰላም የተጠናቀቀ መሆኑን በመጥቀስ ፈተናዉ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የዩንቨርሲቲዉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የፈተና አስፈፃሚ ግብረ-ሀይል አባላት፣ የጣቢያ ኃላፊዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ ፈታኞች፣ የፀጥታ አካላት፣ በተመሳሳይ ለሌሎች አገልግሎት ሰጪ አካላት ምስጋና አቅረበዋል፡፡ ይህን ሀላፊነታችዉንም በተቀናጀ መልኩ በቀጣይ ጊዜ ለሚሰጠዉ የተፈጥሮ ሳይንስ ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ፍፁም ሰላማዊና ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቀ የየራሳቸዉን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ በፈተና ማጠቃለያዉም ተፈታኝ ተማሪዎች፣ፈታኞች፣የጸጥታ አካላት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲዉ የፈተና ግብረ ሀይል ዩኒቨርስቲዉ ባዘጋጀዉየ2016 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በመሳተፍ አሻራቸዉን አስቀምጠዋል፡፡

photo content
+5

ኢሲሰዩ በተለያዩ የትምህርት መርሀ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2216 ተማሪዎችን አስመረቀ ------------------------------------------ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በተለያዩ መርሀ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2216 ተማሪዎችን ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋና ጊቢ በድምቀት አስመረቀ፡፡ ተመራቂዎቹም 122 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 2119 በሁለተኛ ዲግሪ እና 27 ደግሞ በፒኤች ዲ ደረጃ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው፡፡ የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር ተመስገን ቡርቃ የዴሞክራሲ ማዕከል ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ምስረታ፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ጉዞና ከፌዴራሊዝም ስርዓት አጀማመር ጋር ጠንካራ ቁርጠኝት ያለው መሆኑን፣ ዩኒቨርሲቲው ከምስረታው ጀምሮ ባለው ጉዞው ከሰባ ሺህ በላይ ምሩቃንን በማፍራት እና ምሩቃኑም በከፍተኛ የመንግስት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተሰማርተው መንግስትና ሕዝብ የሰጣቸውን ኃላፊነቶች እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አስከትለውም የሲቪል ሰርቪሱ ያሉበትን መሰረታዊ ስብራቶች ለመጠገንና ዘመናዊ፣ ነጻና ገለልተኛ ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መንግስት የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ ማድረግ የጀመረ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ተመስገን ቡርቃ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ሰርቪሱን አቅም የመገንባት ተልዕኮ የተሰጠው ተቋም እንደመሆኑ መጠን፣ ይህን ተልዕኮውን ለመወጣት በትጋት እየሰራ ያለ ስለሆነ፣ ተቋማዊና አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያስፈልገው መሆኑን በማመንና፣ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ዕቅድን መሰረት ያደረገ የሽግግር ሥራዎችን እያሰራ እንደሚገኝ አመልክተው፣ የስራ አመራር ቦርዶም ይህ ጉዞ እንዲሳካ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ ለዕለቱ ተመራቂዎችም ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው ቆይታ ያካበቱትን ዕውቀትና ክህሎት በሚሰማሩበት የስራ መስክ ሀገሪቷንና ኅብረተሰቡን በታማኝነትና በታታሪነት፣ ከአድልኦና ከሙስና በጸዳ፣ ሰብዐዊነትን በተላበሰ መልኩ ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት፣ የመልካም አስተዳደር ችግር እንዲቃለል የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ በብርቱ ጥረትና ትጋት በየትምህርት ፕሮግራሞቹ የተቀመጡትን መስፈርቶች በሚገባ በማጠናቀቅ ህልማችሁን ዕውን ለማድረግ በመቻላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ በማስከተልም፣ ዩኒቨርሲቲው በእስካሁኑ ጉዞው ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ከዲፕሎማ እስከ ፒኤች ዲ ዲግሪ ድረስ አስተምሮ ማስመረቅ የቻለ መሆኑንና ከእነዚህም መካከል 700 የሚሆኑት የጎረቤት ሀገራት ፐብሊክ ሰርቫንቶች መሆናቸውን ገልጸው፣ ይህም ለሀገራችን ኩራት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ሚኒስቴር ስር እንዲደራጅ በመንግስት በመወሰኑ እና በሀገራችን ካሉት የመጀመሪያ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በድህረ ምረቃና ምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ምድብ መመደብ መቻሉ፣ የሀገራችንን ሲቪል ሰርቪስ አቅምና ብቃት የመገንባት ተልዕኮውን ለመወጣት ጠንካራ መንፈስና ተነሳሽነት የፈጠረለት መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰር ፍቅሬ በ2016 ዓ.ም ከመንግስት በተመደበው 837 ሚሊዮን ብርና ከባለድርሻ አካላት በተገኘ ድጋፍ በርካታ የትምህርት፣ የምርምርና ማማከር እንዲሁም የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች የተከናወኑ እና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችም ለመንግስት ሰራተኞች የተሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከጊዜ ወደ ጊዜ ተወዳዳሪነቱና ተመራጭነቱ እያደገ በመምጣቱም በ2016 ዓ.ም 7268 ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን፣ ለ2017 የትምህርት ዘመን ወደ 7000 የሚጠጉ የማስተርስና የፒኤችዲ ተወዳዳሪዎችን በመለየት ብሔራዊ የድህረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና እንዲወስዱ ዝርዝራቸው ለትምህርት ሚኒስቴር መላኩን አመልክተዋል፡፡ ፕሮፌሰር ፍቅሬ በንግግራቸው ዩኒቨርሲቲው ብቁና በቂ የአካዳሚክ ሰራተኞች እንዲኖሩት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን አብራርተው 31 አዳዲስ የትምርት ፕሮግራሞችም ቀረጻ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ የፐብሊክ ሴክተሩን አቅም ከመገንባት አኳያም በ2016 ዓ.ም ከ3206 በላይ ስልጠናና የምዘና ስራ መከናወኑንም አክለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት ሶስት አሰርት ዓመታት የሀገራችንን ሲቪል ሰርቪስ የሰው ኃይል በማልማትና በመንግስት የተዘረጉ የሪፎርም ፕሮግራሞችን ትግበራ በማማከር፣ ሴክተሩ ለሀገር ግንባታ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ፕሮፌሰር ፍቅሬ ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በምርምር ሥራዎች ላይ በሚያደርገው ትኩረት በማሳደግ በ2016 ዓ.ም በ5 ሚሊዮን ብር በጀት 49 ምርምሮችን ያካሄደ ሲሆን፣ ባለፉት አምስት ተከታታይ አመታት በአጠቃላይ 497 ችግር ፈቺና ለፖሊሲ ግብዐት የሚሆኑ ምርምሮች መሰራታቸውንም ፕሮፌሰር ፍቅሬ ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የተሟላ ራስ ገዥ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን በመንግስት በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ከ2016 በጀት ዓመት ጀምሮ በሶስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ የሽግግር ዕቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የገለጹት ፕሮፌሰር ፍቅሬ፣ ትምህርትና ስኬት የህይወት ዘመን ጉዞ አካል ቀጣይ በመሆናቸው፣ በቀጣዩ የሥራ ዓለም ተመራቂዎች የበለጠ አቅማቸውን በመገንባት ሀገራችንን ከድህነት ለማውጣት የሚደረገውን ጥረት በሙሉ ኃየላቸው መደገፍ እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

ከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር የተመራ ከፍተኛ ኃላፊዎች ቡድን በኢሲሰዩ ጉብኝት አደረገ -------------- የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ቡድን ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችና ከከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ክብርት ሚኒስትሯ በዩኒቨርሲቲው ባደረጉት ጉብኝት ወቅት በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይም በዩኒቨርሲቲውና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መካከል ያለውን ነባር ትብብር የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በውይይቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ብቸኛ የአቅም መገንቢያ ተቋም መሆኑን በማስታወስ በርካታ ሥራዎችን ያከናወነ እና ተልዕኮውምን በብቃት ሲወጣ የቆየ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማ ልማት ዘርፍም ዩኒቨርሲቲው ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ትልቅ አጋር በመሆን የዘርፉን ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ በርካታ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየና አሁንም በስፋት እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን የጠቀሱት ፕ/ር ፍቅሬ አሁን ካለው የከተሞች በከፍተኛ ደረጃ የመስፋፋት ዝንባሌ ጋር ተያይዞ ከሚስተዋለው በፕላን የመመራት ችግር ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያግዙ አዳዲስ የትምህርት መርሀ-ግብሮችን በመቅረጽ እና ነባር ፕሮግራሞችንም በመከለስ ሂደት ላይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ደጉ በቀለ ባደረጉት አጭር ገለጻ ኮሌጁ ከምስረታው ጀምሮ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በርካታ ተማሪዎችንም በመደበኛው የትምህርት መርሀ-ግብር አሰልጥኖ ከከፍተኛ ዲፕሎማ እስከ ፒኤች ዲ ድረስ ሊያስመርቅ የቻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪም በሚሰጡት የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎችም እና የማማከር ስራዎችም ከሁለት መቶ ሺ በላይ ለሚሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠት መቻሉንና ለተለያዩ ከተሞችም የከተማ መሪ ፕላኖችን መስራት እና የማሻሻያ ስራዎችን ከማከናወንም ባሻገር በርካታ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችም መከናወናቸውን ዶ/ር ደጉ ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር ደጉ በገለጻቸውም ኮሌጁ ያሉት የትምህርት ፕሮግራሞች ያሉባቸውን ክፍተቶች መለየትና ክለሳ ማድረግ፣ ከከተሜነት መስፋፋትና ዕድገት ጋር ተያይዞ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞችን መቅረጽ፣ በኮሌጁ ያሉትን መምህራን አቅም ማሳደግ፣ የሚሰጡት ስልጠናዎችም ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ማስቻል፣ ልዩ ልዩ ልምዶችን በመቀመር አጋርነትንና ትብብር የበለጠ ማጠናከር በወደፊት የትኩረት አቅጣጫነት ተለይተው የተያዙና በዕቅድ ተይዘው እየተሰራባቸው መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በእስካሁኑ ጉዞው በሀገር ደረጃ ትልቅ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ያለ ተቋም መሆኑ በመግለጽ በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለው ከፍተኛ የከተሜነት መስፋፋት ጋር ተያይዞ እየመጡ ያሉ ከፍተኛ ፍላጎቶች፣ ስማርት ከተሞችን ቀድሞ የማዘጋጀትና በአግባቡ መምራት እንዲሁም በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ የዩኒቨርሲቲው እገዛ እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ በዚህ ረገድ በጋራ በምንሳራቸው ጉዳዮች መለየትና እንዴት እንደሚሰሩም መመካከር አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው በዚህ ረገድም ቀጣይ ውይይቶችን ማድረግ እና ያለውን ግንኙነትም የበለጠ ማጠናከር አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሚያደርገው ሁሉን አቀፍ የልማት እንቅስቃሴም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን ያለቸው የካበተ ልምድና እስካሁንም በሀገር አቀፍ ደረጃ ያበረከቱት አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስታውሰው በቀጣይም ከዩኒቨርሲቲው እገዛ ለተቋሙ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በዩኒቨርሲቲው የሚገኘውን የከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ ቤተ-ሙከራን እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ያሉትን የመሰረተ ልማቶቶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ባሉት ሥራዎችም ያለቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡

photo content
+3

በከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር የተመራ ከፍተኛ ኃላፊዎች ቡድን በኢሲሰዩ ጉብኝት አደረገ -------------- የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ቡድን ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችና ከከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ የተለያዩ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ክብርት ሚኒስትሯ በዩኒቨርሲቲው ባደረጉት ጉብኝት ወቅት በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይም በዩኒቨርሲቲውና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መካከል ያለውን ነባር ትብብር የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በውይይቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ብቸኛ የአቅም መገንቢያ ተቋም መሆኑን በማስታወስ በርካታ ሥራዎችን ያከናወነ እና ተልዕኮውምን በብቃት ሲወጣ የቆየ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማ ልማት ዘርፍም ዩኒቨርሲቲው ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ትልቅ አጋር በመሆን የዘርፉን ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ በርካታ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየና አሁንም በስፋት እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን የጠቀሱት ፕ/ር ፍቅሬ አሁን ካለው የከተሞች በከፍተኛ ደረጃ የመስፋፋት ዝንባሌ ጋር ተያይዞ ከሚስተዋለው በፕላን የመመራት ችግር ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያግዙ አዳዲስ የትምህርት መርሀ-ግብሮችን በመቅረጽ እና ነባር ፕሮግራሞችንም በመከለስ ሂደት ላይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ደጉ በቀለ ባደረጉት አጭር ገለጻ ኮሌጁ ከምስረታው ጀምሮ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በርካታ ተማሪዎችንም በመደበኛው የትምህርት መርሀ-ግብር አሰልጥኖ ከከፍተኛ ዲፕሎማ እስከ ፒኤች ዲ ድረስ ሊያስመርቅ የቻለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪም በሚሰጡት የአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎችም እና የማማከር ስራዎችም ከሁለት መቶ ሺ በላይ ለሚሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠት መቻሉንና ለተለያዩ ከተሞችም የከተማ መሪ ፕላኖችን መስራት እና የማሻሻያ ስራዎችን ከማከናወንም ባሻገር በርካታ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችም መከናወናቸውን ዶ/ር ደጉ ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር ደጉ በገለጻቸውም ኮሌጁ ያሉት የትምህርት ፕሮግራሞች ያሉባቸውን ክፍተቶች መለየትና ክለሳ ማድረግ፣ ከከተሜነት መስፋፋትና ዕድገት ጋር ተያይዞ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞችን መቅረጽ፣ በኮሌጁ ያሉትን መምህራን አቅም ማሳደግ፣ የሚሰጡት ስልጠናዎችም ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ማስቻል፣ ልዩ ልዩ ልምዶችን በመቀመር አጋርነትንና ትብብር የበለጠ ማጠናከር በወደፊት የትኩረት አቅጣጫነት ተለይተው የተያዙና በዕቅድ ተይዘው እየተሰራባቸው መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በእስካሁኑ ጉዞው በሀገር ደረጃ ትልቅ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ያለ ተቋም መሆኑ በመግለጽ በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለው ከፍተኛ የከተሜነት መስፋፋት ጋር ተያይዞ እየመጡ ያሉ ከፍተኛ ፍላጎቶች፣ ስማርት ከተሞችን ቀድሞ የማዘጋጀትና በአግባቡ መምራት እንዲሁም በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ የዩኒቨርሲቲው እገዛ እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ በዚህ ረገድ በጋራ በምንሳራቸው ጉዳዮች መለየትና እንዴት እንደሚሰሩም መመካከር አስፈላጊ መሆኑን አመልክተው በዚህ ረገድም ቀጣይ ውይይቶችን ማድረግ እና ያለውን ግንኙነትም የበለጠ ማጠናከር አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሚያደርገው ሁሉን አቀፍ የልማት እንቅስቃሴም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን ያለቸው የካበተ ልምድና እስካሁንም በሀገር አቀፍ ደረጃ ያበረከቱት አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስታውሰው በቀጣይም ከዩኒቨርሲቲው እገዛ ለተቋሙ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በዩኒቨርሲቲው የሚገኘውን የከተማ ልማትና ምህንድስና ኮሌጅ ቤተ-ሙከራን እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ያሉትን የመሰረተ ልማቶቶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ባሉት ሥራዎችም ያለቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡

photo content
+6

In her inspirational speech Professor Netsanet shared her personal experience to the participants and her determination to get at the position she is now and overcoming the challenges that she was facing in connection to gender stereotype. She also share the experiences of Jimma University on how research works undertake. In jimma University researches and most of international collaborations are initiated by the staffs and holding international conferences and seminars at Jimma University attracted scholars and experts around the world. Nurturing the culture of excellence and innovation, and academic integrity within the university brought positive reputation Professor Netsanet noted. She also underlined the importance of personal growth and development and giving attention to the personal wellbeing in order to be healthy and productive in one’s professional life. In his welcoming speech, Dr. Alemayehu Debebe, ECSU Vice President for Research and Partnership, welcomed the participants and noted that ECSU since its establishment passed through several challenges and overcoming these challenges has gained reputation both domestic and international aspects of the academia. Being guided by the principle of continuous learning, it become designated as a Researched University along with the eight first generation universities in the country, Dr. Alemayehu said. Research universities differ from other universities in its dedication in advancing research culture and wining reputation in research productivity and qualities. Research universities also known to the degree to which their research outcomes enforce the policy making of the nation. We have highly tried to make the consumers of our research outcomes need the information and data of our researches into the policy crafting arena, Dr. Alemayehu noted. On the conference a total of 42 (16 from outside and 26 from ECSU) research papers were presented. The thematic area distribution of these researches included Economic and development, Urban Governance, Diplomacy, International Relations, Peace, Human Recourse Management, Public Service Delivery, Leadership and Development, and Crosse Cutting Issues.

𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗵𝗼𝗹𝗱𝘀 𝘁𝗵𝗲 𝟵𝘁𝗵 𝗡𝗮𝘁𝗶𝗼𝗻𝗮𝗹 𝗖𝗼𝗻𝗳𝗲𝗿𝗲𝗻𝗰𝗲 ------------------------ Ethiopian Civil Service University (ECSU) Research Affairs Directorate (RAD) held the 9th National Conference with the theme “Public Sector Transformation and Development” from June 3- 4, 2024 at the newly inaugurated Omo Hall. At the conference ESCU scholars, Researchers and invited Guests from Federal Ministries, Universities, and Addis Ababa City Administration participated. In his opening speech, Professor Fikre Dessalegn, ECSU President, welcomed the participants of the conference to the momentous academic event of the University and noted that as a successive annual events, the motto of this year conference is “Public Sector Transformation & Development”. He also said that this year’s gathering, links up the broader agenda of transformation and development and addresses it in the context of Economic development, urban governance, and Public service delivery, Peace and Conflict Management, Diplomacy; and also in the context of Environment and Development; and Human Resource and Leadership Competencies. “ECSU has been actively engaging in research activities for nearly a decade and disseminating its research findings to the end users. Data over the past 9 years indicated that the research productivity in terms of volume of research conducted and the number of publications as articles in journals and proceedings; and also as PhD monographs and other scholarly products are very encouraging. A total of 448 staff grant research topics have been researched, dozens of articles have been published in successive volumes of our journals and proceedings; and also in other local and International journals, and we have records of 109 PhD monographs produced by our alumni. The research productivity is higher when including research outputs by our second degree students. Among these, those published in indexed and journals of wider circulation are obviously a key in enhancing our University’s image and visibility at national and global stages, despite five of our journals are still awaiting accreditation by the Ministry of Education.” Professor Fikre noted. He also added that in the past five years alone, ECSU has executed 59 relatively bigger research and consultancy projects, with about 400 million-birr funded by public sector organizations in addition to budget allocated from government treasury and the research findings disseminated and recommendations enabled beneficiaries to deeply understand some of the public sector problems and pin point possible solutions to the problems identified. ECSU is now embarking into the road of becoming Graduate and Research University by maintaining its legacy and responsibility of building public sectors’ capacity. Besides, it is gradually evolving as a university of choice by the public servants and employees of private sector, despite the low intake capacity when compared to candidates applying to join our academic programs, Professor Fikre added. Finally he thanked all the researchers for bringing their expertise and innovative ideas to the conference as well as the organizing committee of the conference. In her keynote address, Professor Netsanet Workneh, Vice president of Research and Partnership of Jimma University said that ECSU has been differentiated as Research University based on its achievements and capacities which has shown through its educational programs, innovative researches, initiatives and capacity building efforts. The university’s commitment for excellence and advancement of public services for the betterment of the society is exemplary, Professor Netsanet added. She also explained that research and innovations are at the heart of the public service transformation and development. The academic staff is more oriented mostly in teaching rather than research undertakings. In this regard, it is expected to make transformations in mindset, create conducive atmosphere to research and innovation to become research intensive university.

photo content
+2

𝐄𝐂𝐒𝐔 𝐇𝐨𝐥𝐝𝐬 𝐚 𝐏𝐮𝐛𝐥𝐢𝐜 𝐥𝐞𝐜𝐭𝐮𝐫𝐞 𝐨𝐧 𝐓𝐫𝐚𝐧𝐬𝐢𝐭𝐢𝐨𝐧𝐚𝐥 𝐉𝐮𝐬𝐭𝐢𝐜𝐞 -------------------------- Ethiopian Civil Service University (ECSU) Research and Partnership Division and School of law in collaboration with the Public Diplomacy section of U.S. Embassy hold a Public lecture under the title "Navigating Truth, Accountability, and Reconciliation: Perspectives on Transitional Justice in Ethiopia" on May 25,2024 at ECSU . At the opening of the program, Vice President for Research and Community Service, Dr Alemayehu Debebe, welcomed the participants and introduced the importance of transitional justice for leading democratic and harmonizes life, particularly with the context of Ethiopia. According to him setting a clear objective for the decision, listing the possible alternatives, placing weighing criteria and selecting the appropriate model for making the decision are the basic steps in decision making process. Guest of the speaker, Professor Sirleaf Matiangai, briefed the participants on the history and current situation of Ethiopia concerning to the transitional justice quoting examples of some African countries. She outlined the main reason why she initiated to conduct this research on this topic is the traumatic history of Ethiopian on War and conflicts. As she indicated that taking lesson from the past and other instances should be important though a lot of challenges are there to undergo the process of transitional justice. She mentioned the four pillars of transitional justice: Truth seeking, Justice or asserting the right to justice and rejecting impunity, Reparation or providing reparation for victims, and guarantees of non-repetition in the future. These processes had been tried on the era of different regime in Ethiopia. Furthermore, the lecturer reviewed the five aspects of transitional justice and considered options to bring peace and justice to the future .Establishing truth commissions, applying reparation programs, making structural reforms, constructing Museums and Memories, and conducting effectively criminal prosecution are the main aspect of TJ . Professor Sirleaf Matiangai also gave brief information about the status of political violence and the role of education and academicians to bring sustainable peace. “Transitional justice is an effort to right the wrong that was done and is an idea of acceptance of responsibility for the committed crimes’’ she underlined. The other speaker was Ms Kalkidan Dereje from Ministry of Justice and she thanked ECSU for inviting the Ministry of Justice to participate in the seminar. This is a good beginning for collaboration and further partnership with ECSU regarding to TJ. Ministry of Justice is the main facilitator for TJ policy implementation she underlined. She said that Higher Education Institution has a critical vote and responsibility under the police and we look forward for further activities in the implementation process. She also explained the process of how TJ policy was developed. The participants raised different questions and the presenters were respectively answered the questions. The public lecture was moderated by Asst. Prof. Teguada Albachew . Professor Sirleaf Matiangai, Professor of Law at the University of Maryland, Francis King Carey School of Law. She holds a secondary appointment in the Department of Epidemiology and Public Health at the University Of Maryland School Of Medicine. Professor Sirleaf writes and teaches in the areas of global public health law, public international law, international human rights law, international criminal law, post-conflict and transitional justice, and criminal law. She is the editor of the first thematic print volume on Race and National Security, which is forthcoming with Oxford University Press in 2023.

photo content
+5

በማጠቃላያዉም ላይ ፕሬዚዳንቱ እንዳሳሰቡት በተለይ እንዲህ አይነት ግምገማ እነደ አመራርም ትልቅ ትኩረት የምንሰጠዉ ፣ የካዉንስል አባላትም በግልጽነት ጥያቄዎች እና ማብራሪያዎች የሚያነሱበት እና የምንወያይበት መድረክ እንደመሆኑ የካዉንስል አባላት በስብሰባ በመገኘት ሀላፊነታቸዉን መወጣት አለባቸዉ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ለአራተኛ ሩብ አመት አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ ግምገማ ተጠናቋል፡፡

ኢሲሰዩ ካውንስል የ2016 የዘጠኝ ወራት የሥራ ክንውን ግምገማ አካሄደ ----------------- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የዩኒቨርሲቲውን የ2016 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውን እና መደበኛ የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ግምገማ ሚያዝያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በግምገማ መድረኩ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ባደረጉት ንግግር መድረኩ ያለፉት ዘጠኝ ወራት በሪፎርምና በዕቅድ የተያዙ ሥራዎች ክንውን የሚገመገምበት እና በቀጣይ ለሚተገበሩ ሥራዎችም አቅጣጫ የምናስቀምጥበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡ አክለውም ከ2016 ዓ.ም የበጀት ዓመት ጀምሮ የተሟላ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆንና የተሸለ መዋቅራዊ፣ አስተዳደራዊና አካዳሚያዊ ነጻነትን ሊያጎናጽፈን የሚችለውን ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆንን የሚያስችል የዝግጅት ጊዜ ዕቅድ አቅደን እየሰራን የቆየን በመሆኑ በዚህ ረገድ የተሰሩ ሥራዎችን በዝርዝር የምንገመግምበት፤ አጀንዳዎቹም ሰፋፊና በርካታ ጉዳዮችን ያካተቱ በመሆናቸው እየተተገበሩ ያሉትን ሥራዎች ከምን ላይ እንደደረሱ ካዉንስሉ የሚያረጋግጥበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም የምርምር ዩኒቨርሲቲ መሆን እና ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆን እራሳቸውን የቻሉ ሁለት የተለያዩ አጀንዳዎች መሆናቸው የገለጹት ፕ/ር ፍቅሬ በምርምር ዪኒቨርሲቲነት የተቀመጡትን ሀገራዊ መስፈርቶች በሚገባ ማሟላት ወሳኝ መሆኑን ፣ ራስ-ገዝ ዩኒቨርቲነትም የሚፈለገውን መስፈርት ተሟልቶ ሲገኝ ብቻ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራትን ከእነዚህ መስፈርቶች አኳያ በስፋት እንገመግማለን ብለዋል፡፡ እነዚህን አጀንዳዎች ለመተግበርም ለዩኒቨርሲቲው በተፈቀደው የምርምር ዩኒቨርሲቲ መዋቅር መሰረት የሰራተኞች ምደባ መደረጉ ትልቁን መደላድል የፈጠረ እና ከዚህ ጋር ተያይዞ የመጣው ለውጥ ምን እንደሆነ፣ ለተልዕኮ ስኬት እጅግም ረብ የማይኖራቸውን ለማጥራት በቀጣይ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን ያወሱት ፕ/ር ፍቅሬ በስፋት አዲስ ከተተገበረው መዋቅር ጋር ተያይዞ የሴኔት መተዳደሪያና የተከታታይ ትምህርት መመሪያ ብቻ የተሸሻሉ በመሆናቸው በቀጣይ ሌሎች በርካታ መሻሻል ያለባቸው ደንቦች ፣ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች መታየት እንደሚኖርባቸው በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ ራስ-ገዝ መሆንን አስመልክቶም ራስ ገዝነት ‘'ራስን በራስ ማስተዳደር’’ ማለት ሳይሆን ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የፋይናንስ አቅም ማሳደግ የተለያዩ የገቢ ምንጮቹን በመለየት ወደ ትግበራ በመግባት ገቢ ማመንጨት፣ ተያያዥ የአፈጻጸም ነጻነቶች ማግኘት ነዉ ብለዋል፡፡ራስን በራስ ማስተዳደር ያለበቂ ሀብት የማይታሰብ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ጠንካራ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው ለማስቻል 22 የተጠኑ የገቢ ማመንጫ ተለይተው እየተሰራባቸው መሆኑን፣ እና ሌሎችም በማጠናከር በ2020 ዓ.ም 30 በመቶ የራሳቸውን በጀት ከውስጥ ገቢ ለመሸፈን የተጣለውን ግብ ለማሳካት መትጋት ያስፈልጋል ፡፡ ሌላው ብቁና በቂ የሰው ኃይል መኖር፣ ያሉት የትምህርትና የስልጠና ፕሮግራሞች ተፈላጊነት፣ የተማሪዎች ምልመላና ቅበላ ፖሊሲዎች፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ማስቀጠል፣ ጠንካራ የምርምርና የማማከር ስርዓትን መፍጠር፣ በድህረ ምረቃ የሚሰራ የምርምር ውጤት በአግባቡ ማደራጀት፣ የዲጂታል የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ማጠናከር፣ በትብብርና ትስስር እንዲሁም ዓለማቀፋዊነት አንጻር እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም እና ውጤቶች፣ ደረጃውን የጠበቀ የመሰረተ ልማት እና ፋሲሊቲ ማስፋፋት እና ሌሎች አንኳር ጉዳዮች ላይ የተሰሩና የታዩ ጉድለቶችን በማንሳት መወያየት እንደሚገባ አስምረውበታል፡፡ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ዓመታት በኦዲት ግኝት ያልተገኘበት ተቋም መሆኑን አስገንዝበው ይህ ጠንካራ የኦዲት ስርዓት ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑን ለካውንስሉ ገልጸው የበጀት እጥረት፣ ለተማሪዎች በሚቀርበው የምግብ አቅርቦት እና ሌሎችም ውጫዊ ጉዳዮች ጫና የፈጠሩበት መሆኑን ለካውንስሉ ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም በአራቱ ዘርፍ ማለትም በአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ፣በምርምርና ትብብር ዘርፍ ም/ፕሬዚዳንት፣በማናጅመንት ዘረፍ እና በአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዘርፍ የተከናወኑ የየዘርፋቸውን የዘጠኝ ወራት የሥራ ክንውን እና የሪፎርም ሥራዎች ሪፖርት ለካውንስሉ ያቀረቡ ሲሆን ከቀረበው ሪፖርት መሰረትም የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ ከራስገዝነት ተልዕኮ ልየታ፣ በመረጃ አያያዝና ዲጂታል ሥርዓት ግንባታን በተመለከተ IFMIS፣ ICSMIS፣ EGP፣የCCTV ካሜራና የሠራተኞች ቁጥጥር በጣት አሻራ ቴክኖሎጂዎች ማካሄድ መቻሉን ፣ አዳዲስ የካሪኩለም ማሻሻያዎች፣ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል፣ እና የሰው ኃይልንም በበቂ ሁኔታ ለማብቃት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውና ስልጠናዎች መሰጠታቸው በሪፖርት ቀርቧል፡፡ የተለያዩ ፖሊሲዎች፣ መመሪያዎችና ደንቦች መከለሳቸው፣ የሚሰሩ የምርምር ጭብጦች የተለዩ መሆናቸው፣ የተጀመሩ አጋርነቶችን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያድጉ መደራጀታቸው በተለይ ዩኒቨርሲቲው የጎረቤት ሀገራትን ሲቪል ሰርቪስ ግንባታ ለመደገፍ እና ትብብርን ለማጠናከር እየሰራ ያለዉ ስራ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን የዓለም አቀፍ ተማሪዎችና መምህራን በተቋሙ ተሳትፎአቸዉ አሁን ካለበት ደረጃ ከፍ ማለት እንደለበት ተመላክቷል ፤ በ 2015 ዓ.ም ፋይናንስ ከተደረጉ ምርምር ስራዎች አስራ ሁለቱ መታተማቸው ከ2011 እስከ 2015 ዓ.ም የተካሄዱ አመታዊ የምርምር ጉባኤዎች ላይ የቀረቡ የጥናት ወረቀቶች በተቋሙ ድረ ገጽ ላይ መጫናቸው እና በማማከር አገልግሎትም ጥራትና ብዛትን ለማሻሻል የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸው በሪፖርቶቹ ተመላክተዋል፡፡ አስተዳደርና ልማትን በተመለከተም ዩኒቨርሲቲው ባካሄደው ሰራተኞች ምደባ ለ 979 ሰራተኞችን በአዲሱ መዋቅር መሰረት ሁሉም ሰራተኞች በሚባል ደረጃ በአሁኑ ወቅት ላይ ምደባ ማግኘታቸው ተገልጸዋል፡፡ የበጀት፣ የፋይናንስ፣ የግዥና የንብረት አስተዳደርን አስመልክቶም በርካታ ስራዎች መከናወናቸው በሪፖርቱ የተገለጸ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 37,108,671.57 ብር ከወጪ ቀሪ የውስጥ ገቢ መገኘቱ፣ አጠቃላይ የበጀት አጠቃቀሙም 82.25 በመቶ መሆኑ እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማትና ፋሲሊቲዎች ማደረጃትን በተመለከተ በአዲስ አበባ ዋናው ግቢ በተለይ ትምህርትና ስልጠናን በዘመናዊ መንገድ የሚያስኬዱ G+7 የስልጠና ማዕከል እና G+8 ሁለገብ ሕንጻዎች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን በተጨማሪም ነባር የወሊሶ ካምፓስ ግንባታዎች እየተካሄዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም በ2015 መጨረሻ ተግባራዊ ለተደረገዉ የመጀመሪያ ዲግሪ የመዉጫ ፈተና (Exit Exam) ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በኢሲሰዩ ዉስጥ የተዘጋጀ ሲሆን ተገቢዉን ግብዓት በማቅረብና በማስተባበር እንዲሁም የሌሎች ተቋማት ተማሪዎች ጭምር በዩኒቨርሲቲዉ እንዲፈተኑ በማመቻቸት ረገድ ዩኒቨርሲቲዉ ተቋማዊ ሀላፊነቱን በብቃት በመወጣት ጉልህ ሚና እንደተጫወተ ተገልጿል፡፡ የካውንስሉ አባላትም በቀረበው ሪፖርት ላይ የተለያዩ ጥያቄዎች፣ ሀሳብና አስተያየቶችን እንዲሁም መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮችን በማንሳት ሰፊ ውይይቶችን ሲያደረጉ አባላቱ ላቀረቧቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የየዘረፉ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

Weekend and Extension Registration for 2017 EC