ar
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

الذهاب إلى القناة على Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Public Service University

تُعد قناة Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 734 مشتركاً، محتلاً المرتبة 15 729 في فئة التعليم والمرتبة 2 648 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 734 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.81‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.95‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 434 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

12 734
المشتركون
+124 ساعات
+187 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+2

ኢሲሰዩ ባለ ስምንት ወለል አዲስ ህንጻ ለማስገንባት ውል ተፈራረመ ----------- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለሚያሰራው ባለ ስምንት ወለል ህንጻ ፕሮጀክት ባወጣው ጨረታ መሰረት የጨረታው አሸናፊ ከሆነው ጉተማ ፈሬሳ ኮንስትራክሽን ጋር መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም የግንባታ ማስጀመርያ ስምምነት ውል ተፈራረመ፡፡ በስምምነት ፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅትም የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደገለጹት ይህ አዲስ የሚገነባው ባለስምንት ወለል ህንጻ በዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ሊባል የሚችል እስካሁን ካከናወናቸዉ ፕሮጀክቶች ትልቁ ፕሮጀክት ሲሆን በተለይ ተቋሙ ራስ ገዝ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እንደአንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሊይዛቸዉ የሚገቡ ዘመናዊ መማሪያ ክፍሎች ዘመኑ የደረሰባቸዉ ቴክኖሎጂዎች አደራጅቶ ይይዛል ብለዋል፡፡ ህንጻዉ ሲጠናቀቅ በርካታ አገልግሎት የሚሰጥ ዘመናዊ ክፍሎች ለተለያየ አገልግሎት የሚዉሉ ዘመኑ ባፈራቸዉ ቴክኖሎጂ የታገዙ ዘመናዊ የዉስጥ ቁሳቁሶች አብሮ ያካተተ ሲሆን ለዩኒቨርስቲያችንም እንደ አንድ ''ላንድ ማርክ'' ተደርጎ የሚወሰድ ነዉ ብለዋል፡፡ ተቋራጩም ባለው የካበተ ልምድ እና ቀደም ሲልም በዩኒቨርሲቲው ሌሎች ህንጻዎችንም በገባው ውል መሰረት አጠናቆ ያስረከበ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን ይህን ፕሮጀክትም በውሉ መሰረት አጠናቆ እንደሚያስረክብ ሙሉ እምነት እንዳላቸዉ በመግለጽ ፤ነገር ግን በተቻለ መጠን በተቀመጠዉ ግዜ ሰሌዳ አጠናቆ ለአገልግሎት እንዲደርስ፣ ተቋሙ የጀመረዉ የራስ ገዝ ሂደት የሚያፋጥን ስለሚሆን አደራ እያልን ድርጅቱም ሀገራዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ የጉተማ ፈሬሳ ኮንስትራክሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉተማ ፈሬሳ በስምምነቱ የተሰማቸው ደስታ ገልጸው ፕሮጀክቱን በውሉ መሰረት በማጠናቀቅ ለዩኒቨርሲቲው ለማስረከብ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸው ከዩኒቨርሲቲውና ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር በመነጋገር፣ በመወያየትና በመተጋገዝ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ እንደሚሆን ቃል ገብተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አማካሪ ኡቦን ቮያጅ አማካሪ ድርጅት ሀላፊ አቶ አለሙ መረራ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ሁሉን አካታችና ዘመናዊ ህንጻ ከመሆኑ እና ስምምነቱም ህንጻውን ከነሙሉ ግብዐቱ አጠናቆ ማስረከብን የሚያካትት በመሆኑ ከተለመደው የግንባታ አካሄድ ወጣ ያለ መሆኑን ተገንዝቦ አሸናፊዉ ድርጅት ከወዲሁ በሁሉም ረገድ ብቁ ሆኖ መገኘት ተገቢ መሆኑን አሳስበዋል፡፡ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሂደት በተመለከት የኢሲሰዩ የምህንድስናና ጥገና አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለሙ ሲሳይ እንደገለጹት ይህ ሁለገብ የመማርያ ህንጻ ለመገንባት ግልጽ ጨረታ የወጣ ሲሆን የተለያዩ ተወዳዳሪዎች ተወዳድረዉ 5 ተወዳዳሪዎች የተቀመጠዉን መስፈርት ያሟሉ ሲሆን ከእነዚህ ዉስጥም የጉተማ ፈሬሳ ኮንስትራክሽን ድርጅት በ 2,326,162,955.48 (ሁለት ቢሊየን ሶስት መቶ ሀያ ስድስት ሚሊየን አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ሺ ዘጠኝ መቶ አምሳ አምስት ብር ) እንዳሸነፈ አብራርተዋል፡፡ የሚገነባው ሕንጻም እጅግ ዘመናዊ መሆኑ የጠቀሱት አቶ አለሙ በውስጡም 19 የተለያዩ ቢሮዎችን፣ 24 አንድ መቶ ተማሪዎችን የሚይዙ የመማሪያ ክፍሎችን፣ 18 ሰላሳ ሰዎችን የሚይዙ ስማርት ክፍሎችን፣ 285 እና 110 ሰዎችን የሚይዙ ሁለት አዳራሾችን ፣ 11 ሱቆችን፣ 1 ሺ ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ አንድ ቤተ-መጽሐፍ፣ 6 ተማሪዎች እርስ በርስ የሚወያዩባቸው ስቱደንት ኮርነርስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ ፣ 87 መኪናዎችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚያስችል የመኪና ማቆሚያና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚሰጥ ህንጻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

photo content

photo content
+2

የኢሲሰዩ የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ሰራተኞቹ የምስጋና ፕሮግራም አደረጉ ------ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ሁለት G+ 10 ህንጻ 175 አባወራዎችእና እማወራዎች የሚዝ በማስገንባት ለመምህራን እና ለሰራተኞች ማስረከቡ ይታወቃል ፡ይህንንም ትልቅ ተግባር ላበረከቱ አመራሮች ነዋሪዎች የምስጋና ፕሮግራም በማዘጋጀት በ 9/6/2016 ዓ.ም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በምስጋና መክፈቻ ፕሮግራም ላይ የነዋሪዎች ተወካይ ዶ/ር ደጀኔ ግርማ እንዳሉት ይህ ትልቅ ሸክም በማቅለል፣ የሰራተኛዉን የቤት ችግር ጥያቄ በመቀበል ፣የግንባታዉን ሀሳብ ጭምር በማመንጨት ለሰራተኛዉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ብዙ ዉጣ ዉረዶችን በማለፍ ለዚህ ልዩ ቀን ላደረሱን ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ነዋሬዎችን ወክዬ ምስጋና በማቅረቤ ትልቅ ደስታ ይሰማኛል ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ምቹ ሁኔታ የተቋሙ ሀላፊዎች በመፍጠራቸዉ ሠራተኛዉን በስራዉ አካባቢ ተረጋግቶ መስራት የሚያስችል፣ ያለበትንም ጫና የሚቀንስ እና የተሰጠዉን ሀላፊነት በተሳካ ሁኔታ ለመፈጸም የሚያስችል ልዩ ፕሮጀክት ሲሆን ፕሬዚዳንቱ ተቋሙን ለመምራት በተቀላቀሉን ወቅት የሰራተኛዉ የቤት ችግር ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን ለዚህም ምላሽ ፕሮጀክት ቀርጸዉ ብዙ ዉጣ ዉረዶችን አልፈዉ ሰራተኛዉ በቤቱ እንዲኖር ትልቅ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለዩኒቨርስቲዉ ፕሬዚዳንት አሁንም ደግመን ደጋግመን እናመሰግናለን በማለት የኛ ምስጋና የአንዴ ብቻ ሳይሆን ሁሌም በወጣን በገባን ቁጥር ምስጋናችን በልባችን እናቀርባለን ለዚህም የነዋሪዎች ኮሚቴ ይህንን የምስጋና ፕሮግራም ያዘጋጀዉ ብለዋል፡፡ የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ በዕለቱ የተሰማቸዉን ደስታ በመጥቀስ ይህ ፕሮጀክት ብዙ ዉጣ ዉረዶች የታለፈበት ቢሆንም የልፋታችን ዉጤት በዚህ መልኩ ስናየዉ ደስታችን የላቀ ፣ድካማችንን ያስረሳ ስኬት ሲሆን አሁን እንዲህ ሰራተኛዉ ገብቶ መኖር በመጀመሩ ለኔ ልዩ ስሜት ያለዉ ሲሆን ከሰራኋቸዉ ስራዎች፣ በህይወቴ ከተደሰትኩባቸዉ ቀናቶች በሙሉ ትልቁን ቦታ ይይዛል ብለዋል፡፡ በህይወት ዘመን ብዙ የግል ስኬቶች ቢኖሩም ነገር ግን በተለይ ለሌላዉ ሰዉ ነገሮችን ማመቻቸት ኑሮን ማቅለል የመሰለ ደስታ የሚሰጥ ሀላፊነት የለም በማለት ለዚህች ልዩ ቀን ደርሰን እናንተም ተደስታችሁ ስላመሰጋናችሁን በማናጅመንቱ ስም አመሰግናለዉ ብለዋል፡፡ በተጨማሪ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ ሰራተኞች ፣አመራሮች እኔም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል ፡፡ በመጨረሻም ኮሚቴዉ የምስጋና ሽልማት እና እዉቅና ሰርተፍኬት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል፡፡ይህ ፕሮጀክት ሁለት G+ 10 ሕንጻ ያሉት በአጠቃላይ 175 አባወራዎችእና እማወራዎች የሚኖሩበት ዘመናዊ የመኖርያ መንደር ነዉ፡፡

photo content

photo content

𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗣𝗿𝗲𝘀𝗶𝗱𝗲𝗻𝘁 𝗗𝗶𝘀𝗰𝘂𝘀𝘀𝗲𝘀 𝘄𝗶𝘁𝗵 𝗗𝗲𝗽𝘂𝘁𝘆 𝗛𝗲𝗮𝗱 𝗼𝗳 𝗘𝗨 𝘁𝗼 𝗔𝗨 Professor Fikre Dessalegne, Ethiopian Civil Service President, discussed with H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of Delegation European Union to the African Union on further strengthening the bilateral relations of ECSU and Kehl University in Germany on January19, 2024 at Hidasse Hall. The President welcomed H.E. Riccardo Mosca, Deputy Head of EU Delegation to African Union and University Scholars and students from Kehl University, Germany. He added: ‘I am pleasured to see scholars from different background and different countries which is a valuable input for working together in the areas of public services. ‘’ The president said that as a higher Institution, one of ECSU strategic plan is partnership, internationalization and networking, so we have interest to further strengthening the tie with Kehl University. As we see, the progress of masters’ program in public Management in International relations which we started in collaboration with kehl University is one of the successes that has brought by collaborative effort he added. He also explained the overall strategic plan of ECSU on the Internationalization and partnership and the interest of working together in different areas with Kehl University. Dr lemma Gudissa, ECSU Vice President for academic affairs, on his part, welcomed the Delegates and explained the strengthening of collaboration between the two institutions in different aspects in the future .He also noted that to further strength the masters’ program and open PhD program in collaboration with Kehl university .Besides, he briefly explained the University’s vision, mission, and values to the representatives and his discussion with kehl university Rector on the bilateral issues . Dr. Joachim Beck, Rector of Kehl University, explained that how the international cooperation creates a learning environment and understand different system of government and practices in each country and opportunities to understand the different cultures in different countries. He also explained that in the collaborative masters’ program five universities from four countries are working together and ECSU is one of the partner institute. He also briefed that the two institutions have the same vision which are working on Public service capacity building. So it possible to work together in administrative culture and developed the two years masters’ program to PhD project he underlined. Onur Yel, Counselor of culture and Press representing Germen Embassy in Ethiopia thanked the hospitality of the Ethiopian and Civil Service University. He also emphasized developing cooperation among different institutions is very important and wished the students for the successful accomplishment of the program. Finally, Students raised different questions for H.E. Riccardo Mosca and he respectively answered the questions raised by the students.

photo content

photo content
+5

G+7 የስልጠና ማዕከል ግንባታ ዉል ስምምነተ ተደረገ ------------------------------------------ የኢትዮጲያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) ዘመናዊ የስልጠና ማዕከል የግንባታ ዉል ስምምነት ከ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ 19/4/2016 ዓ.ም አደረገ፡፡ተቋራጭ ድርጅቱ ግንባታዉን በ2 ዓመት ዉስት ገንብቶ ለዩኒቨርስቲዉ እንደሚያስረክብ ገልጿል፡፡ በዉል ስምምነቱ ወቅት የኢሲሰዩ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደተናገሩት ይህ ፕሮጀክት በ2 ዓመት የግዜ ገደብ የሚጠናቀቅ ሲሆን በተለይ ዩኒቨርሲቲዉ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ለሚያደርገዉ የሽግግር ሂደት ትልቁን ድርሻ ይይዛል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ በዉስጡ የተለያዩ ዘመኑን የዋጁ ማሰልጠኛ ክፍሎች፣ሙዚየሞች እንዲሁም ለአንድ ዘመናዊ ስልጠና ማዕከል የሚያስልጉ ክፍሎች ከተሟሉ ግብአቶች ጋር የሚይዝ ሲሆን ተቋሙን አሁን ካለዉ የስልጠና መዕከል ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግረዉ ነዉ ብለዋል፡፡ የፕሮጀክት አሸናፊ አሴፍ ኢንጂነሪንግ ይህን ግንባታ ሲያከናዉን አደራ ጭምር የምንሰጠዉ የፕሮጀክቱ አሸናፊ ድርጅት ብቻ ሳይሆን እንደ ዜጋ ሀላፊነቱን በመወጣት ለትዉልድ የሚተላለፍ ግንባታ በመገንባት አሻራዉን ማሳረፍ አለበት ብለዋል፡፡ዩኒቨርስቲዉ የሚገነባዉ ህንጻ ለትዉልድ ተሸጋሪ እንዲሆን ከጅማሪዉ ጀምሮ ትልቅ ትኩረት አድርጎ የሰራ መሆኑን በመግለጽ ይህ ፕሮጀክት እዚህ ደረጃ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሂደት በተመለከት የኢሲሰዩ የምህንድስናና ጥገና አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለሙ ሲሳይ እንደገለጹት የስልጠና ማዕከሉ ለመገንባት ግልጽ ጨረታ የወጣ ሲሆን 36 ተወዳዳሪዎች ተወዳድረዉ 6 ተወዳዳሪዎች የተቀመጠዉን መስፈርት ያሟሉ ሲሆን ከእነዚህ ዉስጥም አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ 687,299,720.41 (ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮንሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺ ሰባት መቶ ሃያ ብር) እንዳሸነፈ አብራርተዋል፡፡ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አስራት ኤፍሬም እንደገለጹት ከዩኒቨርስቲዉ ጋር ለመስራት እድሉን ስላገኙ ደስተኛ መሆናቸዉን በመግለጽ ማዕከሉን በጥሩ ሁኔታ መርተን በተቀመጠለት የግዜ ገደብ በማጠናቀቅ እናስረክባለን ብለዋል፡፡ አሴፍ ኢንጅነሪንግ ተቋራጭ ድርጅት በ1994 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመስራት ብዙ ልምድ ያለዉ ዉጤታማ ስራ የሰራ መሆኑን ገልጸዉ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት የምንሰራዉ ስራ ምስክር እንዲሆን አድርገን እንገነባዋለን ብለዋል፡፡

photo content
+1

በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የጸረ ሙስና ቀን ተከበረ --------------------- በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀን ‘‘ሙስና ጠላታችን ነው ፤በጋራ እንታገለው’’ በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርስቲዉ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ/ም በፓናል ውይይት እና በተቋሙ በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት በማቅረብ ተከብሯል፡፡ የውይይቱን መድረክ የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በአስተላለፉት መልዕክት ‘‘ ሙስና ግዑዝ ነገር አይደለም ፤ሀብት በአግባቡ ለታለመለት ጉዳይ አለማዋል ማለት ነዉ ፡፡በዚህም አመራሮች የመወሰን ስልጣን ያለን የመንግስት ሀብት በአግባቡ እየተጠቀምን ነዉ ወይ የሚለዉን መጠየቅ ፣ተቋማችንን እያየን በመገምገም አቅጣጫ እያስቀመጥን የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የጸረ ሙስና ትግል አካል ሆነን እነደ ዜጋ ድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል ፡፡’’ ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ በስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሰላማዊት ተ/ሚካኤል ‘’የሙስና ምንነትና የሚያስከትለው ጉዳት’’ በሚል ርዕስ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በስጋት አስተዳደር ላይ የተካሄደ የጥናት ግኝት ቀርቧል፡፡ በውይይቱም የሙስና ምንነት ፤ መንስኤዎችና መገለጫዎቹ፤ ሙስና የሚያስከትለው ጉዳት እንዲሁም ሙስናን በጋራ ለመከላከል የባለ ደርሻ አካላት ሚና ምን መሆን እንዳለበት ለተሳታፊዎች በዝርዝር ቀርቧል ፡፡ በእለቱም በየዘርፉ ያሉ ኃላፊዎች የሙስና ተጋላጭነት እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚታገሉት የዘረጉት አሰራር ጭምር አብራርተዉ ለሙስና ሂደት በር የሚከፍቱ አሰራሮች እንዴት እንደሚከታተሉ አስተያየታቸዉን በመስጠት የዘርፋቸዉን ሂደት ገምገመዋል፡፡በተለይ ከፍተኛ ፋይናንስ የሚያንቀሳቅሱ እና የሰው ሀብትን የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ከመታገል አኳያ እራሳቸውን እንዲፈትሹ በቀረበው የውይይት ርዕስ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአንዳንድ ስራ አስፈጻሚዎች በተጨባጭ የተሰራው ስራ እና የታየው የፀረ ሙስና ትግል ቁርጠኝነት ለሁሉም ስራ አስፈጻሚዎች በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በማጠቃላያዉም ላይ ፕሬዚዳንቱ እንደተናገሩት ይህ መድረክ የምንማማርበት ግንዛቤ የምንጨብጥበት መድረክ እንደመሆኑ ሁላችንም በተሰማራንበት እና አመራር በምንሰጥበት ዘርፍ ስራዎች በአግባቡ መሰራቱን የማረጋገጥ ትልቅ ሀላፊነት እንዳለብን ከዚህ ባለፈም ለምንስራቸዉ ማንኛዉም ስህተቶች ከተጠያቂነት እንደማናመልጥ መገንዘብ ማንኛዉም ስራዎች በህግ እና በህግ አግባባብ ብቻ መስራት አስፈላጊ ነዉ ብለዋል፡፡

photo content
+2

በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተከበረ --------------- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን ቀን “ ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት“ በሚል መሪ ቃል ህዳር 21 ቀን 2016 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ ተማሪዎችን እና ሰራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት እና የጥያቄና መልስ ዉድድር በማድረግ አከበሩ፡፡ የፓናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታዴዎስ ሜንታ እንደተናገሩት ይህ በዐል በዋናነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲከበር የባህል ትዉዉቅ ከመፍጠሩም በላይ የሕዝቦችን ወንድማማችነት በማጠናከር ሕብረ ብሔራዊ አንድት ለማጎልበት ትልቅ ሚና እንደሚኖረዉ በመግለጽ በዓሉ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች እርስ በእርስ ከመተዋወቃቸዉ ባሻገር የእርስ በእርስ መቀራረብ የሚፈጠርበት ትልቅ ኩነት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ ሀገራችን በርካታ መገለጫዎች ያሏቸው ከ80 በላይ ብሄሮች ብሄረሰቦች ያሉባት ሀገር እንደመሆኗ የህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓት በጠንካራ ሂደት መገንባት ለሀገር እድገት እና ሰላም ግንባታ የማይተካ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ የፌደራሊዝም ጥናት ትምክርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ግሩም ክንፈሚካኤል ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ በጽሁፋቸው ኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ የተገበረቻቸዉን የመንግስት አወቃቀር በመዳሰስ በአሁን ወቅት እየከተለቸዉ ያለዉን የሕብረ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓት አብራርተዋል፡፡ በቀረበው የመነሻ ፅሁፍ ላይ አሰተያየቶችና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች በመቅረብ ውይይት ተደርጓል፡፡ በማስከተልም በፊደራሊዝም የሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎች መካከል የጥያቄና ምልስ ዉድድር ተካሂዷል፡፡ በዓሉን አስመልክቶ ቀደም ሲል በተከናወኑ መርሀ- ግብሮችም በህዳር 14 ቀን 2016 ዓም በጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን ማዕከል የአልባሳት ልገሳ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ በክረምት መርሀ ግብር በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራ ተከናውኗል፡፡

photo content
+1

𝗘𝗖𝗦𝗨 𝗚𝗿𝗮𝗱𝘂𝗮𝘁𝗲𝘀 𝗛𝗗𝗣 𝗧𝗿𝗮𝗶𝗻𝗲𝗲𝘀 -------------------------------------------------- Ethiopian Civil Service University graduated 23 instructors with Higher Diploma Program (HDP) on October 29, 2023 at Hidase Hall of the University. The training was underway for one year and facilitated by Academic Programs Directorate (APD). On the graduation program, ECSU President Prof. Fikre Dessalegn congratulated the graduates for their successful accomplishment of the training and awarded them higher diploma certificates. He also disclosed that it is mandatory for a higher institution instructors to take HDP training in order to continue as an effective instructors. Besides, he explained that the training is given at the higher diploma level enables the instructors to transfer their knowledge gained in the academic fields of study to students .It also gives them an understanding of how instructors should teach their students by using the appropriate and up-to-date teaching methodologies. According to Dr. Temesegen Birega, Director of the Academy Program Directorate, ECSU has certified 146 instructors in five rounds with higher diplomas and become able to reach 51.3 percent of instructors certified with HDP so far. The coordinator of the program, Ms. Ababa Siyum on her part, thanked those who supported the training program. She also extended her deepest gratitude to Dr. Alemayehu Debebe, on behalf of the HDP training team for his invaluable support.

photo content
+2

የኢሲሰዩ ካውንስል የ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ ክንውን ግምገማ አካሄደ ------------ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ ክንውን ግምገማ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በስብሰባው መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ዩኒቨርሲቲው ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ተጠሪነቱ ለኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር መሆኑን ተከትሎ በርካታ የሪፎርምና የማሻሻያ ስራዎችን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ባደረግነውም ጥረት ከአንጋፋ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በምርምር ዩኒቨርሲቲ ምድብ ስር ለመመደብ የቻልን ቢሆንም ካሉት መስፈርቶችም መካከልም ገና በስፋት ልንሰራባቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ከዕቅዱ ጋር ተካተው እየተተገበሩ መሆናቸውን የምንገመግምበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡ በመቀጠልም አሁን በመተግበር ላይ ባለው አዲስ የመዋቅር ለውጥ ጋር ታያይዞም አመራሩን የማደራጀት፣ ቀጥሎም የዩኒቨርሲቲውን የአካዳሚክ ዘርፍ አመራሮችን የመደልደል እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞችንም በውድድር የመመደብ ሰፊ ስራዎችን ተሰርተዋል፤ የተቀሩትንም ለመመደብ ስራዎች በመሰራት ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ የመዋቅር ለውጡን ተከትሎም የተለያዩ መመሪያዎች፣ ደንቦች እና ፖሊሲዎች ላይ የክለሳና የማሻሻል ስራዎች መሰራታቸውንና ከእነዚህ ክለሳ ከተደረገባቸው መመሪያዎች መካከልም የዩኒቨርሲቲው የሴኔት ሌጅስሌሽን በቅርቡ እንደሚጸድቅ ለካውንስሉ ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ከተማሪዎች የመውጫ ፈተና እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በመተግበር ላይ ካለው ከድህረ ምረቃ የተማሪዎች ቅበላ ፈተናን ከአሁኑ ታሳቢ በማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ለካውንስሉ አሳስበዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲውን የመማር ማስተማር ሥራም በቴክኖሎጂ የተደገፈ በማድረግና ሌሎች ተጓዳኝ ተግባራትም ላይ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ያመላከቱት ፕ/ር ፍቅሬ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ሁለትና ሶስት ዓመታት ውስጥ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን የተቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ጠንካራ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው፣ ተመራጭ የሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዲኖሩትና ተወዳዳሪ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን፣ በምርምር ዘርፉም ምርታማና ፋይዳ ያላቸው የምርምር ስራዎች የሚሰሩበት ስርዓት እንዲኖር ከወዲሁ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በግምገማው ላይም የአካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ፣ የምርምርና ትብብር ዘርፍ፣ የአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዚደንቶች ዶ/ር ለማ ጉዲሳ፣ ዶ/ር አለማየሁ ደበበ፣ ዶ/ር ታዲዎስ ሜንታ የየዘርፋቸውን የ 2016 ዓ.ም ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የማኔጅመንት ድጋፍ ዘርፍ ሪፖርት ደግሞ በዶ/ር አብርሃም ሐጎስ የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ ቀርቦ ካውንስሉ በስፋት ተወያይቶበታል፡፡ በመጨረሻም ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በሰጡት ማጠቃለያ አዲስ እየተተገበረ ያለው ሪፎርም ለዩኒቨርሲቲው እጅግ ወሳኝ ከመሆኑ አንጻር ሁሉም የስራ ክፍል የሪፎርም አጀንዳዎቹን በዕቅድ ውስጥ በማካተት ለተግባራዊነቱ መስራት ተገቢ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዩኒቨርስቲ ምድብ ሥር የተካተተ መሆኑን በማስታወስ አንድ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች አንጸር የበለጠ ብቁ ሆኖ መገኘት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው እዚህ ብቃት ላይ እንዲደርስ መስፈርቶቹን መሰረት በማድረግ በበለጠ ትጋትና ኃላፊነት መስራት ፣ ለዚህም ከአሁኑ መነሳት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

photo content
+4