ar
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

إظهار المزيد
3 587
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
+4830 أيام
أرشيف المشاركات
ለ ኮንስትራክሽን መፅሐፍ ፈላጊዎች ከላይ ባለው አድራሻ አግኙት @etconp

Bids must be delivered to the address below on or before April 27, 2025 at 2:30 P.M except for Construction Works of Aletawondo - Teferikela - Dilla (32.503km) and Aletawondo - Chuko Spur (7.092km) Road Project on or before March 20, 2025 at 2:30 P.M. Director General 2nd Floor, Conference Room Ethiopian Roads Administration Ras Abebe Aregay Street P. O. Box 1770 Addis Ababa, Ethiopia Tel. +251-11-551 71 70/79 Fax. +251-11-5514866

🔺ታምራት ፕሌት እና ጄቦልት አቅራቢ🏗 📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን ✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና ማጠፊያ ማሽኖች አሉን 🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን
🔺ታምራት ፕሌት እና ጄቦልት አቅራቢ🏗 📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን ✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና  ማጠፊያ ማሽኖች አሉን 🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን 📐ማንኛዉንም የሞደፊክ ስራዎችን እንሰራለን 📍ኢትዮጵያ ዉስጥ የትም እንልክሎታለን! ➕➕➕➕➕➕➕➕➕ 📍አድራሻችን፦ ቁ.1 አዉቶብስ ተራ(መሳለሚያ)                     ቁ.2 መርካቶ                     ቁ.3 ተክለሀይማኖት 📞0904040477 📞0911016833

📌ኬኙማም ኮንስትራክሽን ግብዓት አምራች 🫅👸ለውድ ደንበኞችን ጥራት ያላቸውን ምርቶቻችንን እያቀረብን መቆየታችን ይታወቃል ። በመሆኑም አሁን :-         🏘 ለመኖሪያ ቤቶች          🏨ለአፓርትመንት          🏢ለኮንዶሚኒየም         🏗 ለተለያዩ ህንፃ ግንባታ የሚውሉ የተለያየ መጠን ያላቸውን ብሎኬቶች ከቱርክ ባስመጣነው ሀይድሮሊክ ማሽን ማቅረባችንን ቀጥለናል ። 🚧ባለ # 10 🚧ባለ # 15 🚧ባለ # 20 🤌🤌 ይደውሉ 0901222277/88 0987127351 0944124540 0913122512

በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያ
በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል። በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል። 🔴ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15278/

ኮንስትራክሽን ዘርፍ አደጋ። "በህይወት ማዉጣት ተችሏል" 🏷ትላንት የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7 ቤለር እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በደረሰ የኮንስትራክሽን የስራ ላይ
+3
ኮንስትራክሽን ዘርፍ አደጋ። "በህይወት ማዉጣት ተችሏል" 🏷ትላንት የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7 ቤለር እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በደረሰ የኮንስትራክሽን የስራ ላይ አደጋ ሁለት ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። አደጋዉ የደረሰዉ የመንገድ ፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ ለመቅበር በቁፋሮ ስራ ላይ በነበሩ ሁለት ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ መጠን ያለዉ አፈር ተንዶባቸዉ ነበር። የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ባለሞያዎች አምስት ሜትር ገደማ ጥልቀት ካለዉ ጠባብ ጉድጓድ ዉስጥ አፈር ተጭኗቸዉ የነበሩትን ሁለቱን ሰራተኞች 1:20 ሰዓት በፈጀ ጥረት በኋላ በህይወት ማዉጣት ችለዋል። በህይወት የወጡት ሁለቱ ወጣቶች እድሜያቸው  27 እና 29 ዓመት የተገመተ ሲሆን በአደጋው ምክኒያት ጉዳት የደረሰባቸው በመሆኑ  በኮሚሽኑ አምቡላንስ እየተረዱ ወደ ዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ በአዲስ አበባ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ተገቢዉን የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ጠብቆ ባለመስራት መሰል አደጋዎች በተደጋጋሚ እያጋጠሙ በመሆኑ በተለይም አሰሪዎች የሰራተኞቻቸዉን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታቸዉን እንዲወጡም ኮሚሽን መ/ቤቱ ያሳስባል። ለእሳትና ለሌሎች ድነገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ 939 ፈጥነው ያሳውቁ Via እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር @etconp

👉COST TYPES 1.Direct Cost vs. Indirect Cost - Direct Cost These costs are directly linked to a specific project, task, or activity. They vary depending on the project’s scope and progress. ⚡️Examples: Raw materials used in construction (cement, steel, bricks) Wages of laborers and site engineers assigned to a project Subcontractor costs for specific project tasks Equipment or machinery rented for a particular project - Indirect Cost These are overhead costs that support multiple projects but are not tied to a specific activity. They remain relatively constant regardless of individual project progress. ⚡️Examples: Office rent, utilities, and administrative salaries IT infrastructure and software licenses Safety training, legal compliance, and insurance Company-wide marketing and management expenses 2.Fixed Cost Vs Variable Cost -Fixed Cost Costs that remain constant regardless of project activity or production levels. They do not fluctuate with the volume of work performed. ⚡️Examples: Office rent and administrative salaries,Equipment depreciation ,Long-term leasing of machinery or site offices Insurance and permit fees. - Variable Cost Costs that change depending on the level of production or work performed. These expenses fluctuate as project activity increases or decreases. ⚡️Examples: Wages of temporary laborers hired per project phase,Fuel costs for site equipment and vehicles,Cost of materials (cement, steel, sand) based on demand ,Utility bills (electricity, water) that vary with usage 3.Operational Cost These are ongoing expenses required to maintain daily business or project operations. Unlike capital costs (one-time investments in assets), operational costs are recurring. ⚡️Examples: Salaries of permanent employees ,Maintenance and repair of machinery and equipment Fuel, utilities, and transportation expenses,Office supplies, communication, and IT support.

#ADVERTISEMENT 🔧📐📐ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት 📐📐 መማምረቻ ድርጅት⚙🔧🛠 🛠🛠🛠የምንሰጣቸው አገልግሎቶች🛠🛠🛠 1 መገለጫችን የሆነው የሞደፊክ ስራዎች 2 እዲሁም ፕሌት ከ 1
#ADVERTISEMENT 🔧📐📐ፀግሽ ፕሌት እና ጄቦልት 📐📐                    መማምረቻ ድርጅት⚙🔧🛠 🛠🛠🛠የምንሰጣቸው አገልግሎቶች🛠🛠🛠 1 መገለጫችን የሆነው የሞደፊክ ስራዎች 2 እዲሁም ፕሌት ከ 1ሚሊም እስከ 30 ሚሊም እንቆርጣለን እበሳለን 3 በመቀጠል ጄቦልት 12ሚ እስከ 32ድረስ ጥርስ አውጥተን አጥፈን እናቀርባለን 4 የተለያዩ ቦልቶች በፈለጉት መጥን
📍 አድራሻ መገኛችን
ቁ1. በእጆት ባለ ስልክ ለናተ ቅርብ ቁ2. በታታሪዎች መገኛ ኮርቻ ተራ ቁ3. አየር ጤና ኪዳን ምህረት ጊቢ ማንኛውም ልሜራ እዛው በዘመናዊ ማሽን እቆርጣለን ቁ4. ሴሚት ፍየል ቤት በቅርባ ባራቱም አቅጣጫ ማሳሰብያ ከጊዜው አንፃር የዋጋ ንረት ካሳሰቦት እኛጋ እሚገርም መፍትሄ አለ በማያስቡት መልክ ስራዎን ይሰራሉ ይደውሉ ስልክ ቁጥር☎️ 📞0912492727 📞0913061530 📞0923764834 መልካም ስራ ለራስ ነው ቸር ይግጠማቹ ፀግሽ    ፕሌት እና ጄቦልት!

ማስታወቂያ:- NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ መገኛ አድራሻው ቦታ:- 📍- ተክለሃይ
+3
ማስታወቂያ:-
NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ
መገኛ አድራሻው ቦታ:-
📍- ተክለሃይማኖት በርበሬ በረንዳ
ስልክ ቁጥር:-
🔺📞+251- 944454610 🔺📞+251- 952730999 #LTZ 28 #LTZ 38 #LTZ 48 #CHS ከ ባለ 12mm ጀምሮ .... #RHS #I BEAM #U CHANNEL #H BEAM #Mesh Wire #የ ኣጥር ሽቦ #Galvanized Pipe #Angle #Aluminium Sheet #D ብረት#8 ቁጥር #ፌርሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ! ስትፈልጉ በቀጥታ ይደውሉ.. .

ለአዲስ አበባ ባለጓሮዎች በ2016 ዓ.ም በተሻሻለው የአዲስ አበባ የህንፃ መመሪያ መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ክልል ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ ማልማት የሚችሉበትን ህጋዊ አሰራር ያሳ
ለአዲስ አበባ ባለጓሮዎች በ2016 ዓ.ም በተሻሻለው የአዲስ አበባ የህንፃ መመሪያ መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ክልል ውስጥ የሚገኙ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ ማልማት የሚችሉበትን ህጋዊ አሰራር ያሳያል፡፡ በመመሪያው ከገጽ 34 እስከ 36 በተገለፀው መሰረት ከ1,000 ካሬ በታች ላሉ ይዞታቸው ስፋት 80 በመቶ ያልበለጠ፣ ከ1,001 እስከ 2,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 70 በመቶ ያልበለጠ፣ ከ2,001 እስከ 3,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 50 በመቶ ያልበለጠ፣ ከ3,001 እስከ 4,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 25 በመቶ ያልበለጠ፣ ከ4,001 እስከ 5,000 ካሬ ሜትር ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ እንዲሁም ከ5,001 ካሬ ሜትር በላይ ላሉ ይዞታዎች የይዞታው 20 በመቶ ያልበለጠ ነገር ግን አጠቃላይ ግንባታው ከ2,000 ካሬ ሜትር በላይ መብለጥ የለበትም ሲል ይደነግጋል፡፡ ይህ ማለት ቀደም ብሎ አርሶ አደሩ ማልማት የሚችለው 5% በሚል ተቀምጦ የነበረው አሰራር ከላይ በተዘረዘሩት አገላለፆች ተቀይሯል ማለት ነው፡፡ የአርሶ አደር ማቋቋምና ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ ሎኮ ዳለቻ አርሶ አደሩ ለረጂም ጊዜ ሲጠይቅ የነበረው ጥያቄ መልስ ያገኘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ነገር ግን ሌብነትና ብልሹ አሰራርን መከላከል ይገባል ብለዋል፡፡ አያይዘውም በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መመሪያው ሳይሸራረፍ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የአርሶ አደር ማቋቋምና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረጋሣ ባይሳ በበኩላቸው መመሪያውን ለክፍለ ከተሞች እንዳወረዱ፤ በባለሙያም አተገባበሩ ላይ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡ በአዲስ አበባ አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን

በሀገራችን ኢትዮጵያ በግንባታው ዘርፍ የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች:- 🚧በኮንስትራክሽንፈ ኢንዱስትሪ የማጭበርበር አመለካከትና ተግባር የሚስተዋልበት ነባራዊ ሁኔታ መኖሩ 🚧በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የሰለጠነና የሙያ ብቃቱ የተረጋገጠ የሰው ኃይል እጥረት ያለ መሆኑ 🚧የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ስራ አመራር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የተሳለጠ ያለመሆኑ 🚧በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የሚሠማሩ አማካሪዎችና ተቋራጮች መካከል ተወዳዳሪነት በሚፈለገው ደረጃ ማድረስ ያልተቻለ መሆኑ 🚧ለኮንስትክሽን ኢንዱስትሪ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ቀጣይነት ያለው የአቅርቦት ሠንሠለት ያልተዘረጋ መሆኑ 🌟ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መስፋፋትና መጠናከር የተመቻቸ ሁኔታ የሚፈጥር የፋይናንስና የማሽነሪ አቅርቦት ሥርዓት የተጠናከረ ያለመሆን 🌟የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዋና ዋና ባለሚናዎች በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ ለዘርፉ የተፋጠነ ዕድገት በጋራ የሚሰሩበት ሁኔታ ያለመፈጠሩ 🌟የህንፃ ግንባታና መጠቀሚያ ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር አገልግሎት የተጠናከረ ያለመሆን 🌟ፈርጀ ብዙ ሥራዎች ከኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ሥራዎች ጋር ተጣጥመው የሚታቀዱበትና የሚተገበሩበት ሥርዓት ያለመዘርጋቱ 🌟የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ልማት ፕሮግራም ወይም ፓኬጅ አዘጋጅቶ በተሟላና በቀጣይነት ያለመተግበር 🌟ለባለሞያዎችና ስራተቋራጮች የሚደረግ የአቅም ግንባታ ድጋፍ እጅግ አናሳ መሆን

👉"ስለኖሩበት ብቻ በሕገ ወጥ መንገድ የተገነቡ ቤቶች አይፍረሱም" የሚለውን እሳቤ እንደማይቀበለው የሸገር ከተማ አስተዳደር አስታወቀ 🏷በከተማው ከ1 ሺሕ በላይ ባለሃብቶች ከተፈቀደላቸው መሬት በላይ ወስደው መገኘታቸው ተገልጿል የሸገር ከተማ አስተዳደር ያለፉትን አስር ዓመታት ሲገነቡ የነበሩ ሕገ-ወጥ ቤቶች፤ ለቀጣይ የተሻለ ከተማ ለመግንባት ችግር በመሆናቸው መፍረሳቸው ተገቢ ነው ሲል ለአሐዱ ገልጿል፡፡ 'ውሃ እየከፈልኩ ነበር' 'መብራት ስከፍል ቀይቻለሁ' በሚል ምክንያት የሚቆይበት ዕድል እንደሌለና 'ለዛ ምትክ ይሰጠኝ' የሚለው ጉዳይ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ከሚከተለው የከተማ ግንባታ ጋር አብሮ የሚሄድ አለመሆኑን፤ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ተናግዋል፡፡ "ባደጉት ሀገራት ከተሞች እንዴት ነው ያደጉት የሚለውን መመልከት ያስፈልጋል" የሚሉት ዶ/ር ተሾመ፤ ሕጋዊ የሆነ ስርዓት ሲኖርና በሕግ መሬት ሲወሰድ እንዲሁም በሕግ ግንባታ ሲፈፀም ብቻ  መሆኑን አክለዋል፡፡ በመሆኑም ከተማዋውን ወደፊት መገንባት በሚፈለግበት ሁኔታ ላይ ምንም ዓይነት ሕገ-ወጥ አካሄዶችን እንደማይታገሱ ከንቲባው ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው የሸገር ከተማ አስተዳደር ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ የቤት ግንባታዎችን ማከናወኑን የሚገልጹት ከንቲባው፤ በተለይም ለከተማ አስተዳደሩ ሠራተኛ እና ነዋሪዎች ቤት ግንባታ ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ባለው አነስተኛ በጀት በሁለት ቢሊዮን ብር በስምንት የከተማ አስተዳደሩ ክፍለ ከተሞች ላይ የቤት ግንባታ ማከናወናቸውን ጨምረው ገልጸዋል። አሐዱም "በሸገር ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ አካባቢዎች ቤት ገንብተው ግብር ሲከፍሉ እና የውሃ እና መብራት ሲከፍሉ የኖሩ ዜጎች እጣ ፈንታ ምን ይሆናል?" ሲል ከንቲባውን ጠይቋል፡፡ የከተማ አስተዳዳሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በምላሻቸው፤ "መብራት ሲከለከልም ሆነ ውሃ ሲከፈል የቆየ ነዋሪ በሕገ-ወጥ መንገድ ይቀጥል ተብሎ አይጠበቅም" ብለዋል፡፡ "በሕገ-ወጥ ቤት ግንባታ ላይ የሚሰማሩ ዜጎች ምንም ዓይነት ለኢኮኖሚው የሚሰጡት ጠቀሜታ የለም" የሚሉት ከንቲባው፤ በተለይም ያለፉት አስር ዓመታትን በዚህ ረገድ ከፍተኛ ችግር መስተዋሉን ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል በከተማ አስተዳደሩ ከ4 ሺሕ ባለሃብቶች ውስጥ ከአንድ ሺሕ በላይ የሚሆኑት ከተፈቀደላቸው መሬት በላይ ይዘው መገኘታቸውን ከንቲባው ገልጸዋል። በከተማ አስተዳደሩ የመሬት ወረራን በተመለከተ ከፍተኛ ሥራ መስራቱን የተናገሩም ሲሆን፤ በዚህ ሕገ-ወጥ ድርጊት ላይ ተሳትፈው የሚገኙ ባለሃብቶች ላይ እርምጃ መወሰዱንና መሬቱም ለሌላ ባለሃብት ተላልፎ መሰጠቱን አስታውቀዋል። "አሁን ላይ በዘፈቀደ መሬት መቀራመትም ሆነ መውረር በፍፁም አይቻልም" ያሉት ከንቲባው፤ አብዛኛው ሥራ በዚህ ወቅት በቴክኖሎጂ በተደገፈ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ውጪ ሀገር የሚገኙትን ጨምሮ በኦን ላይን ወይም በይነ መረብ ምዝገባ እስካሁን 500 አመልካቾች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በተለይም ከዚህ ቀደም ለባለሃብት መሬት መሰጠት ላይ ብልሹ አሰራር ውስጥ ተዘፈቀው የሚገኙ አመራሮች እና ሠራተኞች ላይ እርምጃ መውሰዱን እንዲሁም፤ አሁን ላይ በድንበር የሚፈጠር ግጭት አለመኖሩን ከንቲባው ጨምረው ተናግረዋል፡፡ አክለውም በአሁን ወቅት በሸገር ከተማ አንድ ባለሃብት መሬት ለማግኘት አንድ ቀን ብቻ እንደሚፈጅበት አንስተዋል፡፡ "ከዚህ ቀደም ባለሃብቱ በዚህ ቦታ ላይ 'መሬት ይሰጠኝ' በማለት ያለ ፕላን በዘፈቀደ መሬት ከመሰጠቱም በላይ ለእርሻ የሚሆኑ ቦታዎች ጭምር በኢንቨስትመንት ሥም ተሰጥተዋል" ብለዋል። በመሆኑም ከተማ አስተዳደሩ በሁለት ዓመት ውስጥ በሰራው ሥራ ያለ አግባብ ከ10 እና 15 ዓመት በላይ መሬት አጥረው የተቀመጡ መሬቶችን ጭምር የመውረስ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል። Via አሐዱ ሬዲዮ @etconp

🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱 Red brick:- This is the classic brick color that you see Quality with affordable price 🧱ጥራ
🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱 Red brick:- This is the classic brick color that you see Quality with affordable price 🧱ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ ጡቦችን እናመርታለን። 🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣ 🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣ 🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣ 🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣ 🧱  ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣ 🧱 ለx-ray ክፍሎች፣ 🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣ 🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣ 🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣ 🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣ 🧱 ለአበባ መትከያ 🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣ 🧱 ለፒዛ ኦቭን፣ 🧱 ለምድጃ፣ 🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ፣    NEW POINT BRICK FACTORY *We produced best quality clay bricks for various construction purposes. 🧱 For building construction, 🧱 For bank vaults, 🧱 Fence for the yard, 🧱 For road edges, 🧱 For Hotels,Restaurants,and Cafes decoration, 🧱 For x-ray rooms, 🧱 For manuals, 🧱 For kitchen, 🧱 For shower tray 🧱 To cover PBC drains, 🧱 For garden, 🧱 Furnace For steel factory, 🧱 For pizza oven, 🧱 For waste incinerator, 🧱 For more information join our telegram channel 🧱Order now 📲0912854327,0902378888 🧱"Quality is our first priority 🧱Thank you 谢谢

VACANCY 💫ስትራክቸራል ፎርማን (የመንገድ ግንባታ) 🚧ማንበብና መጻፍ የሚችል አግባብ ባለው የሥራ ልምድ ከዚህ ውስጥ 6 ዓመት እንደ ፎርማን የሰራ 📜ችሎታዎች - ድሮዊንግ በአግባቡ ማንበብ የሚችል - ከስሩ ላሉ ሰራተኞች የስራ ክፍፍል መስጠት እንዲሁም መምራት የሚችል Quanitity Required: 2 Addis Ababa Minimum Years Of Experience: #9_years Deadline: March 12, 2025 📩How To Apply: የትምህርት ማስረጃችሁን እና የስራ ልምዳችሁን ፎቶ በማንሳት ከታች ያለውን የ ቴሌግራም ሊንክ በመጠቀም ያመልክቱ https://t.me/anduamlak4

👉ከአያት ሪል ስቴት ሱቅ የገዙ ሰዎች በድርጅቱ ላይ አቤቱታ አሰሙ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አያት ሾፒንግ ሞል በሚል በተገነባው ህንፃ ውስጥ ሱቅ የገዙት የዛሬ 16
👉ከአያት ሪል ስቴት ሱቅ የገዙ ሰዎች በድርጅቱ ላይ አቤቱታ አሰሙ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አያት ሾፒንግ ሞል በሚል በተገነባው ህንፃ ውስጥ ሱቅ የገዙት የዛሬ 16 አመት እንደነበር አቤቱታ አቅራቢዎቹ ገልፀዋል፡፡ በወቅቱ ድርጅቱ በሁለት አመት ውስጥ ግንባታውን አጠናቆ እንደሚያስረክባቸው ቃል እንደገባላቸውም አስረድተዋል፡፡ የአያት ሞል ሱቅ ባለቤቶች ማህበር ፀሀፊ ሩት ግርማይ ስትናገር ‹‹እኛ የማህበሩ አባላት በህጋዊ መንገድ ሱቅ የገዛንና ውል የፈፀምን ነን፡፡ ነገር ግን ድርጅቱ ተገቢውን መሰረተ ልማት አሟልቶ ባለማጠናቀቁ ሱቃችንን ለመረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናችን ተዘግቶ ይገኛል›› ብላለች፡፡ እንደገለፀችውም በህንፃው ውስጥ ካልተጠናቀቁት መሰረተ ልማቶች መካከል መብራት፣ ውሀ፣ መፀዳጃ ቤት፣ መኪና ማቆሚያና ሊፍት ይገኙበታል፡፡ የህንፃው ግንባታ ረጅም ጊዜ በመቆየቱ አንዳንድ የማህበሩ አባላት በራሳቸው ወጪ አጠናቀው ስራ መጀመራቸውን ሩት ገልፃለች፡፡ ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ለመውሰድ ቢፈልጉም የገንዘብ እጥረት እንዳለባቸው ጠቅሳም በአሁኑ ወቅት ለሚመለከታቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች አቤቱታ በማቅረብ ላይ ቢሆኑም ምንም መፍትሄ አለማግኘታቸውን አስርታለች፡፡ የአያት ሪል ስቴት ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አብይ ማሞ ስለጉዳዩ ከዘሪፖርተር ተጠይቀው ሲመልሱ ‹‹እኛ ሱቅ ገዢዎቹን በመነጋገርና በውይይት ችግሩን እንድንፈታ ጠይቀናቸው ነበር፡፡ እነሱ ግን ጉዳዩን ወደተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መውሰድን መርጠዋል›› ካሉ በኋላ ጉዳዩን ለመፍታት በሂደት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ Via ዘ-ሐበሻ @etconp