Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
الذهاب إلى القناة على Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
إظهار المزيد3 589
المشتركون
-524 ساعات
+37 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
የሐምሌ_ወር_2015_ዓ_ም_የሀራጅ_ሽያጭ_ማስታወቂያ.PDF3.39 MB
*ማስታወቂያ*
የነባር እና የአዳዲስ ስራ ተቋራጮች እና ማህበራት ምዘገባ ለ 5 የስራ ቀናት መራዘሙን የሚገልፅ ማስታወቂያ፡-
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከቤት ልማቱ ጎን ለጎን ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚው ተጠቃሚ ሲያደርግ የቆየና እያደረገም ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ በሚኖረው የግንባታ ፕሮጀክቶች በዘርፉ የተሠማሩ ስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን አሳታፊ አድርጎ ለመስራት ያሰበና ለዚህም ይረዳው ዘንድ በከተማችን ያሉትን የስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን በመመዝገብ መረጃዎችን አደራጅቶ መያዝ እና መመልመል አስፈላጊ ሆኖ በማግኘቱን በቅርቡ በተቋሙ ማህበራዊ ድረ-ገጽ ምዝገባ ማካሄዱ ይታወቃል፡፡
ይሁንና ምዝገባው በተለያየ ምክንያት ያለፋቸው እና ያልሰሙ በመኖራቸው እና ባቀረቡት ቅሬታ መሰረት ለነባር እና አዳዲስ ተመዝጋቢዎች ከቀን 06/11/2015 - 11/11/2015 ዓ.ም ከቀኑ 12:00 ሰአት ድረስ ለለተከታታይ አምስት የስራ ቀናት online ምዝገባው መራዘሙን እየገለጽን ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) http://aahdc.gov.et በመጫን እና የሚጠይቀውን መረጃ በአግባቡ በማስገባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡-
በነባር፡-
በተቋማችንና በተለያዩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የስራ ትስስር ተደርጎላችሁ ስትሠሩ የነበራችሁ ስራ ተቋራጮችና ማህበራት ነባር በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማድረግ ያለባችሁ ሲሆን፤
በአዲስ፡-
ከዚህ በፊት በተቋማችንም ሆነ በቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ምንም ዓይነት የስራ ትስስር ያልተደረገላችሁ አዲስ በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማካሄድ ትችላላችሁ፡፡
ለምዝገባ አስፈላጊ ማስረጃዎችን በድጋሚ ለማስታወስ ያህል፡-
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- የግበር መክፈያ መለያ ቁጥር( Tax
Identification Number- TIN.)
- የስም ስያሜ ምዝገባ ሰርተፊኬት
- የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት
- የስራ ልምድ ከ1-2 ገፅ በማይበልጥ
በዝርዝር ይጠቀስ
- የስራ ልምድ ክብደት በገንዘብ ሲቀየር
የሚያሳዩ መረጃዎች
- እና ሌሎች ስራ ተቋራጩን እና
ማህበራቱን የሚገልጹ ሰነዶችን ናቸው
ማሳሰቢያ፡-
ከስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ ከሚመለከተው አካል በሚላከው መረጃ መሠረትና በተቋማችን ባለው መረጃ መሠረት ወደ ስራ ሲገባ በነባር መመዝገብ እያለባችሁ በአዲስ ተመዝግባችሁ የተገኛችሁት ላይ እንዲሁም በሁለቱም (በነባርም፣በአዲስም) ተመዝግቦ የሚገኝ ስራ ተቋራጭም ሆነ ማህበራት ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ከዚህ በፊት በነበረው ምዝገባ ማለትም እስከሰኔ 27/2015 ለተከታታይ 15 ቀን ሲደረግ በነበረው ምዝገባ የተመዘገባችሁ በዚህ ምዝገባ ማድረግ የማይጠበቅባችሁ መሆኑን እንዲሁም
አንድ ተቋራጭ ወይም ማህበር ከአንድ ጊዜ በላይ መመዝገብ የሌለበት መሆኑን እያሳወቅን ማንኛውም ይህንን ማሳሰቢያ ተላልፎ የተገኘ ተመዝጋቢ ከምዝገባው የሚሠረዝ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ነው
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የተለያዩ የድህንነት መጠበቂያ ዕቃዎች ግዥ
ጨረታ ቁጥር ECWCT/NCB/PG-57/2015
‹
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የተለያዩ የየተለያዩ የድህንነት መጠበቂያ ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ብቁ ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
1. በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ነገር ግን በአቅራቢዎች ዝርዝር ያልተመዘገቡ ተጫራቾች ለሚመለከተው የመንግስት መ/ቤት በማመልከት የምዝገባ ሰርቲፊኬት ማግኘት ይችላሉ፡፡
2. በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል የዘመኑ ግብር የከፈሉበት ከሚፈለገው አገልግሎት የተዛመደ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት እና በጨረታው ለመሳተፍ ከሀገር ውስጥ ገቢዎች ቢሮ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ በማቅረብ የማይመለስ ብር 300.00/ሶስት መቶ /በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት የሀገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን ቢሮ በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
3. የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው፡፡ የጨረታው ሰነድ የተዘጋጀው በአማረኛ ቋንቋ ነው ፡፡
4. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ጨረታ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይንም በባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ግዥ መምሪያ ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ ቀን ሐምሌ 11 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ነው፡፡
6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ቀን ሐምሌ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ቅጥር ግቢ በሚገኘው ግዥ መምሪያ-1 የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
8. ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግዥ መምሪያ ቢሮ
አድራሻ፡-ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ህንፃ 200 ሜትር ገባ ብሎ
አንድነት ኢንተርናሽናል ት/ቤት ፊት-ለፊት
ስልክ ቁጥር 0118-13 45 27 / 0118-72 29 47
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ማስታወቂያ-ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር አባላት!
ጂ.አይ.ዜድ. ኢትዮጵያ ኢንተግሬሽን በሚባል ኩባንያ በኩል ከፍ ያለ ደረጃ ያለውና ለ 10 ቀናት የሚሰጥ የአመራር (Leadership) ሥልጠና ለመስጠት አቅዶ በዚህ ሥልጠና ላይ ለመካፈል ፍላጎቱ ያላቸውን በፆታቸው ሴት የሆኑና በአመራርነት እየሠሩ የሚገኙ ሠልጣኞችን መርጠን እንድልክለት ጠይቆናል፡፡
ለሥልጠናው ብቁ የሚሆኑ ሠልጣኞችን ለመምረጥ የሚስችል መሥፈርትም አዘጋጅቶ የላከልን በመሆኑ ይኽው መሥፈርት ከዚህ ማስታወሻ ጋር ተያይዞ እንዲደርሳችሁ ተደርጓል፡፡ ሥልጠናው የሚጀምረው እ.ኤ.አ. በኦገስት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ ሥልጠና ላይ ለመካፈል ፍላጎቱ ያላቸውና መሥፈርቱን የሚያሟሉ ሠልጣኞችን እስከ መጪው ረቡዕ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በዚሁ ገፅ ላይ እንድታሳውቁን እንጠይቃለን፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር
የግንባታ ስራ የሚያከናውኑ ማሽነሪ ኦፕሬተሮችና ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ለመንገድ ደህንነት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ተገለጸ።
መንገዶች ላይ ጉዳት በሚያስከትል ሁኔታ ጭነት በሚያጓጉዙ አሽከርካሪዎችና የኮንስትራክሽን ግንባታ ማሽነሪ ኦፕሬተሮች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳሰበ።
በከተማችን በተለያዩ ስፍራዎች ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑ ይታወቃል። ከግንባታዎቹ ጋር ተያይዞ ሲሚንቶ የሚያቦኩ ተሽከርካሪዎች የተቦካ ሲሚንቶ መንገድ ላይ በማፍሰስ እንዲሁም ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ከጭነት አቅም በላይ አፈርና ሌሎች ተረፈ ምርቶችን መንገዶች ላይ በማፍሰስ እና ጭቃ በጎማቸው ይዘው ወደ ጎዳና የሚወጡ አሽከርካሪዎችም ሆኑ ባለንብረቶች ለመንገዶች ደህንነት ማድረግ የሚገባቸውን ጥንቃቄ ባለማድረጋቸው በከፍተኛ ወጪ በተገነቡ መንገዶች ላይ ጉዳት ከማድረሳቸው ባሸገር ለትራፊክ መጨናነቅ መንስኤ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
ፖሊስ አጥፊዎቹ ከጥፋታቸው እንዲታረሙ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ መቆየቱን አስተውሷል።
በጥፋቱ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከለካል የአዲስ አበባ ፖሊስ እርምጃ እንደሚወስድ አሰጠንቅቋል።
የግንባታ ስራ የሚያከናውኑ ማሽነሪ ኦፕሬተሮችና ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ጭነት በሚጭኑበት ወቅት የመንገድ ደህንነት ህጉ በሚያዘው መሰረት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበቸው እንዲሁም መንገዶቹን በጭቃ የሚያበላሹ፤ የተሽከርካሪዎችንም የጎማ ፅዳት የመጠበቅ ግዴታቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል ያለው ፖሊስ ይህንን መልእክት በመተላለፍ ጥፋት ላይ በሚገኙ አሽከርካሪዎችም ሆኑ ባለንብረቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
💥
ስለ ኮንክሪት እና የኮንክሪት ግሬዶች
.
⚡ኮንክሪት (concrete) ስሙን ያገኘው ከጥንት ሮማኖች ሲሆን
ቃሉም የመጣው ኮንክሪተስ (Concretus) ከሚለው የሮማኖች ቃል ነው የቃል በቃል ትርጉሙ ተያይዞ ማደግ / አንድ ላይ ማደግ የሚለውን ይወክላል።
.
*ኮንክሪት በአለም ላይ በብዛት የምንጠቀመው የግንባታ ቁስ ነው።
ኮንክሪት የሲሚንቶ የአሸዋ እና የጠጠሮች ውህድ ነው ።
የኮንክሪት የእመቃ ጥንካሬ (compressive strength)
ሚለካው በግሬዱ ነው (Grade)። የተለያዩ የኮንክሪት ግሬዶች
አሉ C-5 ፣ C-15 C-25 C-30 ወዘተ የኮንክሪት ግሬድ ማለት
ኮንክሪቱ ከሃያ ስምንት ቀን በኋላ የሚኖረው የእመቃ ጥንካሬ
(compressive strength ) ማለት ነው ለምሳላ C-25 የሆነ
ኮንክሪት ግሬድ ከ28 ቀን በኋላ የሚኖረው የእመቃ ጥንካሬ
25N/mm^2 ይሆናል ማለት ነው የC-30 ግሬድ ደግሞ
ጥንካሬው 30N/mm^2 ነው
.
*ለውሃ ስራዎች ብዙን ግዜ ተመራጩ የኮንክሪት ግሬድ ከ C-30 በላይ ነው
.
*አንዳንድ ግዜ የኮንክሪት ግሬዶች በተለያዩ መፅሃፎች በተለያየ
መልክ ይጠቀሳሉ ለምሳሌ አንዳንድ መፅሃፎች C-30 C-15
የሚለውን አጠቃቀስ ሲጠቀሙ አንዳንዶቹ ደግሞ M-30 M-15
የሚለውን ይጠቀማሉ (ከታች በምስሉ እንደተጠቀሰው) ....በ
«C»የሚጠቀሱ የኮንክሪት ግሬዶች በC መጠቀሳቸው የእመቃ ጥንካሬያቸው የተለካው በሲሊንደሪካል ፍተሻ (CYLINDRICAL test ) ስለሆነ ነው በM የሚጠቀሱት ደግሞ ፍተሻው (test) የተደረገው በኪውቢክ ፍተሻ (cubic test) ስለሆነ ነው። በሁለቱ የፍተሻ አይነቶች የሚደረጉ የኮንክሪት ግሬዶች የእመቃ ጥንካሬአቸው ይለያያል። ሲሊንደሪካል ፍተሻ በአንፃራዊነት የኮንክሪትን ትክክለኛ እምቅ ጥንካሬ ይገልፃል ስለዚህ ከኪውቢክ ፍተሻው የተሻለ ነው ማለት ነው።💥መሰረት /Foundation/
1) ቁፋሮ እና አፈር ሙሌት
⏺መሰረት ሁልጊዜ የተረጋጋ መሬት ላይ ሊቀመጥ ይገባል።
ጥሩ አፈር ካልሆነ በተመረጠ እና ከሌላ ቦታ በመጣ አፈር በሚገባ
ተጠቅጥቆ እና ተደልድሎ ሊቀመጥ ይገባል።
⏺የተመረጠው አፈር ንብርብር/layer/ በየ 25 ሴ᎐ሜ በሚገባ
ሊጠቀጠቅ ወይም ሊደለደል/compact/ ሊደረግ ይገባል።
⏺በሚደለደልበት ወቅት በተወሰነ ረገድ እያንዳንዱን ንብርብር ለተሻለ ጥቅጠቃ እንዲያመች እርጥበት እነዲያገኝ ውሀ ማርከፍከፍ ያስፈልጋል
2) አርማታ ሙሌት እና የብረት ስራ
⏺ቀጭን አርማታ/lean Concrete/ ከተመረጠው አፈር ሙሌት በላይ ሊደረግ ይገባል እንደ አስፈላጊነቱም እርጥበተ መከላከያ/water proof/ ሊደረግ ይችላል።
⏺አርማታ ሙሌት ለመሰረት፣ ቢም፣ ኮለን እና ወለል ስራ የአርማታ ጥንካሬ በትንሹ C25 ሊኖረው ይገባል በተጨማሪ እንደ ስትራክቸራል ዲዛይኑ ሊለያይ ይችላል።
⏺የቢም ብረት የላይኛው ብረት መሀል ላይ የታችኛው ደግሞ ኮለን ድጋፍ/support/ ላይ ሊሆን ይገባል እንዲሁም ማት ፋውንዴሽን ላይ የዚህ ተቃራኒ ይሆናል።
⏺ብረት 4D የብረቱን ውፍረት በአራት በማባዛት የሚሰጠንን ርዝመት በመደረብ መተላለፍ ይተበቅበታል።
⏺ዲዛይን ላይ በተቆራረጠ መስመር /hidden line የሚቀመጡ ብረቶች ሁልጊዜ የታች ብረት ሆነው ይቀመጣሉ።
⏺የአርማታ ሽፋን/concrete cover/አብዛኛውን ግዜ 5ሴ᎐ሜ ይሆናል ከመሬት በላይ ግን በ 2᎐5ሴ.ሜ ይሰራል።
⏺በአርማታ ወይም በብረት የሚሰራ ክፍተት መስጫ spacer/ ልንጠቀም ይገባል።
#Foundation
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
