ar
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie

تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 336 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 651 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 347 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 336 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -104، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 35.99‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.61‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 158 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 808 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.

14 336
المشتركون
-824 ساعات
-327 أيام
-10430 أيام
أرشيف المشاركات
➔መከላከያ ባለበት ቦታ ሁሉ የማታጣው፤ ➔በአማራ ሥም የኢትዮጵያ ልዩ ሃይል የሆነው፤ ➔ሰሜን እዝን በመውጋት የተጀመረውን ጦርነት ከአፋር ወንድሙ ጋር የተሸከመው፤ ➔የፌደራል መንግሥቱ ሊያመሠግነው ቀ
+2
➔መከላከያ ባለበት ቦታ ሁሉ የማታጣው፤ ➔በአማራ ሥም የኢትዮጵያ ልዩ ሃይል የሆነው፤ ➔ሰሜን እዝን በመውጋት የተጀመረውን ጦርነት ከአፋር ወንድሙ ጋር የተሸከመው፤ ➔የፌደራል መንግሥቱ ሊያመሠግነው ቀርቶ ሥሙን ለመጥራት የሚቀፍፈው..... ጀግናው የአማራ ልዩ ሃይል ተጨማሪ የአገር ጠባቂዎችን አስመርቋል። በከሃዲ ሃይሎች ያላግባብ ከመሰዋት የጸዳ የድል ዘመን ተመኘሁላችሁ‼️

አንደበት፣ እውቀት፣ ወገናዊ ስሜት፣ ዘርፈ ብዙ ብቃት፣ የታዳሚን የስሜት ሕዋሳት የመሳብ ክሕሎት የተሰጠው ትንግርተኛ ሰው...!! ትንግርቱ...!! የሚጠሉንን መዝለፍ ትተን የሚበጁንን ከፍ ከፍ ብናደ
አንደበት፣ እውቀት፣ ወገናዊ ስሜት፣ ዘርፈ ብዙ ብቃት፣ የታዳሚን የስሜት ሕዋሳት የመሳብ ክሕሎት የተሰጠው ትንግርተኛ ሰው...!! ትንግርቱ...!! የሚጠሉንን መዝለፍ ትተን የሚበጁንን ከፍ ከፍ ብናደርግ በርካታ አኩሪ ሰዎች ይኖሩን ነበር።

"ጭምብላም" ከሚል ፍረጃ መዳን ከፈለግክ ዘርን መሠረት አድርገው የሚያከፋፍሉትን ጥቃትም ሆነ ጥቅም በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርተህ ይፋ በማውጣት ፈንታ ዘረኛ ድርጊታቸውን ወደ ሰውኛ እሳቤ ቀይሮ በሚ
"ጭምብላም" ከሚል ፍረጃ መዳን ከፈለግክ ዘርን መሠረት አድርገው የሚያከፋፍሉትን ጥቃትም ሆነ ጥቅም በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመስርተህ ይፋ በማውጣት ፈንታ ዘረኛ ድርጊታቸውን ወደ ሰውኛ እሳቤ ቀይሮ በሚሸነግል ኢትዮጵያዊ መነጽር መመልከት ይኖርብኻል!"

ከዚህ በኋላ በአማራም ሆነ በአፋር ክልል ውስጥ ለሚከሰት ወረራ ዋነኛ እና ብቸኛ ተጠያቂው ወራሪው ቡድን ሲዳከም የማገገሚያ ጊዜ ነይቶ የሚመለሰው መንግሥት እንጂ የትኛውም የሽብር ድርጅት ሊሆን አይችልም።

በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመው ግፍና በደል ሊሰማህ የማይችለው የሌላ ብሔር ተወላጅ ስትሆን ሳይሆን የብአዴን አመራር መሆን ከቻልክ ብቻ ነው! እናቶቻቸው አጥፊዎቻቸውን የወለዱት ምን አይነት ሐጢያት ሰርተው ቢረገሙ ይሆን?

አሸባሪው ሃይል በአማራ ሕዝብ ላይ የፈጸመው ጥቃት ይሄኛው አካል ሊፈጽመው ወይም ሊያስፈጽመው ካቀደው ውድመት ጋር ሲነፃፀር ኢምንት ነው። የደረሰብን ግፍ ከተደገሰልን ጋር ሲነፃፀር ምንም ነው! እናም ወገኔ ሆይ ንቃ!

ሁሉም አማራ ሊያነብበው የሚገባ የክሕደት ሰነድ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ አሸባሪው ሃይል የዘመቱበትን ጠላቶች ሲዘረዝር ከኤርትራ መንግሥትና ከፌደራሉ መንግሥቱ በመቀጠል የአማራ ክልልን በሦስተኝነት ያስቀም
ሁሉም አማራ ሊያነብበው የሚገባ የክሕደት ሰነድ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ አሸባሪው ሃይል የዘመቱበትን ጠላቶች ሲዘረዝር ከኤርትራ መንግሥትና ከፌደራሉ መንግሥቱ በመቀጠል የአማራ ክልልን በሦስተኝነት ያስቀምጠዋል። መንግሥት ተብዬው አካል ግን በዚህ ሰነድ ላይ በመከላከያ ሠራዊቱ የተወከሉትን ሁሉንም ክልሎች በጦርነቱ አሳትፎ የትግሉ ባለቤት ካደረጋቸውና ካመሰገናቸው በኋላ ከአሸባሪው ቀጠና በባሰ መልኩ የአማራ ክልልን የስጋቱ ምንጭ ያደርገዋል። ቆይ እኔ እምለው... ➔የአማራ ሕዝብ ልጆቹን ከጉያው አውጥቶ በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ አላሳተፈም እንዴ? ➔ሠራዊቱ በገባበት ሁሉ እየገባ ሲቆስልና ሲሰዋ የከረመው የአማራ ልዩ ሃይል አይደለም እንዴ? ➔150 ሺህ ታጣቂና ፋኖ ያዘመተውስ የአማራ ክልል አልነበረም እንዴ? ➔ከሁሉም በላይ ደግሞ "ትግሉ አልተጠናቀቀም" ከማለት ባለፈ "ድሉ የእኛ ብቻ ነው" የሚል የድል ሽሚያ ውስጥ የገባ የአማራ ኤሊትም ሆነ አክቲቪስት ነበረ እንዴ? እንዲህ ያለ የክሕደት ሰነድ አዘጋጅቶ ለውይይት የሚያቀርብ አካልስ በአማራ ሕዝብ ዘንድ እንደ ጠላት እንጂ እንደ መንግሥት ሊታይ ይገባዋል ወይ?

ፋኖ እኮ...‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔ፋኖ እኮ ትምህርቱን፣ ሥራውን፣ እርሻውን ጥሎ ከቤቱ የወጣው ‹‹የመጣብን ጠላት በመደበኛ የጸጥታ ሃይል የሚመለስ ስላልሆነ ተደራጅተህ እራስህን እና ሕዝብህን አስከብር›› የሚል ጥሪ ከመንግሥት ቀርቦለት እንጂ መንግሥትን ለመውጋት አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ በተወሰነ መልኩ ትጥቅ ማግኘት የቻለው የእነ ጌታቸው ረዳን "በከንቱ አትለቅ" የሚል ምክር ችላ ብሎ በክትክታ በትርና በአሮጌ ሚኒሽር ባደረገው ተጋድሎ የአገር አፍራሾችን ክላሽ ማርኮ እንጂ ሰሜን እዝን ወግቶ ወይም ደግሞ ከመከላከያ ሠራዊቱ ቀምቶ አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ ከክልሉ ባለፈ ለኢትዮጵያ ቀጣይነት እራሱን ለመሰዋት የተዘጋጀ ሃይል እንጂ ዜጎችን የማጥቃትም ሆነ አገር የመውጋት ግብ ይዞ የተነሳ የጥፋት ቡድን አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ ሕዝቡንና ክልሉን ከወራሪዎች ከመከላከል ውጭ የትኛውንም ክልልም ሆነ ሕዝብ የመውረር ዓላማ ያለው ጸረ ሰላም ሃይል አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ ከመከላከያ ሠራዊቱና ከልዩ ሃይሉ ጎን ያለምንም ደምወዝ ተሰልፎ ደጀን ሲሆን የሰነበተ የወጣቶች አደረጃጀት እንጂ እንደ ኦ*ግ ወይም እንደ ት*ነግ ታጣቂዎች መደበኛውን የጸጥታ ሃይል ሲያባትል ወይም ደግሞ ሲገድል የከረመ የባንዳዎች ጥርቅም አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ የመንግሥት ጥበቃ ከወራሪ ሃይል ሊያስጥላቸው ባልቻሉ አካባቢዎች ላይ በእራሱ ስንቅና ትጥቅ ተደራጅቶ በመውጣት ከአስገድዶ ደፋሪዎች፣ ከጨፍጫፊዎችና ከዘራፊዎች ጋር ግብግብ ሲገጥም የከረመ የደህንነት ሃይል እንጂ ሕግና መንግሥት ጠፋ ብሎ ንብረት ሲዘርፍና ሕይወት ሲጨፈጭፍ የከረመ የጥፋት ሃይል አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ የመንግሥት አመራር ሕዝባቸውን ለወራሪ አስረክበው ሲጠፉ ቤተሰቡንና ሕዝቡን ለመጠበቅ ያለምንም ሥልጠና ከሞት ቀጠና ውስጥ ዘሎ የገባ የጀግኖች ስብስብ እንጂ፤ የክልሉንም ሆነ የፌደራሉን ሥልጣንና ወንበር መንጠቅ የሚያስብ የፖለቲከኞች ስብስብ አይደለም፡፡ ➔ፋኖ እኮ ለፈጸመው ተጋድሎ ሽልማት ባይሰጠው እንኳን የምሥጋና መድረክ ተዘጋጅቶለት አድናቆት ሊቸረው የሚገባው የሀገር ባለውለታ እንጂ በስብሰባ መድረኮች ላይ ‹‹ኢ መደበኛ ሃይል›› ተብሎ በስጋት መልክ የሚወሳ አልነበረም፡፡ እናም እንዳጠቃላይ... ፋኖ የስጋት ምንጭ ሊሆን የሚችለው ክልሉ ድረስ ሄዶ አማራን የመግደልና የማፈናቀል እቅድ ላለው አካል ብቻ ነው፡፡

የኦሮሚያ ብልጽግና በአገር ደረጃ እያካሄደው ባለው መድረክ ለውይይት ያቀረባቸው ነጥቦች፦ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ 1. አማራ ድላችንን ቀምቶ "ጦርነቱን ያሸነፍኩት እኔ ነኝ" እያለ ስለሆነ ምን እናድርግ? 2. ከአሸባሪው እጅ ላይ መሣሪያ ማርኮ የታጠቀውን ፋኖ ትጥቅ ማስፈታት የሚቻለው እንዴት ነው? 3.አሀዳዊው ሃይል ወደ ሥልጣን እንዳይመጣ ከብሔር ብሔረሰቦች ምን ይጠበቃል? . . . ለማስታወስ ያህል የአሀዳዊነት መገለጫው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት አድርጎ ዜጎችን መግደልና ማፈናቀል ነው። የአማራ ክልል ደግሞ በውስጡ ያሉትን ብሔረሰቦች ባሕልና ማንነት አክብሮ፣ በልዩ ዞን አዋቅሮ፣ በራሳቸው መሪዎች የሚተዳደሩበትን እድል ፈጥሮ፣ እውነተኛ ፌደራሊዝምን ተግብሮ በማስተዳደር ላይ የሚገኝ ፌደራሊስት ክልል ነው። ገባችሁ ወይ እነ ከትክቴ?

የብልጽግና ኢትዮጵያ ስትገመገም አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔በአማራ ደም የመከበር እንጂ እንደማንኛውም ብሔር አማራን የማክበር ፍላጎት የላትም። ➔በአማራ ሕዝብ ስብራትና ጉዳት ላይ ካልሆነ በቀር በእሱ እኩልነትና ተጠቃሚነት ላይ ቀጣይነቷን ማረጋገጥ አትሻም። ➔አማራ የሚባለው ሕዝብ ለእሷ ሕልውና ደሙን ከማፍሰስ ባለፈ እሷን በማፍረስ ሂደት ውስጥ ፋይዳ አለው ብላ አታምንም። ➔በተደጋጋሚ በፈጸመችበት ክሕደትና ጥቃት ተገፋፍቶ በአገር አፍራሽነት የሚሳተፍና በውጫዊ ሃይሎች የሚደገፍ አማፂ አማራ ክልል ውስጥ የተፈጠረ እንደሁ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አትረዳም። ➔እንደ አገር አማራን አሸናፊ ከሚያደርግ ድል ይልቅ "አማራን ጠፊ፣ እርሷን ተሸናፊ" የሚያደርግ ትግል ይመስጣታል። ➔እሷን ለማፍረስ በተነሳ ጠላት ከግማሽ ትሪሊየን ብር በላይ የሆነ ሐብት ከወደመበት ክልል ይልቅ የሰሜን እዝን ወግቶ በለኮሰው ጦርነት የመቶ ቢሊዮን ብር የበጀት ካሳ የሰጠችው አካል አንጀቷን ይበላዋል። ➔በባንዳነት ተግባር ተሰማርተው ሲወጓት ከከረሙት ታጣቂዎች በላይ በክትክታ ዱላ ሲዋጋላት የሰነበተው ፋኖ የስጋት ምንጭ ሆኖ ይታያታል። ➔አማራ ሲዳከም የማገገም ስሜት ይሰማታል። . . . ይህ ሁኔታ ግን ከዚህ በላይ መቀጠል የለበትም። ስለሆነም... በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የምትኖሩ አማራዎች ገንዘባችሁንም ሆነ እውቀታችሁን፤ ጊዜያችሁንም ሆነ ሐሳባችሁን ለተገፊው ሕዝባችሁ ብቻ ልታውሉት ይገባል።

እንዲህ ብለን ነበር 😁
እንዲህ ብለን ነበር 😁

እንደ እስክንድር አይነት በየትኛውም ፈተና የማይሸነፉ ብርቱ ታጋዮች በብዛት ያስፈልጉናል።
እንደ እስክንድር አይነት በየትኛውም ፈተና የማይሸነፉ ብርቱ ታጋዮች በብዛት ያስፈልጉናል።

የሰውየውን ቀጣይ ተግባራት ስንገምት ▬▬▬▬▬▬▬ ➔አማራን እያስገደለ በሰበር ዜና ሕዝቡን ማዘናጋት፤ ➔ከህውሓት ጋር በመደራደር ፋኖን እና የአማራ ልዩ ሃይልን ማስበላት፤ ➔ኢትዮጵያን ስጋት ውስጥ በመክተት "ይሄን ሰውዬ ካልደገፍነው አገራችን መፍረሷ ነው" የሚል ደጋፊ መፍጠር፤ ➔የአማራ ክልልን በጎጥ የሚከፋፍል ግድያ ማቀናበር ➔የእርሱን ክህደት የሚሸፋፍን የሃይማኖት ግጭት መቀስቀስ ➔በወለጋ እና መተከል የኦነግ ሸኔን ጦር በማሰማራት አማራዎችን በጅምላ ማስጨፍጨፍ፤ ➔መከላከያ ሠራዊቱን ስቦ በማውጣትና ፋኖን በማስበላት ጎንደርን ለወራሪዎች ማስረከብ፤ ➔ይህ ሁሉ ካልተሳካ ደግሞ "አፋን ነፍጠኛ እንቤኩ" ብሎ የእነ እንቶኔን ካምፕ መቀላቀል፤ (ጨምሩበት)

አገራቸውን በገንዘብ ሲደግፉና በየመንገዱ ሲሰለፉ የከረሙ ዲያስፖራዎች የመንግሥትን ጥሪ ሰምተው ወደ ኢትዮጵያ መጡ። ክብር የለሹ መንግሥት ግን "ዳውን ዳውን ኢትዮጵያ" ሲሉ የከረሙትን የሚያስፈነጥዝ ውሳኔውን ይፋ ሲያደርግ "በአገራችሁ በዓልን አሳልፉ" ብሎ የጠራቸውን ዲያስፖራዎች የገና ምሽት ስቅለት በማድረግ ነበር። ምን ለማለት ፈልጌ ነው? በደንብ ካሰባችሁበት ውሳኔው የሚያስተምር እንጂ የሚያማርር ሊሆን አይችልም።

የእሸቴና ይታገስ መስዋዕትነት የተሰማ ቀን የፃፍንላቸውን ላስት ወርድ እንዲህ በሚል ሕያው ቃል መካነ መቃብራቸው ላይ አስቀምጠን ተመልሰናል። "ወንበር ላይ ከተዘፈዘፉት አመራሮችና ፖለቲከኞች ይልቅ በ
+2
የእሸቴና ይታገስ መስዋዕትነት የተሰማ ቀን የፃፍንላቸውን ላስት ወርድ እንዲህ በሚል ሕያው ቃል መካነ መቃብራቸው ላይ አስቀምጠን ተመልሰናል። "ወንበር ላይ ከተዘፈዘፉት አመራሮችና ፖለቲከኞች ይልቅ በዚህ መቃብር ውስጥ ያንቀላፉት ጀግኖች በሕይወት አሉ‼️" ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለጀግኖቻችን‼️

‹‹ከተፈቱት ሰዎች ሥም ዝርዝር ውስጥ የእነ አቦይ ስብሓት ሥም ሲካተት፣ የማዕረግ እድገት ካገኙት የጦር መሪዎች መሃከል ሥማችን ሳይካተት ቀረ›› የሚል ቅሬታ የተሰማቸው የሽብር ቡድን መሪዎች በዋጃ
+1
‹‹ከተፈቱት ሰዎች ሥም ዝርዝር ውስጥ የእነ አቦይ ስብሓት ሥም ሲካተት፣ የማዕረግ እድገት ካገኙት የጦር መሪዎች መሃከል ሥማችን ሳይካተት ቀረ›› የሚል ቅሬታ የተሰማቸው የሽብር ቡድን መሪዎች በዋጃ እና ጥሙጋ አካባቢ በለኮሱት ጦርነት ዜጎችን እያፈናቀሉ ነው። እናም ሰላም ወዳዱ መንግሥት ጻድቃንን "ምክትል ፊልድ ማርሻል" ለምን አያደርገውም?

በጌታቸው ረዳ አንደበት ሲቀርብ የነበረው የኢትዮጵያውያን ጥያቄ መልስ አግኝቶ አቦይ ስብሐት ከእስር እንዲፈቱ መወሰኑን ፋስት መረጃ ዘግቧል። እናመሠግናለን ጃል ሆይ‼️😁
+1
በጌታቸው ረዳ አንደበት ሲቀርብ የነበረው የኢትዮጵያውያን ጥያቄ መልስ አግኝቶ አቦይ ስብሐት ከእስር እንዲፈቱ መወሰኑን ፋስት መረጃ ዘግቧል። እናመሠግናለን ጃል ሆይ‼️😁

በገናው ምድር ለወረራ ሲሄዱ በድሮን የታረዱ....
በገናው ምድር ለወረራ ሲሄዱ በድሮን የታረዱ....

ሙሉጌታ ድጋፌ ይባላል፡፡ አማራ ሳይንት ወረዳ ውስጥ ሆስፒታል ቀርቶ ጤና ጣቢያ በሌለበት ዘመን ክሊኒክ ከፍቶ በምጥ የተያዙትን እያገላገለ፣ የታመሙትን እያከመ ወገኑን ሲያገለግል ነበር፡፡ ባሁኑ ሰዓት
+1
ሙሉጌታ ድጋፌ ይባላል፡፡ አማራ ሳይንት ወረዳ ውስጥ ሆስፒታል ቀርቶ ጤና ጣቢያ በሌለበት ዘመን ክሊኒክ ከፍቶ በምጥ የተያዙትን እያገላገለ፣ የታመሙትን እያከመ ወገኑን ሲያገለግል ነበር፡፡ ባሁኑ ሰዓትም በወሎ ምድር የታወቀ አንጋፋ የሕክምና ጠበብትና ባለሃብት ሲሆን በተለይ ደግሞ ዘመናዊውን ሳይንስ ከባሕላዊው ጋር አስማምቶ በሚሰጠው ሕክምናው በመደበኛው የሕክምና አገልግሎት ተስፋ ቆርጠው በደዌ ሲማቅቁ የኖሩ ታማሚዎችን በቀላል ወጪ ከስቃይ በመገላገል ረገድ ከፍተኛ ሥም አፍርቷል። የሚገርመው ነገር ታዲያ ምንም አይነት ሐኪምና የጤና ተቋም ባልነበረበት ዘመን ክሊኒክ ከፍቶ ወገኑን ሲጠቅም የነበረው ይህ አንጋፋ ሀኪም በቅርቡ ደግሞ ወሎን የሚያወድም ወራሪ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ መንግሥታዊው አመራር ደብዛውን ሲያጠፋ ብቸኛ አስተባባሪና አስተዳዳሪ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡ በዚህም ሒደት በአመራር እጦት ሲታወክ የነበረውን ሕዝብ አረጋግቶ፣ ከእራሱ ኪስ በርካታ በጀት መድቦ፣ የወረዳውን ታጣቂዎች በእራሱ መኪና ከተለያዩ ቀበሌዎች አሰባስቦ፣ እንዲሁም መግቢያና መውጫ መንገዶችን አዘግቶ… ወታደራዊ ስምሪት በመስጠት ወገኑን ከጥፋት ሰይፍ ታድጓል፡፡ "ሰው ማለት ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋ እለት" እንደሚባለው… እንደ ዶክተር የቆሰለውን የሚያክም፣ እንደ አመራር ሕዝቡን የሚያረጋጋ፣ እንደ ወታደር ከምሽግ ገብቶ የሚዋጋ፣ እንደ ጦር መሪ ያሰባሰበውን ታጣቂ የሚያዋጋ ዘርፈ ብዙ ጀግና ሆኖ በመገኘት ወገኑን አኩርቷል፡፡ አሁን ደግሞ ከወራሪው ጋር በተረደገው ጦርነት አባወራዎቻቸውን ላጡ ቤተሰቦች የበዓል ሙክት አስሮ በየቤታቸው በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡ እናም በዚህ አጋጣሚ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋዜጠኞች ወደ ስፍራው አቅንተው የአቶ ሙሉጌታ ድጋፌን ጀብዱ ቢተርኩት ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ እንደሚሆን አምናለሁ፡፡

በርካታ አውዳሚ መንጋ አከማችቶ ጎንደርን ለመውረር የተዘጋጀውን አሸባሪ በብዙ መንገድ የጥፋት እቅዱንና ፕሮግራሙን ማክሸፍ እየተቻለ ዋጋ ሲያስከፍለን በኖረው የመከላከል ስልት ተወስነን መጠበቃችን ልክ አይመስለኝም‼️