Assaye Derbie
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie
تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 336 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 651 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 347 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 336 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -104، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 35.99%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.61% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 158 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 808 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.
14 336
المشتركون
-824 ساعات
-327 أيام
-10430 أيام
أرشيف المشاركات
14 336
ለታማኝ በየነ
ከአሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
በባለፈው ቁጣ በሚንጸባረቅበት ድምጽ "ወራሪው ሃይል ወሎ እስኪደርስ ድረስ ምን እያደረጋችሁ ነበር?" በማለት ጠይቀኸን ነበር።
መልሱን ልንገርህ...
"አሁን አንተ የምታደርገውን እያደረግን ነበር!" 😁
ማለትም...
ድግስ ወዳዱ መንግሥታችን "ኢትዮጵያ ሰላም ናት" በሚል ርዕስ ካዘጋጀው ኮንሰርት ላይ ለመታደም ትኬት ቆርጠን እየተጠባበቅን ሳለን ነበር አሸባሪው ሃይል ደሴን የመውረር እቅዱን ሊያሳካ ጉዞ የጀመረው።
አሁንም "ታሪክ እራሱን ይደግማል" እንደሚባለው ኮንሰርቱ ብቻ ሳይሆን ጥቃቱም እንዳይደገም "ዛሬም ለኢትዮጵያችን" በሚል ቃል መስቀል አደባባይ ላይ ልታካሂደው ያሰብከውን ኮንሰርት ቆቦ ላይ ብታደርገው ጥበቃውን እና እስክስታውን ጎን ለጎን ለማስኬድ ይመቸን ነበር። በዚያ ላይ ደግሞ በወራሪ ጥቃት ሲሰቃይ የከረመው ሕዝብም መዝናናት ይቻለው ነበር።
አክባሪህ‼️
14 336
በአርበኛ እሸቴ ሞገስ፣ በአርበኛ መሳፍንት፤ በአርበኛ ሐሰን ከረሙ... ሥም የሚሰየሙ ዩኒቨርሰቲዎችና ኮሌጆች ያስፈልጉናል።
ከዚህ ጋር በተገናኘም ታሪክ ሠርተው በተሰውም ሆነ በሕይወት ባሉ ፋኖዎቻችን ሥም የሚጠሩ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ አውራ ጎዳናዎች... ሊኖሩን ይገባል።
የመቃብር ቦታዎችን ደግሞ በእነ ጌቾና ደፂ ሥም መሰየም ግድ ይላል።
14 336
ያለምንም ተኩስ ለኢቲቪ እና ፋና ጋዜጠኞች እጁን ሲሰጥ የከረመው አሸባሪ በዚህ ሰዓት ደራ ላይ ጦርነት ለኩሶ ሕፃናትና ሴት እየጨፈጨፈ ነው።
14 336
በባለፈው መምሕር ገብረ ኪዳን ማረፋቸውን ሰምተን ስናለቅስ ሰነበትን።
ዛሬ ደግሞ ተስፋዬ ገብረ አብ ማረፉን ከውብሸት ታየ አንደበት ሰምተን በእጅጉ አዘንን!
ደግ አይበረክትልሽ ተብላ የተረገመች አገር 😭😂😭
14 336
የአማራን ምድር የዝሆኖች መራገጫ ቦታ እንዲሆን የፈረደበት ማን ነው? አማራ ሰላም አይናፍቀውም? እርሻ አያርስም? ልጆቹን አያስተምርም? ነግዶ አይበላም? በቃህ ማለት በቃህ ነው‼️😡
14 336
የመንግሥት ውሳኔ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ሥጋት አይሁን እንጂ
ለአራት ኪሎ ዙፋን- ለያዝኩት ሥልጣኔ
አፈር ልሶ መጥቶ-
አማራን ቢያወድመው- ምን አገባኝ እኔ?
አላማጣ ኮረም፣
እንዳሻው ራያ፣ እንዳሻው ወልቃይት
አዲስ አበባ እንጂ-
አዲ አርቃይ አይደለም-የኔ ቤተመንግሥት
ያም ሆኖ ግን ሕዝቤ-
ካሰብክበት ሳይደርስ- ትግሉ ሲጠናቀቅ
ከአሸባሪ ጋር-
ልደራደር መስሎህ- ከቶ እንዳትጨነቅ
ዘመቻው ቆመ እንጂ-
ከጁንታዎች ጋራ- መቼም አይኖርም እርቅ
ወንበሬን ሳይነካ
ምን አገባኝ ምድሩ- በደም ቢጨማለቅ፡፡
የወገን ጦር ደግሞ-
ይሄን ያህል ከሄድክ- ፍትሕን ፍለጋ
ባልታሰበ ቅጽበት-
አማራን ሊያወድም- ካንተ ጋር ሊዋጋ
ሲደራጅ ሰንብቶ-
እስኪመጣ ድረስ- ሽብርተኛው መንጋ
ትዕዛዜን አክብረህ- ባለህበት እርጋ፡፡
ተራው ሕዝቤ ደግሞ-
ሰላምን አትናፍቅ- አትጓጓ ለድል
ይልቅ ዝግጁ ሁን-
ለሌላ ዙር ፍልሚያ- ለሌላ ዙር ትግል
የኔ ሥልጣን እና-
ያንት የኑሮ ኡደት-እንዲህ ነው የሚቀጥል!
14 336
ኢትዮጵያን ለመከራ የዳረጋት አረመኔው ጠላቷ ሳይሆን ይቅር ባይ መንግሥቷ ነው!
ለማስረጃም ያህል....
ኢትዮጵያን ሲዘርፍና ዜጎቿን ሲጨፈጭፍ 27 ዓመት የኖረው አረመኔ በወጣቶች ተጋድሎ ከሥልጣኑ ተነሳ፡፡
ይቅር ባዩ መንግሥትም እኒህን ወንጀለኞች ወደ እስር ቤት በመላክ ፈንታ ወደ ቤተ-መንግሥት ጠርቶ ከጋበዛቸው በኋላ በክብር ሸኛቸው፡፡
አረመኔዎቹም ወደ መቀሌ ከሄዱ በኋላ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ከበጀት ውጭ ምንም አይነት ግንኙነት የለንም›› ብለው ሦስት ዓመት ሙሉ ኢትዮጵያን ሲያቃጥሏትና በደም ሲያጨቀዮት ኖሩ፡፡
አርቆ አሳቢው መንግሥትም ፍጹም በተረጋጋች ክልል ውስጥ ተቀምጦ አገር የሚያቃጥለውን ድርጅትና መሰሪውን ፕሬዝዳንት ሊያወግዘው ሲገባ ‹‹ደብረ ጽዮንን ልናግዘው ይገባል›› እያለ ሦስት ዓመት ሙሉ እሳት በማጥፋት አሳለፈ፡፡
አረመኔው ቡድንም ‹‹ከክልሌ ያለው ሠራዊት ተጠሪነቱ ለፌደራል መንግሥት ሳይሆን ለክልሉ መንግሥት ነው›› የሚል አዋጅ ካጸደቀ በኋላ ባንዱ ሌሊት ሰሜን እዝን በመጨፍጨፍ በቅራቅርና በራያ በኩል ወረራ ፈጸመ፡፡
ደጉ መንግሥትም በቴሌቪዥን ቀርቦ ስለተፈጸመው ክህደት ካብራራ በኋላ አገራዊ ጥሪ አቀረበ፡፡
የአማራና የአፋር ልዩሃይልና ታጣቂም ጥሪውን ተቀብሎ ከመከላከያ ሠራዊታችን ጎን በመሰለፍ ከፍተኛ ዋጋ ከከፈለ በኋላ አሸባሪውን ከመቀሌ ወደ ቆላተንቤን መሸኘት ቻለ፡፡
አብዛኛው የጁንታው ታጣቂም ከባድ መሳሪያውን በቤተ-እምነቶች ውስጥ ከደበቀ በኋላ በሲቪል ልብስ ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀላቀለ፡፡
በዚያች ክልል የሚጨክን ልብ የሌለው የፌደራል መንግሥታችንም የመቶ ቢሊዮን ብር በጀት ከደለደለ በኋላ ወደ ምርጫ ዝግጅት ገባ፡፡
አረመኔው ቡድንም ይሄንን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ሁለተኛውን ክህዴት በሠራዊታችን ላይ ሰነዘረ፡፡
ጨዋው መንግሥትም የተናጠል ተኩስ አቁም አድርጎ ደጀን ፍለጋ ሠራዊቱን ስቦ አስወጣ፡፡
እብሪተኛው አሸባሪም ‹‹የማዋርደው ብሔር፣ የማፈርሳት አገርና በቁጥጥር ስር የማውለው አመራር አለኝ›› በሚል ፉከራ አማራና አፋር ክልልን ወርሮ በዋጋ የማይተመን ሰብዓዊ ጉዳትና ወደ ግማሽ ትሪሊዮን የሚጠጋ ሐብት ማውደምና መዝረፍ ቻለ፡፡
ይሄንን አድርጎ ሲጨርስ ‹‹ከዚህ በኋላ የአራት ኪሎን ወንበር መቆጣጠር እንጂ መደራደር አይታሰብም›› በሚል ፉከራ ወደ ሸዋ ማምራት ጀመረ፡፡
መንግሥትም ሳይወድ በግዱ በሚዲያ ብቅ ብሎ ‹‹ ይሄን አሸባሪ ቡድን በመደበኛ ሠራዊት ማሸነፍ እንደማይቻል ከገለጸ በኋላ ‹‹እኔ ወደ ግንባር እያመራሁ ስለሆነ አገር መታደግ የምትፈልጉ ሁሉ ተከተሉኝ›› የሚል ጥሪ አቀረበ፡፡
እኒያ የፈረደባቸው የሁለት ክልል ሕዝቦችም ከመከላከያ ሠራዊቱ ጋር ተሰልፈው ከፍተኛ ዋጋ ከከፈሉ በኋላ ወረራውን መቀልበስ ቻሉ፡፡
አረመኔው ቡድንም ለሰላም ሲል ከአፋርና ከአማራ ክልል ሠራዊቱን ማስወጣቱን ገልጾ ውይይት ይጀመር ዘንድ ጥሪ አቀረበ፡፡
ይቅር ባዩ መንግሥትም የአሸባሪውን ጦር እግር በእግር የመከታተል ዓላማ እንደሌለው ገልጾ ስለ ድርድር ያወራ ጀመር፡፡
ምን ልልህ ፈልጌ ነው?
በብልጽግና ዘመን እጅግ በጣም ቀላሉ ነገር ተከዜን ተሻግሮ በሆነ ሕዝብ ላይ አረመኔያዊ ተግባር ፈጽሞ መመለስ ሲሆን የማይቻለው ደግሞ ይሄንኑ ወንዝ አልፎ ወንጀለኛን መቆጣጠር ነው።
‹‹ክቡር አሸባሪ-
ጨፍጭፋ የምትሸሽ- ዘርፋ የምትከስስ
የተረገመ ሕዝብ-
ሲታረድ ሰንብቶ- ባዶ እጅ የሚመለስ›› እንደማለት…
14 336
ወረራ ፈጽሞ በርካታ ሴቶችን ከደፈረውና ንጹሐንን ጨፍጭፎ በጅምላ ከቀበረው አሸባሪ በላይ ከዚህ የሽብር ድርጅት ጋር ተደራዳሪ ሆኖ የሚቀርብ አካል በአማራና አፋር ሕዝብ ዘንድ እንደ ትልቅ ወንጀለኛ ይቆጠራል!
14 336
በዚህ ምሽት የተፈጸመ ጀብዱ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ወራሪው ሃይል ወረራ ከፈጸመባቸው አካባቢዎች ተጠራርጎ በወጣ ማግሥት ከቤቴ ተቀምጣ ነገር ስትፈልገኝ የከረመቺው አደገኛ ጁንታ ‹‹የተፈጨው ዱቄት ስላለቀ ጤፍ የምገዛበት ገንዘብ እፈልጋለሁ›› እያለች የሆነ ፓውደር ፊቷ ላይ ትነሰነስ ጀመር፡፡
ያን ጊዜም መኖሪያ ቤቴ ውስጥ ወረራ ካልተፈጸመ በቀር በባለፈው ወር የተፈጨው ዱቄት በአንድ አባወራ ተበልቶ እንደማያልቅ እርግጠኛ ሆኜ ‹‹አንቺ ግን ሚስት ነሽ ወይስ ህው*ሓት?›› በማለት ስጠይቃት ‹‹ዱቄቱ ያለቀው ጋግሬው ሳይሆን ልክ እንደዚህ ስለምደፋው ነው›› በማለት ከጓዳ ያለውን ማቡኪያ ብድግ አድርጋ ሊጡን ደፋችው፡፡ ከዚህ ባለፈም የቤቴን እቃ እየሰባበረች ከፍተኛ የሆነ ቁሳዊ ውድመት ትፈጽም ያዘች፡፡
ይሄንንም ጥፋት ፈጽማ ስትጨርስ ወደ ሳሎን መጥታ ‹‹ከኪስህ ያለውን ገንዘብ ሙልጭ አድርገህ አምጣ›› ስትለኝ ‹‹አንቺ ሴትዮ ከልቤ ያለው ትግስት ተሟጥጦ አልቆ ዱቄት የሆነ እንደሁ እርምጃዬ ከባድ ስለሚሆን ብታርፊ ይሻልሻል›› በማለት አስጠነቀቅኳት፡፡
እሷ ግን ማስጠንቀቂያን ችላ ብላ ወደ ጾታዊ ትንኮሳ በመግባት ‹‹አንት ፎጣ ለባሽ›› እያለች የለበስኩትን ፎጣ ትገትተው ጀመር፡፡ በዚህም ጥቃቷ ከሳሎን ተፈናቅዬ ወደ መኝታ ቤት ሳመራ ‹‹ወዴት ነው የምትሄደው አንተ ተስፋፊ ኤሊት›› እያለች ስትከተለኝ ‹‹ከዚህ መኝታ ቤት መውጣት ዘሎ እንደመግባት ቀላል ስላልሆነ አርፈሽ ተቀመጪ›› ብያት ነበር፡፡
በእብሪት የተወጣጠረችው ይህቺ እብሪተኛ ጁንታ ግን ምክሬን በመቀበል ፈንታ ‹‹አንተ ጨፍላቂ የጨፍላቂ ልጅ›› እያለች በሩን በእርግጫ ስትደበድብ ከቆየች በኋላ በርግዳው ገባች፡፡ ያን ጊዜም እጇን ለቀም አድርጌ ካልጋ ላይ ካጋደምኳት በኋላ 85 ኪሎ በሚመዝን ሰውነቴ ልጨፈልቃት ስል ገላዋ የሚታረስበትን ብልት እንደ ወሎ መሬት ከመዳፏ ስር አስገባችው፡፡ ይሄም አልበቃ ብሏት አምርቶ የሚቀልባትን የዘር ፍሬ አንቃ ‹‹እንዲህ ነን እኛ የግንቦት ሃያ ፍሬዎች›› እያለች ስትገትተው እንደ ደጋን ወደኋላ ተቀልብሼ ‹‹እንደራደር›› በማለት ለምኛት ነበር፡፡
ይሄንንም የድርድር ጥያቄዬን ‹‹ባለቀ ጦርነት ላይ ከማን ጋር ነው የምደራደረው?›› በሚል መልስ ውድቅ ካደረገችው በኋላ ‹‹ደቁሶም›› እያለች ክንዷን ስታበረታው ‹‹የክተት ጥሪ›› አውጄ ወደ ፍልሚያ ገባሁ፡፡
በቅጽበት ዘመቻም ጨምድዳ የያዘችውን እቃ ከእጇ ፈልቅቄ ወደ ቀድሞ ይዞታው በመመለስ ዲሽቃ አደረግኩት፡፡
ከዚያም ወደ ማጥቃት እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቼ ከደረቷ ያለውን የወተት ከረጢት እንደ አፋርና ወሎ መሬት ከመዳፌ ሳስገባው ‹‹አውቄ ነው የለቀቅኩልህ›› ብላ ሽንፈቷን ካስተባበለች በኋላ ‹‹በማንም ፎጣ ለባሽ ምሽጌ አይደፈርም›› በሚል መፈክር ጋሽናዋን በሁለት መዳፏ አንቃ ትታገል ያዘች፡፡
ለዚህም ንግግሯ ‹‹ቲሽ! ቀሚስ ለባሽ›› የሚል መልስ ከሰጠኋት በኋላ እንደ ድሮን ከላይ ሆኜ በሚሳኤል ስደበድባት ቆየሁ፡፡ ከእልህ አስጨራሽ ትግል በኋላም ጋሼናዋን ሰባብሬ ስገባ ሌላ ምሽግ ያላት ይመስል ‹‹ጋሼናን የለቀቅኩልህ ስትራቴጂክ ቦታ ስላልሆነ ነው›› ከሚል ማስተባበያ ጋር እንደ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ ዓይኗን ጨፈነች፡፡ እንደ ሥዩም መስፍን አንገቷን አዘነበለች፡፡
ከዚያም የቀራትን ብቸኛ ጉልበት በመጠቀም ጌታቸው ረዳን በሚያስታውስ አንደበት ‹‹እኔን በሃይል ማስገበር ስለማይቻል ከአልጋው ወርደን በጠረጴዛ ዙሪያ እንደራደር›› በማለት ከተናገረች በኋላ እንዲህ ብላኝ አባይ ጸሐየን ሆነች፡፡
‹‹ክብርን ሞጎስን ንጀጋኑ ሰማዕታትና›› 😆
14 336
➔ወራሪው መንጋ ፋብሪካችንን ነቅሎ ወስዶታል፡፡ እኛ ግን በፒንሳና ካቻቪቴ እየተጨቃጨቅን ነው፡፡
➔አሸባሪው ቡድን እንደ ወልድያ ያሉ ትልልቅ ከተሞቻችንን ነጥቆናል፡፡ እኛ ግን በማንቆርቆሪያ እየተካሰስን ነው፡፡
➔ርሐብ*ተኛው መንጋ በእኛው ተሸከርካሪ ጭኖ ዱቄታችንን እና እህላችንን ወስዶታል፡፡ እኛ ግን ‹‹ጆንያውንና ጎማውን ማን ወሰደው›› በሚል ርዕስ ሌባና ፖሊስ እየተጫወትን ነው፡፡
➔ወራራው ሃይል መደብሮቻችንን እና ተቋማቶቻችንን ዘርፎ ባዷቸውን አስቀርቷቸዋል፡፡ እኛ ግን የቤት ችግራችንን በውስጥ መፍታት አቅቶን ክልሉን ለመዝረፍ በተዘጋጀው ሃይል ፈንታ "ካርቶኑን የወሰደው ማን ነው›› በሚል አጀንዳ እኝኝኝኝኝ እያልን ነው፡፡
እናስ....
እንደ እኛ አይነት ሐሞት የለሽ ውዳቂ ልጅ ያፈራ ሕዝብ ተዋርዶ ከመኖር ውጭ ምን አማራጭ አለው?
14 336
😁😁
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ድፍን ወሎን እና ሸዋን ከወረረ በኋላ ደብረ ሲና ላይ ሆኖ "የዘጋችሁትን መንገድ ከፍታችሁ ወደ አዲስ አበባ አሳልፉኝ" እያለ ሲቆጣን የነበረ አሸባሪ ሰሜን ወሎ ላይ ቁሞ "ወደ መቀሌ አሳልፉኝ" እያለ ሲለማመጥ ከማየት በላይ ምን የሚያስቅ ነገር አለ?
የሆነው ሆኖ የዛሬው የድል ዜና "80 ሺህ ጠላት ገድ*ለን ላሊበላን ተቆጣጥረናል" የሚል ሆኗል።
በቀጣይ ደግሞ "የኢትዮጵያን ሠራዊት ሙሉ በሙሉ ደምስ*ሰን መቀሌ ገብተናል" በሚል ሰበር ዜና "ቶኩስ ቶኩስ ቶኩስ" እየተባባሉ ከበሮ ሲመቱ እናያቸው ይሆናል። 😁
14 336
ሊወደስ የሚገባውን የፋኖ ሥም ለማራከስ ለሚሞክሩ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔የፋኖ መገለጫ የተዘረፈን ሐብት ለማስመለስና በከንቱ የፈሰሰን የወገንን ደም ለማ*በስ በሚደረግ ትግል ውስጥ ቀዳሚ ሆኖ መገኘት ነው፡፡
➔የፋኖ ዓላማ የእራስን ሕይወት በሚያሳጣ ፍልሚያ ውስጥ ገብቶ ሕዝብን አንገት ከመድፋት፣ አገርን ከፍርሰት፣ ተቋማትን ከውድመት መከላከል ነው፡፡
➔የፋኖ አቋም የወራሪን ግብዓተ መሬ*ት ፈጽሞ የተወረረ አካባቢን ነጻ ማውጣት ነው፡፡
➔የፋኖ የትግል ግብ አስገድዶ ደፋሪን፣ ዘራፊን እና ጨፍጫፊን… ደ*ቁሶ ፍትሕን እና ነጻነትን ማረጋገጥ ነው፡፡
➔ፋኖነት ማለት በእራስ ፍላጎትና በእራስ ሕይወት ከመከላከያ ሠራዊታችንና ከልዩ ሃይላችን ጎን ተሰልፎ የሕዝብን ስጋት መቅረፍ ነው፡፡
➔ፋኖነት ማለት በግብረ ገብነት፣ በጀግንነት፣ በእንባ አባሽነት፣ በሕዝብ ጠባቂነት… መታወቅ ማለት ነው፡፡
እናም ከእነዚህ መስፈርቶች በተጻራሪ ተሰልፎ የተገኘ አካል ‹‹ባንዳ›› ተብሎ ሊጠራ፣ ሊከሰስ፣ ሊወቀስ፣ ሊወነጀል ይችላል እንጂ ‹‹ፋኖ›› በሚል መጠሪያ ሊከሰስ አይገባውም፡፡
የወራሪውን እግር ተከትለው በተለያዩ ከተሞች ሲዘርፉ፣ ሲመዘብሩ፣ ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩና አሁንም ድረስ እየፈጸሙ ያሉ ወጣት ባንዳዎችን ‹‹ፋኖዎች›› የሚል ሥም ሰጥቶ ከመከላከያችን እና ከልዩ ሃይላችንን ጎን ተሰልፎ የሕይወት መስዋዕትነት የሚከፍለውን ‹‹የጀግኖች ስብስብ›› ለመወንጀል መሞከር ልክ አይደለም፡፡
‹‹ወሎ ምድር የሚኖር ወገኔ ተጠቃብኝ›› ብሎ ከጎንደር፣ ከሸዋ፣ ከጎጃም ድረስ ተጉዞ ደሙን እና ላቡን ሲያፈስስ የከረመውን ፋኖ ማማስገንና ማወደስ ሲገባ በፌክ አካውንት ተደብቆ ‹‹ከተማዬን ዘረፈብኝ›› እያሉ በመክሰስ የፋኖን ውለታ ማርከስም ሆነ ወሎን ከሞተለት ወገኑ ለይቶ ሲገድለው ከሰነበተው ሃይል ጋር ማቧደን የትም አያደርስም!
14 336
ሊወደስ የሚገባውን የፋኖ ሥም ለማራከስ ለሚሞክሩ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔የፋኖ መገለጫ የተዘረፈን ሐብት ለማስመለስና በከንቱ የፈሰሰን የወገንን ደም ለማ*በስ በሚደረግ ትግል ውስጥ ቀዳሚ ሆኖ መገኘት ነው፡፡
➔የፋኖ ዓላማ የእራስን ሕይወት በሚያሳጣ ፍልሚያ ውስጥ ገብቶ ሕዝብን አንገት ከመድፋት፣ አገርን ከፍርሰት፣ ተቋማትን ከውድመት መከላከል ነው፡፡
➔የፋኖ አቋም የወራሪን ግብዓተ መሬ*ት ፈጽሞ የተወረረ አካባቢን ነጻ ማውጣት ነው፡፡
➔የፋኖ የትግል ግብ አስገድዶ ደፋሪን፣ ዘራፊን እና ጨፍጫፊን… ደ*ቁሶ ፍትሕን እና ነጻነትን ማረጋገጥ ነው፡፡
➔ፋኖነት ማለት በእራስ ፍላጎትና በእራስ ሕይወት ከመከላከያ ሠራዊታችንና ከልዩ ሃይላችን ጎን ተሰልፎ የሕዝብን ስጋት መቅረፍ ነው፡፡
➔ፋኖነት ማለት በግብረ ገብነት፣ በጀግንነት፣ በእንባ አባሽነት፣ በሕዝብ ጠባቂነት… መታወቅ ማለት ነው፡፡
እናም ከእነዚህ መስፈርቶች በተጻራሪ ተሰልፎ የተገኘ አካል ‹‹ባንዳ›› ተብሎ ሊጠራ፣ ሊከሰስ፣ ሊወቀስ፣ ሊወነጀል ይችላል እንጂ ‹‹ፋኖ›› በሚል መጠሪያ ሊከሰስ አይገባውም፡፡
የወራሪውን እግር ተከትለው በተለያዩ ከተሞች ሲዘርፉ፣ ሲመዘብሩ፣ ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩና አሁንም ድረስ እየፈጸሙ ያሉ ወጣት ባንዳዎችን ‹‹ፋኖዎች›› የሚል ሥም ሰጥቶ ከመከላከያችን እና ከልዩ ሃይላችንን ጎን ተሰልፎ የሕይወት መስዋዕትነት የሚከፍለውን ‹‹የጀግኖች ስብስብ›› ለመወንጀል መሞከር ልክ አይደለም፡፡
‹‹ወሎ ምድር የሚኖር ወገኔ ተጠቃብኝ›› ብሎ ከጎንደር፣ ከሸዋ፣ ከጎጃም ድረስ ተጉዞ ደሙን እና ላቡን ሲያፈስስ የከረመውን ፋኖ ማማስገንና ማወደስ ሲገባ በፌክ አካውንት ተደብቆ ‹‹ከተማዬን ዘረፈብኝ›› እያሉ በመክሰስ የፋኖን ውለታ ማርከስም ሆነ ወሎን ከሞተለት ወገኑ ለይቶ ሲገድለው ከሰነበተው ሃይል ጋር ማቧደን የትም አያደርስም፡፡
14 336
እለታዊ መረጃዎች
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔ከወልዲያ ወደ መቀሌ የሚወስደውን መንገድ በቆረጣ ገብቶ የወገን ጦር ተቆጣጥሮታል፡፡
➔በሌላ ግንባር ደግሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት በርካታ ስትራቴጂክ ቦታዎችን ተቆጣጥሮ በሁለት አቅጣጫ ወደ ሀራ እና መርሳ በመገስገስ ላይ ይገኛል፡፡
➔ስለሆነም መውጫ ቀዳዳ ያጣው አውዳሚ መንጋ ቁስለኛውንና ከባድ መሣሪያውን እየጣለ እግሩ ወዳመራው አቅጣጫ በመፈርጠጥ ላይ ይገኛል፡፡
➔ይሄንንም የተረዳው ኣይተ ጌታቸው ረዳ (ቦርቧሬ) ‹‹ጠላታችን›› የሚለውን ሕዝብ ‹‹ወንድማችን›› በሚል ሥም ጠርቶ ‹‹ሂድና ወንድሞችህን ጨፍጭፈህ ዝረፋቸው የሚል ትዕዛዝ ሰጥተን የላክነውን ሠራዊት ጨዋዉ የአማራ ሕዝብ እንደ ወንድም ተቀብሎ ሲወድም በመክረሙ ላመሰግነው እወዳለሁ›› ብሏል፡፡
ከዚህም ፖስት ስር እንዲህ የሚል ኮሜንት ተሰጥቶታል፡፡
‹‹ወንድሞቻችንን - መጥተን ለመጠይቅ
በራያ እና ሽሬ -ትግራይ ስለምንዘልቅ
ወሬውን ተውና…
ዱቄቱን አቡክተህ- ሊጡን ጋግረህ ጠብቅ፡፡››
14 336
የደረሰብን ጉዳትና የተከፈለው መስዋዕትነት የዩ ቲዩብ ሰበር ዜና ሆኖ መቅረት የለበትም
▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ሲዘርፍ ከርሞ ‹‹ተዘረፍኩኝ›› ፣ ሲጨፍጭፎ ሲንብቶ ‹‹ጀኖ ሳይድ ተፈጸመብኝ›› በሚል ክሱ የሚታወቀውን አሸባሪ የሕግም ሆነ የታሪክ ተጠያቂ ለማድረግ ብሎም በወቅቱ የደረሰውን ሁሉ አሁን ላለውም ሆነ ለሚመጣው ትውልድ ለማስተላለፍ የሰነድ ማስረጃ ትልቅ አስተዋጾ አለው፡፡
በዚህም መሠረት ወራሪው ቡድን ያደረሰብን ጉዳትና ጀግኖቻችንን የከፈሉት መስዋዕትነት የአንድ ሰሞን የዩቲዩብ ሰበር ዜና ሆኖ መቅረት የለበትም›› በማለት ሰሜን እዝ ተጠቅቶ ጦርነቱ ከተለኮሰበት ጊዜ አንስቶ በርካታ መረጃዎችን ስናሰባስብና ስንጽፍ ነበር፡፡ ባሁኑ ሰዓትም በሸዋ ምድር በመንቀሳቀስ የደረሰውን ጉዳት በመመልከት ላይ እንገኛለን፡፡
ሆኖም ግን እንደ አጠቃላይ ወረራ በተፈጸመባቸው (በአፋር፣ በራያና ቆቦ፣ በሰሜን ወሎ፣ በደቡብ ወሎ፣ በደቡብ እና ሰሜን ጎንደር፣ በላስትና ሰቆጣ አካባቢዎች የደረሱትን ጉዳቶች ለማጠናቀር ብሎም የተከፈለውን መስዋዕትነት የሚዘክር መጽሐፍ ለማሳተም የትራንስፖርትም ሆነ የሕትመት ወጪው እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ የሁላችንም ትብብር ያስፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት ይህ ታሪካዊና እጅግ አስፈላጊ መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ወደ ህትመት ይገባ ዘንድ በተለያዬ መንገድ አሻራችሁን ማስፈር የምትፈልጉ ከታች ያስቀመጥኩትን ሊንክ በመጫን በኢንቦክስ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ከመጽሐፉ የሚገኝ ገቢ ለሰማዕታት ልጆች የሚውል ይሆናል፡፡
https://www.facebook.com/assaye.derbie
14 336
ከመካነ-መቃብራቸው ላይ እንዲህ ብላችሁ ጻፉበት!
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ከትግራይ ተነስቶ፥
ሸዋን የወረረ፥ ጨፍጫፊ ዘጠኝ ሞት፤
‹‹አንዱን ግባ በለው››
ብሎ የሚያስተናግድ፥ ሰው ያገኘ መስሎት፤
ይታገስ ደቦሉን
እሸቴ አንበሳውን፥ ሊማርክ ሲለፋ፤
በሕያዋን ክንዶች
በጅምላ ተገድሎ- ሞት እራሱ ጠፋ፡፡
እናም ከዚህ ስፍራ
ተንቆ ተዋርዶ፥ ከአፈር ስር የዋለ፤
ዘጠኝ ሞት እንጂ
የይታገስ አባት፥ እሸቴም አይደለ፡፡
14 336
በምክንያት የለሽ ጥላቻ ይሄን ሁሉ አረመኔያዊ ድርጊት ከፈጸሙብን በአማራ ልብ ውስጥ የተፈጠረው ምክንያታዊ ቁጣ ምን ሊያስከትል እንደሚችል መገመት አይከብድም።
ትግሬ ሆነው የተፈጠሩበትን ቀን እስኪረግሙ ድረስ እንበቀላቸዋለን።
14 336
ላሊበላ ትዝ እንዳይለን
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
የጦር ሠራዊቱ- ትዕዛዝ ተቀብሎ- ነፍጡን እስኪያነሳ
ቅዱስ ላሊበላን- ሰቆጣ ወልዲያን- ወሎን የሚያስረሳ
አእምሮ የሚያባትል- ልብን የሚሰልብ- ትኩረት የሚነጥቅ
በሆነ ጉዳይ ላይ- ሰበር ዜና ብለህ- መንግሥት ሆይ ልቀቅ፡፡
አገሩ ጸጥ ሲል- የሚሰማው ጩኸት- በጣም ነው የሚጨንቅ፡፡
እባክህ ጃን ሆይ- በሌላ አደባባይ- በሌላ አለባበስ
ከሹማምንቱ ጋር- እንደ አዲስ ደግሰህ- ከእንደገና ንገሥ
ቲቪውን ተውና- መንገዱን ዘጋግተህ- ኢሳያስ ጋር ደንስ
እንደ ሊጥ ሞሃቻ- ለባንዳ ወራሪ- ያስረከብከው መቅደስ
ዘፈኑ ሲቆም ነው- ትዝ ትዝ እያለኝ- እራሴን የምወቅስ፡፡
ወይ ደግሞ ካልሆነ- ከዚህ እና ከዚያ- ባንድራ ምረጡ
እንትና ተሽሮ- እገሌ ተሾመ- የሚል አጀንዳ አምጡ
ምክንያቱም…
ከወራሪ አፈሙዝ- ወገኑን ማዳኛ- የቸገረው አቅም
ጫጫታው ሲያባራ- ጸጥ ሲል አይወድም፡፡
እዚያ የጁ ምድር- እኅቱን የሰጠ- ለአረመኔ መንጋ
ራያና አዘቦ- ወገን ያስቀመጠ- ከጅቦች መንጋጋ
ሰቆጣ ጎንደር ላይ- ሕጻን የሚያስገርፍ- በርሐብ አለንጋ
ነፍሱን የሚያሻቅል- ለቅሶ ይሰማልና- አገር ሲረጋጋ፤
እባክህ መንግሥት ሆይ-
ድምጹን ጨምር እንጂ- ዘፈኑን አትዝጋ፡፡
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
