cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

The Christian News

ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት። @TCNEW

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
5 010
المشتركون
+824 ساعات
+367 أيام
+10630 أيام
توزيع وقت النشر

جاري تحميل البيانات...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
تحليل النشر
المشاركاتالمشاهدات
الأسهم
ديناميات المشاهدات
01
#አዲስ መጽሐፍ #በቅርብ #ቀን... ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተ #ድንቅ የአማርኛ መጽሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት በዘላለም መንግስቱ ተዘጋጅቶ በቅርብ ቀን ወደ አንባቢያን ይደርሳል። 23 ዓመታት የፈጀው #ይህ #ድንቅ መጽሀፍ በቅርብ ቀን በአዲስ አበባ ሰኔ 15 2016 በኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ (ETC) የምስጋና ጊዜ ከጠዋቱ 4 እስከ 6 ሰዓት በድምቀት ይመረቃል።
7051Loading...
02
#የዛሬ -ሃምሳ #ዓመት #እኔ #በጌታ ምሪት #ወደ ባሌ ጎባ ገብቼ ቤተክርስቲያን ለመትከል ቤት የተከራየውበት ቀን #በሮቤና በአጋርፋ ይሠሩና ይኖሩ ከነበሩት ሁለት ወንድሞች #አያና መኳንንና #ከአባተ ወላኒዎሰ ጋር ከሮቤ አንድ ታጣፊ አልጋ ከነፍራሹ በ28 ብር ገዝተን ቤቱን ደግሞ በ10 ብር ተከራይተን የኪራይ ውል ፈጸምን። ኪራዩን ከሁለቱ ወንድሞች ማን እንደከፈለ ትዝ አይለኝም ። ቤቱ ወንዝ ደር ከመሆኑም በላይ ንፋስ ያስገባል እና በጣም ይበርዳል። በተለይም በማያውቁት አገር ሌሊቱን ለብቻ ማደር እንዴት ያስፈራል። ሃምሳ ዓመት ወደ ኋሊት አሰብኩ ። የአምላኬ ምህረትና ማደን ቸርነቱም ገረመኝ ደነቀኝም። ስሙ ለዘለዓለም የተባረከ ይሁን ። 🙏🙏🙏 ከመጋቢ ጻድቁ አብዶ (የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ኅብረት ፕረዚዳንት) ገጽ የተወሰደ
9642Loading...
03
በመቱ የሙሉ #ወንጌል አማኞች #ላይ ደረሰ የተባለው ድብደባ እንዲጣራ የአብያተ ክርስቲያናት ኅብረቱ ጠየቀ። #እሁድ ግንቦት 25 በመቱ ከተማ ለወንጌል ስርጭት በወጡ ክርስቲያኖች ላይ በፖሊስ እና ሚሊሻዎች ድብደባ ተፈጽሟል። ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ወገኖች መካከል አስተያቷን ለአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የሰጠችው ኤደን ግርማ እንዲህ ብላለች። ኤደን ግርማ፣ ጥቃት የደረሰባት “የእሁድ አምልኮ ጨርሰን ለወንጌል ስርጭት ሶሪ ዳቦ የሚባልበት አካባቢ ስንደርስ ፖሊሶችና ሚልሻዎች በመኪና መጡ። መሬት ላይ ተቀመጡ ካሉ በኋላ፣ የተወሰኑ ወጣቶች ወደ ፖሊስ ጣብያ ወሰዱን። አመሻሽ ላይ ከአንዱ አመራር ጋር ፖሊስ ጣብያው አካባቢ መሬት ተቀመጡ ብሎ እያወራን፣ ፖሊሶችና ሚሊሻዎች ድብደባ ጀመሩ። እኔ ጭንቅላቴን ተመቼ ስደማ፣ ሌሎችም በጣም ተጎድተው ወደ ሆስፒታል ለህክምና ተወስደናል።” ስትል ተናግራለች። #ቄስ ደበላ ያደታ፣ የኢሉባቦር ዞን ወንጌላዊያን አብያተ ክርስትያናት ህብረት ሰብሳቢ በበኩላቸው “እኛ ህገ መንግስቱ በሚሰጠን መብት መሰረት እምነታችንን የማካሄድ መብት አለን። ከመንግስት ጋርም በሚያስፈልጉ ነገሮች ዙርያ በትብብር ስንሰራ ቆይተናል። መንግስት እንደዚህ ያደርጋል የሚል እምነት ባይኖረንም፣ የመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ሰዎች ግን ይሄንን እንዳደረሱ በትክክል እናውቃለን። ስለዚህ ሁኔታው በትክክል እንዲታራ እንጠይቃለን።” ብለዋል። አቶ ተሻለ ኤጄርሶ፣ የመቱ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው “ከሳምንት በፊት ለነበረው ስብከተ ወንጌል ፍቃድ የተሰጠ ቢሆንም፣ እሁድ ግንቦት 18 ሲደረግ ለነበረው የወንጌል ስርጭት የተሰጠ ፍቃድ የለም። አላስፈላጊ ድብደባና ግጭት ከፖሊስ ዘንድ መድረሱን ተመልክተናል። ከጸጥታ አካላት ጋርም ይሄንኑ ጉዳይ በተመለከተ ምርመራ እየተካሄደ ነው።” VOA Amharic
1 5292Loading...
04
ምዕመናን #ወደ ፕሮግራሙ እንዳትሄዱ። "በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም የሚደረገው ኮንፈረንስ እውቅና የለዉም" ስትል የወላይታ ቀጠና ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ገለፀች። ቤተክርስቲያኒቱ ከሰኔ 01 እና 02/2016ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም CJ ኮንፍራንስ ለማድረግ በሶሻል ሚዲያ እና ለአጥቢያዎች ደብዳቤ በመጻፉ የማስታወቂያ ስራዎችን መስራቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑ የሶዶ ከተማ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ኅብረት ይህ ኮንፈረንስ በወላይታ ቀጠና ቃ/ሕ/ጽ/ቤት ፤ የሶዶ ከተማ እና ዞን ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስሉም እንዲሁም የሶዶ ከተማ ቃ/ሕ/ቤ/ያናት ኅብረትም ዕውቅና የሌለው በመሆኑም አጥቢያዎችም ሆነ ምዕመኖቻቸው ወደዚህ ፕሮግራም እንዳይሄዱ በዞን ፕሮግራም ጭምር በማስታወቂያ እንዲነገራቸው በጌታ ፍቅር እናሳውቃለን፡፡ ሲሉ በደብዳቤ ገልፀዋል። በቀኑ በኅብረቱ እውቅና ኮንፈረንስን ያዘጋጁ አጥቢያዎች ስታዲየም ቃ/ሕ/ቤ/ያን እና መብራት ኃይል ታ/ሕ/ቤ/ያን በእነዚህ አጥቢያዎች ንፁህን የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት እንዲትካፈለ እናሳስባለን፡፡ ሲሉም አሳስበዋል።
1 6345Loading...
05
የመጋቢ ቢኒያም ሽታዬ እና ነቢይ ኢዮብ ጭሮ ጨምሮ የ4 ግለሰቦች #ቤተክርስቲያን ፈቃድ ተሰረዘ። #የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስህተት ትምህርትና ልምምዶች ዙሪያ የ3ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔን ጋዜጣዊ መግለጫ ለሚዲያዎች ሰጥቷል። የካውንስሉን ምክር ተቀበለው፤ ሕዝብን ከሚያሳስት ተግባራቸው ለመመለስ ፈቃደኛ ሆነው ባለመገኘታቸው፤ ስማቸው ከዚህ በታች የተዘረዘሩት አብያተ ክርስቲያናትና ሚኒስትሪዎች ሠርተፍኬት እንዲሰረዝ ተወስኗል ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል። በዚህ መሰረት 1. ነቢይ ኢዮብ ጭሮ (ጆይ ጭሮ) (ጋድስ ላይት ግሎሪ ኢንተርናሽናል ሚኒስትሪ) 2. መጋቢ ካሳ ኪራጋ (ገዥዋ ዓለም አቀፍ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን) 3. መጋቢ መዝገቡ ሚስጥሩ (የሰማይቱ ጽዮን ማኅበርተኞች የክርስቶስ ቤተክርስቲያን) 4. መጋቢ ቢኒያም ሽታዬ (የእግዚአብሔር መንግስት እውነት ዓለም አቀፍ ሚኒስትሪ) ሙሉ በሙሉ ፈቃዳቸው ተሰርዟል። በመሆኑም የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት ከላይ ስማቸው የተቀመጡ አካላት ከዚህ ቀደም ከነበረባቸው ስህተቶች እንዲታረሙ በዝርዝር ቢመከሩም ፈጽሞ ሊመለሱ ያልቻሉ መሆናቸው ታውቆ ካውንስሉ ለሚወስደው ማንኛውም አስተዳደራዊ እርምጃ አስፈላጊውን ድግፍ እንዲያደርግ ተጠይቋል። በቀጣይ በተቋማቱ እና በግለሰቦቹ ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦችና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ሁሉ ላይ የሚወስደውን አስተዳደራዊ እርምጃ አስመልከቶ ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ድጋፍ ተጠይቋል። ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በቪዲዮ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
1 3923Loading...
06
https://youtu.be/h0KzcI2sFmQ?si=rFBhkHS9t0C42miP
1 3982Loading...
07
#እግዚአብሔር ያፅናናሽ። የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የመጀመሪያ ልጅ #ወደ ጌታ ሄደ። የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የ 17 ዓመት የመጀመሪያ ልጅ ክርስቲያን ላቃቸው በድንገተኛ ህመም ላንሴት አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል። The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለአርቲስት ዘሪቱና ለወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ይመኛል።
1 42414Loading...
08
#ዜና «ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ" የተሰኘ የመዝሙር ድግስ በሚሊኒየም #አዳራሽ ሊካሄድ ነዉ። ኤልሀዳር ኢንጂነሪንግ ከዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ጋር በመተባበር «ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ» የተሰኘውን የመዝሙር ድግስ በሚኒሊየም አዳራሽ ሰኔ 2/2016 ዓ.ም ቀን ከ7፡00 ጀምሮ ማዘጋጀቱን #ዛሬ ግንቦት 27/2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ። #ዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ሶስት አልበሞችን እና የተለያዩ ዝማሬዎችን ከተለያዩ ዘማሪዎች ጋር በመስራት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያበረከተ ሲሆን «ሙጫ ካዮ» ከተሰኘ የህፃናት ህብረት ጋር በመሆን ሁለት ቪሲዲዎችን በመስራት ለአማኞች አድርሷል። በእለቱ ስለታማ ነገሮች ምግብ እና መጠጥ ይዞ መግባት እንደማይቻል የተገለፀ ሲሆን በሚሊኒየም አዳራሽ መጠጥ እና ምግብ በሽያጭ እንደተዘጋጀ ተነግሯል። በዚህ ፕሮግራም ለመሳተፍ የመግቢያ ዋጋው በነፃ ስለሆነ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮ እንዲገኙ ጥሪ አስተላልፈዋል። ፎቶ 📸 @ጥላሁን ደሳለኝ
1 6091Loading...
09
በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦራ መቱ ከተማ ለሃይማኖታዊ ስብከት አደባባይ ወጥተው የነበሩ የሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አባላት በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ተፈጽሞባቸው ጉዳት እንደደረሰ ለቢቢሲ ተናገሩ። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ግለሰቦች እንዳሉት ከሆነ የፀጥታ ኃይሎቹ በፈጸሙት ድብደባ የተጎዱት ሰዎች ከ20 በላይ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። የመቱ ከተማ ከንቲባ አቶ ተሻለ ኤጀርሶ በበኩላቸው የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ያካሄዱት የጎዳና ላይ ስብከት ከተገቢው የመንግሥት አካል ፈቃድ እንዳላገኘ ተናግረዋል። የሙሉ ወንጌል #ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ፓስተር ብርሃኑ ዘለቀ በበኩላቸው ከመቱ እና አካባቢዋ የመጡ የቤተክርስቲያኒቷ አባላት እሁድ ግንቦት 25/2016 ዓ.ም ለጎዳና ላይ ስብከት በወጡበት በፖሊስ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። “ወደ ከተማዋ ጎዳና የወጣነው ወንጌል ለመስበክ ነው። ከአንድ #ሺህ #ሰው በላይ ይሆናል በወቅቱ የወጣው። መንገድ ሳንዘጋ በጎዳናው ላይ እየተንቀሳቀስን እየሰበክን ነበር። ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው። የፀጥታ ኃይሎች መጥተው አስቆሙን” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የከተማው ከንቲባ በበኩላቸው “በዕለቱ በከተማችን የትኛውም የእምነት ተቋም በከተማዋ ጎዳና ላይ አምልኮ ለማካሄድ በሚል ፈቃድ አልጠየቀም፣ አልወሰደም። በከተማው ጎዳና ላይ ወጥተው የነበሩ ሰዎችን ፖሊስ አስቁሟቸዋል። ፖሊስ ያስቆማቸው ፈቃድ ስለሌላቸው እና የመሰባሰባቸው ምክንያት ባለመታወቁ ነው” ብለዋል። ፓስተር ብርሃኑ፣ የፀጥታ ኃይል አባላቱ ምዕመናኑን ካስቆሟቸው በኋላ እየዘመሩ የነበሩትን በመኪና ጭነው ወደ ፖሊስ ጣቢያ መውሰዳቸውንም ይናገራሉ። ሙሉ ዝርዝር መረጃ ከThe Christian news የfacebook ገፃችን ያንብቡ #ወንጌል #ለዓለም #ሁሉ
1 9245Loading...
10
የኮርያ እና አይቮሪ ኮስት አብያተ ክርስቲያናት ከእናት ሜቱዲስት ቤ/ክ  መገንጠልን ለምን መረጡ? በአሜሪካ ከሚገኙ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት መካከል የዩናይትድ ሜቱዲስት ቸርች ተጠቃሽ ናት። ስር መሰረቷን እንግሊዝ ሃገር ከተነሱ የ18ኛው ክ/ዘመን መጀመሪያ፣ እውቅ የስነ መለኮት መምህራን መካከል የሆኑት ጆን ዌስሊይ ያደረገችው ይህቺ ቤ/ክ ዛሬ በአሜሪካ እና መላው አለም በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ተክላ ወንጌል ስትሰራ ቆይታለች። ታሪካዊ በሆነ ውሳኔ፣ ይህቺ ጥንታዊት ቤ/ክ ልክ የዛሬ 1 ወር በፊት ነው፣ ግብረሰዶም የሆኑ አገልጋዮችን በቤቷ የፈቀደችው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየወሩ በአለም ዙርያ ያሉ አብረው ሰራተኛ አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ማድረጋቸውን እያቆሙ ነው። ለአብነትም የኮትዲቯር፣ እና ሌሎችም የአፍሪካ ሃገራት የሚገኙ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሏቸው ሃገራት ከአሜሪካዋ ሜቱዲስት ጋር ያላቸውን ህብረት ማቆማቸውን በግልጽ አውጀዋል። ይሄንኑ የቤ/ክኗ ውሳኔ ተከትሎ፣ በሃገረ አሜሪካ ብቻ የሚገኙ ከ77 መቶ በላይ አብያተ ክርስቲያናትም ህብረት ማቆማቸውን አሳውቀው ነበር። ይህም የአባላቱን ቁጥር ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በድምሩ ከ10 ሚሊዮን በላይ ያደርገዋል። የኮርያ ሜቱዲስት አብያተ ክርስቲያናትም የቤተ ክርስቲያኗን ውሳኔ ተከትለው “ክርስትና የስሜት ጉዳይ አይደለም!” ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል። መጽሃፍ ቅዱስ በግልጽ ሃጢያት ነው ብለው ያስቀመጠው ጉዳይ ላይ የግለሰቦች ሃሳብ በቤ/ክን ላይ መሰልጠን የለበትም ብለዋል አቋማቸውን ሲገልጡ። ቤተ ክርስቲያኗ ያላት #አንድ ተስፋ በአፍሪካ ብቻ ነው ብለዋል። በዚህ ውሳኔዋ ብቻ ከአባላቷ ሩብ ያክል ወደ 11 ሚሊዮን የሚገመቱ አባላትን የያዙ አብያተ ክርስቲያናት፣ ህብረታቸውን ከአሜሪካ ሜቱዲስት ጋር አቋርጠዋል።
1 9968Loading...
11
#እናመሰግናለን 🙏🙏🙏 The Christian News - የክርስቲያን ዜና በYoutube ቻናላችን #50k ሺህ ቤተስቦች ደርሰናል። ታማኝ እና ፈጣን #የክርስቲያን መረጃዎች ምንጭ አድርጋችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን። በቀጣይ እጅግ በርካታ ስራዎች በጋራ እንደምንሰራ በማመን አሁንም አብሮነታችሁ ይቀጥል እንላለን። በቅርብ ጊዜ ለምስጋና በድጋሜ እንደምንገናኝ እናምናለን። https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A
1 9130Loading...
12
ተወዳጁ ዘማሪ አዉታሩ ከበደ ቁጥር 7ቱን የዝማሬ አልበም ሊለቅ ነዉ። "ከ9 አመታት በኋላ የ7 ቁጥር አልበሜ በመንፈስ ተጠምቆ ለቅዱሳን በረከት ላልዳኑ የኢየሱሰን አዳኝነት ለማብሰር ተጠናቋል" ሲል ዘማሪዉ ገልጿል። የምትፅልዩልኝ,በነገር ሁሉ ከጎኔ ያላችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። በሁላችሁ እጅ ላይ በቅርቡ የሚደርስበትን ቀን አሳውቃለው የዘማሪዉ መልዕክት ነዉ።
2 9273Loading...
13
የዝሙት ሕይወቴን ማንም አያወቅም ነበር ሰዎች መማር ካለባቸው ከእኔ ይማሩ #ድንቅ #ምስክርነት ከዚህ ልምምድ መውጣት ሲያቅተኝ ከጌታ ቤት ባክ አደረኩኝ https://youtu.be/ugkLCiXAYII
3 29520Loading...
14
#ይፈቱ በኤርትራ ከ 20 አመታት በላይ የታሰሩ የፕሮቴስታንት እምነት ፓስተሮች እንዲፈቱ አሜሪካ ጠየቀች። የአሜሪካው ዓለማቀፍ የኃይማኖት ነጻነት ኮሚሽን፣ የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኤርትራ ላለው የኃይማኖት ነጻነት ጥሰት ትልቅ ትኩረት እንዲሰጥ መጠየቁ ዳጉ ጆርናል ከዘገባዎች ተመልክቷል። ኮሚሽኑ፣ ፓስተር ኃይሌ ናይዝጊ እና ፓስተር ክፍሉ ገብረመስቀል የተባሉ የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ሰባኪዎች ከታሠሩ ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥረዋል ሲል ለአብነት ጠቅሷል። #ኤርትራ ፣ ከኃይማኖት ነጻነት ጋር በተያያዘ 5 መቶ ያህል ሰዎችን ክስ ሳይመሠረትባቸው እንዳሠረች ኮሚሽኑ አመልክቷል። የኤርትራ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከኃይማኖት ጋር በተያያዘ የታሠሩ ዘጠኝ እስረኞችን #ብቻ መፍታቱን ያስታወሰው ኮሚሽኑ፣ ጅምሩ #ግን ሳይቀጥል ቀርቷል በማለት ወቅሷል። ሲል ዋዜማ ሬድዬ ዘግቧል። ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
3 3554Loading...
15
#መቀሌ #ታላቁ ተልዕኮ ኢትዮጵያ 10 ቢሮውን በትግራይ መቀሌ ከፈተ። ግሬት ኮሚሽን ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ #በኢትዮጵያ የወንጌል ስራን ሲሰራ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት በአዳማ፣ ባህርዳር፣ ሃረር፣ ሃዋሳ፣ ጅማ፣ ነቀምቴ፣ አርባ ምንጭ፣ ሆሳዕና እና አምቦ የአካባቢ ቢሮዎችን አቋቁሞ በየአካባቢው ከሚገኙ ሚኒስትሪዎችና አብያተ ክርስቲያናት ጋር ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ግሬት ኮሚሽን #ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ፣ የጂሰስ ፊልምን በ74 የሃገር ውስጥ ቋንቋዎች በማስተርጎምና በ10 ሃገራት ውስጥ ኢንዲጂተስ በተሰኘ የቴክኖሎጂ ማህበረሰብን በመፍጠር በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጪም ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ከጦርነት መልስ የወንጌል ስርጭት ማዕከል በትግራይ የተከፈተውን ይሄንን ቢሮ ያስተባበረው ወንድም #ካሳሁን_ሰዒድ ሲሆን በመድረኩ እውቅና ተሰጥቶታል። ወንድም ካሳሁን መቀሌ እና መላውን ትግራይ ላለፉት 10 ዓመታት በወንጌል ለመድረስ ሲያገለግል ቆይቷል። ምንጭ፣ GCMEthiopia ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
2 5542Loading...
16
የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርታቸውን ለመንግሥት እንዲያቀርቡ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት፣ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ፡፡ " የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጅ፣ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውንም ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው የሚደነግግ መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። የሃይማኖት ተቋማቱ የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን እንደሚኖርበትና የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን እንዳለባቸውም ይገልጻል። አንድ የሃይማኖት ተቋም በራሱ የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ፣ ለዚሁ ሥራ የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ እንዳለበትም ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ ይኖርበታል ተብሏል። በተጨማሪም የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስምና አድራሻ፣ የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነትና መጠን፣ እንዲሁም ስጦታው ወይም ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ የሃይማኖት ተቋማቱ ጨምርው ማሳወቅ እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡
2 1103Loading...
17
"#የአፍሪካ #መንፈሳዊ ቀን" በአፍሪካ ሕብረት ተካሄደ። በInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) አዘጋጅነት "Educating the African person to be Spiritually fit in the 21st Century" በሚል መሪ ቃል ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ መሪዎች በተገኙበት በአፍሪካ ሕብረት ተከናውኗል። የሃይማኖት ተቋማት እና መሪዎች በሰላም እና በልማት ስራዎች ላይ በቅንጅት ለአፍሪካ መስራት እንደሚገባቸው በመድረኩ ተጠቅሷል። በመድረኩ የInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) የአፍሪካ ሊቀመንበር ዶ/ር ኡዙዊን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እና የእስልምና እምነት በሀገራችን የትምህርት ስረዓት ያበረከቱትን አስተዋጽዖ በተመለከተ የተለያዩ ጽሑፎች ቀርበዋል። በጉባኤው በቅርብ ጊዜ የምስረታ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓላቸውን ያከበሩት አንጋፋዎቹ የመሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ (ቢጫ ኳይር) ዝማሬ አቅርበዋል።
2 2412Loading...
18
#ቤተ #በአዲስ አበባ በሆሳዕና ለረጅም አመት እያገለገለች የምትገኘዉ ቤተምህረት #አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ የቤተ ክርስቲያን ተከላና- የመክፈቻ ፕሮግራም ከግንቦት 21-25 / ከእሮብ እስከ ቅዳሜ ከ 10:00 ጀምሮ እሁድ ጠዋት ይከናወናል። #አድራሻ ፦ ከቡልጋሪያ #ወደ ቄራ ሲወርዱ ስካኒያ አካባቢ የቤተ ምህረት ማስታወቂያ ባለበት 100 ሜትር ገባ ብሎ ያገኙናል። #ቤተ ምህረት እንገናኝ 🙏🙏
2 9762Loading...
19
#የአርሰናል ደጋፊዎች በቤተክርስቲያን ምስጋና አቀረቡ። በኬንያ የሚገኙ የአርሰናል ደጋፊዎች ከድል በኋላ በቤተክርስቲያን ዉስጥ ምስጋና አቀረቡ በኬንያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ የሚገኙት የአርሰናል ደጋፊዎች ቅዳሜ እለት ባደረጉት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቡድናቸው ክሪስታል ፓላስን 5 ለ 0 በመርታቱ አድናቆትን ከማትረፍ ባለፈ በአንድ አጥቢያ ቤተክርስትያን በመሰባሰብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ደጋፊዎቹ የመድፈኞቹን ማሊያ ለብሰው በእሁድ ጠዋት አገልግሎት ላይ ቡድናቸው ላሳየው አስደናቂ ብቃት በደስታ ውዳሴ እና ምስጋና አቅርበዋል።በመጪው የውድድር ዘመን ለአርሰናል ቀጣይ ስኬት ተስፋ በማድረግ ጸሎት አቅርበዋል። ከታዳሚዎቹ መካከል ጋዜጠኛ ኬኔዲ ሙሪቲ በፀሎት ስነ ስርዓቱ ላይ የተነሱትን ፎቶዎች በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራቱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።የሰሜን ለንደኑ አርሰናል አንድ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቸስተር ሲቲ እኩል እና ከሊቨርፑል በአምስት ነጥብ ዝቅ ብሎ ተቀምጧል። ፎቶዎቹ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን የፈጠሩ ሲሆን አንዳንዶቹ በደጋፊዎች ላይ አፌዜዋለሁ፡፡
2 97113Loading...
20
ራስን ማጥፋት የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ Assisted Suicide #ወይም በእገዛ ራስን ማጥፋትን እየተቃወሙ ይገኛሉ። ይሄንን ያውቁ ነበረ። በአለማችን 15 ሃገራት በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ይፈቅዳሉ። በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ማለት፣ #አንድ #ሰው ራሱን ሲያጠፋ በሃኪም እገዛ ህጋዊ በሆነ መንገድ የህይወት ጉዞውን ማብቃት ማለት ነው። የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት ይሄንኑ ድርጊት በሃገሪቱ ህጋዊ እንዲሆን መጠየቁን ተከትሎ ነው ድምጻቸውን ያሰሙት። ለ129 የምክር ቤት አባላት በተላከው ደብዳቤ መሰረት፣ በአንድ የምክር ቤቱ አባል የቀረበውን ይሄንኑ አጸያፊ ተግባር ህጋዊ እንዳይደረግ ጠይቀዋል። በደብዳቤያቸው፣ ይሄ ህግ የሰው ልጅን ሞራላዊነት አሽቀንጥሮ መጣል ነው፣ እንደ ሃገር አለን የምንለውን የሰው ልጆች ዋጋ የሚያሳጣን ነው ብለዋል። ህጉ የሚጸድቅ ከሆነ ስኮትላንድ ስነምግባር የሌለባት፣ ምክር ቤታችንም ለሰው ልጆች ዋጋ የሌለው አዳራሽ መሆኑ ነው ሲሉ አሳስበዋል። በእገዛ ራስን ማጥፋት ማለት የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ የሌለው መሆኑን ማሳያ ነው። ዘፍጥረት ላይ #እግዚአብሔር በአምሳያው የሰውን ልጆች መፍጠሩ፣ ሁሉም የሰው #ልጆች በእግዚአብሔር እንደሚወደድ ማሳያ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ አለው ብለዋል። ይሄንን ደብዳቤ የላኩት ቄስ አንድሪው ዶውኒ እና ቄስ ቦብ አክሮይድ የዩናይትድ ፍሪ ቸርች ኦፍ ስኮትላንድ አገልጋዮች ናቸው። ሃገራችን ስኮትላንድ ሰዎች ራሳቸውን ማጥፋት የማያስቡባት መሆን አለባት ብለዋል። ምናልባት በመሰል ስሜት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ማህበረሰባችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ፍቅርና እንክብካቤ ማሳየት አለበት ብለዋል። ስኮትላንድ የ1517ቱ ተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲስፋፋ ያገዙት ጆን ኖክስ ትውልድ ሃገር መሆኗ ይታወሳል።
3 3589Loading...
21
የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር በአዲስ አበባ ስብሰባውን አካሄደ። ማህበሩ ባካሄደው ስብሰባው የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ተጽኖ የሚያደርሱ ጉዳዮች በስፋት ተዳሰዋል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት፣ ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ማህበሩ በአፍሪካ የሚገኙ ከ250 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናትን ያቀፈ ነው። በስብሰባው የአፍሪካ ህብረት በ2063 ሊያሳካ ካቀዳቸው ግቦች መካከል ጤናማ ዜጋ መፍጠር እና ተሸጋጋሪ ኢኮኖሚ ግንባታን እውን ማድረግን እንደሚያግዝ በመድረኩ ተነስቷል። አፍሪካን የበለጸገችና ሰላማዊ ለማድረግ እንደሚሰራም የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር ገልጿል።
2 8051Loading...
22
#እንኳን #ደስ አለህ #ወጣቱ ወንድማገኝ የመላዉ አፍሪካ አብያተክርስቲያናት ጉባኤ የጠቅላላ ኮሚቴ አባል በመሆን ተመርጧል። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ ናይጄሪያ አቡጃ እየተካሄደ በሚገኘዉ በ12ኛው የመላ አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ወጣቶችን በመወከል የጠቅላላ ኮሚቴ አባል በመሆን ተመርጧል:: The Christian News - የክርስቲያን ዜና የተሰማንን ደስታ እየገለፅን #መልካም የአገልግሎት #ጊዜ እንዲሆንልህ እንመኛለን። Wondmagegn Udessa Bidire 🙏🙏🙏
2 4841Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
#አዲስ መጽሐፍ #በቅርብ #ቀን... ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተ #ድንቅ የአማርኛ መጽሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት በዘላለም መንግስቱ ተዘጋጅቶ በቅርብ ቀን ወደ አንባቢያን ይደርሳል። 23 ዓመታት የፈጀው #ይህ #ድንቅ መጽሀፍ በቅርብ ቀን በአዲስ አበባ ሰኔ 15 2016 በኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ (ETC) የምስጋና ጊዜ ከጠዋቱ 4 እስከ 6 ሰዓት በድምቀት ይመረቃል።
إظهار الكل...
👍 20 5🔥 1🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
#የዛሬ -ሃምሳ #ዓመት #እኔ #በጌታ ምሪት #ወደ ባሌ ጎባ ገብቼ ቤተክርስቲያን ለመትከል ቤት የተከራየውበት ቀን #በሮቤና በአጋርፋ ይሠሩና ይኖሩ ከነበሩት ሁለት ወንድሞች #አያና መኳንንና #ከአባተ ወላኒዎሰ ጋር ከሮቤ አንድ ታጣፊ አልጋ ከነፍራሹ በ28 ብር ገዝተን ቤቱን ደግሞ በ10 ብር ተከራይተን የኪራይ ውል ፈጸምን። ኪራዩን ከሁለቱ ወንድሞች ማን እንደከፈለ ትዝ አይለኝም ። ቤቱ ወንዝ ደር ከመሆኑም በላይ ንፋስ ያስገባል እና በጣም ይበርዳል። በተለይም በማያውቁት አገር ሌሊቱን ለብቻ ማደር እንዴት ያስፈራል። ሃምሳ ዓመት ወደ ኋሊት አሰብኩ ። የአምላኬ ምህረትና ማደን ቸርነቱም ገረመኝ ደነቀኝም። ስሙ ለዘለዓለም የተባረከ ይሁን ። 🙏🙏🙏 ከመጋቢ ጻድቁ አብዶ (የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ኅብረት ፕረዚዳንት) ገጽ የተወሰደ
إظهار الكل...
👍 19 10🙏 3🔥 2🥰 1🕊 1
Photo unavailableShow in Telegram
በመቱ የሙሉ #ወንጌል አማኞች #ላይ ደረሰ የተባለው ድብደባ እንዲጣራ የአብያተ ክርስቲያናት ኅብረቱ ጠየቀ። #እሁድ ግንቦት 25 በመቱ ከተማ ለወንጌል ስርጭት በወጡ ክርስቲያኖች ላይ በፖሊስ እና ሚሊሻዎች ድብደባ ተፈጽሟል። ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ወገኖች መካከል አስተያቷን ለአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የሰጠችው ኤደን ግርማ እንዲህ ብላለች። ኤደን ግርማ፣ ጥቃት የደረሰባት “የእሁድ አምልኮ ጨርሰን ለወንጌል ስርጭት ሶሪ ዳቦ የሚባልበት አካባቢ ስንደርስ ፖሊሶችና ሚልሻዎች በመኪና መጡ። መሬት ላይ ተቀመጡ ካሉ በኋላ፣ የተወሰኑ ወጣቶች ወደ ፖሊስ ጣብያ ወሰዱን። አመሻሽ ላይ ከአንዱ አመራር ጋር ፖሊስ ጣብያው አካባቢ መሬት ተቀመጡ ብሎ እያወራን፣ ፖሊሶችና ሚሊሻዎች ድብደባ ጀመሩ። እኔ ጭንቅላቴን ተመቼ ስደማ፣ ሌሎችም በጣም ተጎድተው ወደ ሆስፒታል ለህክምና ተወስደናል።” ስትል ተናግራለች። #ቄስ ደበላ ያደታ፣ የኢሉባቦር ዞን ወንጌላዊያን አብያተ ክርስትያናት ህብረት ሰብሳቢ በበኩላቸው “እኛ ህገ መንግስቱ በሚሰጠን መብት መሰረት እምነታችንን የማካሄድ መብት አለን። ከመንግስት ጋርም በሚያስፈልጉ ነገሮች ዙርያ በትብብር ስንሰራ ቆይተናል። መንግስት እንደዚህ ያደርጋል የሚል እምነት ባይኖረንም፣ የመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ሰዎች ግን ይሄንን እንዳደረሱ በትክክል እናውቃለን። ስለዚህ ሁኔታው በትክክል እንዲታራ እንጠይቃለን።” ብለዋል። አቶ ተሻለ ኤጄርሶ፣ የመቱ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው “ከሳምንት በፊት ለነበረው ስብከተ ወንጌል ፍቃድ የተሰጠ ቢሆንም፣ እሁድ ግንቦት 18 ሲደረግ ለነበረው የወንጌል ስርጭት የተሰጠ ፍቃድ የለም። አላስፈላጊ ድብደባና ግጭት ከፖሊስ ዘንድ መድረሱን ተመልክተናል። ከጸጥታ አካላት ጋርም ይሄንኑ ጉዳይ በተመለከተ ምርመራ እየተካሄደ ነው።” VOA Amharic
إظهار الكل...
👍 22 3🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
ምዕመናን #ወደ ፕሮግራሙ እንዳትሄዱ። "በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም የሚደረገው ኮንፈረንስ እውቅና የለዉም" ስትል የወላይታ ቀጠና ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ገለፀች። ቤተክርስቲያኒቱ ከሰኔ 01 እና 02/2016ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም CJ ኮንፍራንስ ለማድረግ በሶሻል ሚዲያ እና ለአጥቢያዎች ደብዳቤ በመጻፉ የማስታወቂያ ስራዎችን መስራቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑ የሶዶ ከተማ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ኅብረት ይህ ኮንፈረንስ በወላይታ ቀጠና ቃ/ሕ/ጽ/ቤት ፤ የሶዶ ከተማ እና ዞን ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስሉም እንዲሁም የሶዶ ከተማ ቃ/ሕ/ቤ/ያናት ኅብረትም ዕውቅና የሌለው በመሆኑም አጥቢያዎችም ሆነ ምዕመኖቻቸው ወደዚህ ፕሮግራም እንዳይሄዱ በዞን ፕሮግራም ጭምር በማስታወቂያ እንዲነገራቸው በጌታ ፍቅር እናሳውቃለን፡፡ ሲሉ በደብዳቤ ገልፀዋል። በቀኑ በኅብረቱ እውቅና ኮንፈረንስን ያዘጋጁ አጥቢያዎች ስታዲየም ቃ/ሕ/ቤ/ያን እና መብራት ኃይል ታ/ሕ/ቤ/ያን በእነዚህ አጥቢያዎች ንፁህን የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት እንዲትካፈለ እናሳስባለን፡፡ ሲሉም አሳስበዋል።
إظهار الكل...
👍 17 6🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
የመጋቢ ቢኒያም ሽታዬ እና ነቢይ ኢዮብ ጭሮ ጨምሮ የ4 ግለሰቦች #ቤተክርስቲያን ፈቃድ ተሰረዘ። #የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በስህተት ትምህርትና ልምምዶች ዙሪያ የ3ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔን ጋዜጣዊ መግለጫ ለሚዲያዎች ሰጥቷል። የካውንስሉን ምክር ተቀበለው፤ ሕዝብን ከሚያሳስት ተግባራቸው ለመመለስ ፈቃደኛ ሆነው ባለመገኘታቸው፤ ስማቸው ከዚህ በታች የተዘረዘሩት አብያተ ክርስቲያናትና ሚኒስትሪዎች ሠርተፍኬት እንዲሰረዝ ተወስኗል ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል። በዚህ መሰረት 1. ነቢይ ኢዮብ ጭሮ (ጆይ ጭሮ) (ጋድስ ላይት ግሎሪ ኢንተርናሽናል ሚኒስትሪ) 2. መጋቢ ካሳ ኪራጋ (ገዥዋ ዓለም አቀፍ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን) 3. መጋቢ መዝገቡ ሚስጥሩ (የሰማይቱ ጽዮን ማኅበርተኞች የክርስቶስ ቤተክርስቲያን) 4. መጋቢ ቢኒያም ሽታዬ (የእግዚአብሔር መንግስት እውነት ዓለም አቀፍ ሚኒስትሪ) ሙሉ በሙሉ ፈቃዳቸው ተሰርዟል። በመሆኑም የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት ከላይ ስማቸው የተቀመጡ አካላት ከዚህ ቀደም ከነበረባቸው ስህተቶች እንዲታረሙ በዝርዝር ቢመከሩም ፈጽሞ ሊመለሱ ያልቻሉ መሆናቸው ታውቆ ካውንስሉ ለሚወስደው ማንኛውም አስተዳደራዊ እርምጃ አስፈላጊውን ድግፍ እንዲያደርግ ተጠይቋል። በቀጣይ በተቋማቱ እና በግለሰቦቹ ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦችና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ሁሉ ላይ የሚወስደውን አስተዳደራዊ እርምጃ አስመልከቶ ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ድጋፍ ተጠይቋል። ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በቪዲዮ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
إظهار الكل...
👍 22 4🔥 1👏 1
إظهار الكل...

👍 3 1🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
#እግዚአብሔር ያፅናናሽ። የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የመጀመሪያ ልጅ #ወደ ጌታ ሄደ። የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የ 17 ዓመት የመጀመሪያ ልጅ ክርስቲያን ላቃቸው በድንገተኛ ህመም ላንሴት አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል። The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለአርቲስት ዘሪቱና ለወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ይመኛል።
إظهار الكل...
😭 48 3🕊 2🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
#ዜና «ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ" የተሰኘ የመዝሙር ድግስ በሚሊኒየም #አዳራሽ ሊካሄድ ነዉ። ኤልሀዳር ኢንጂነሪንግ ከዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ጋር በመተባበር «ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ» የተሰኘውን የመዝሙር ድግስ በሚኒሊየም አዳራሽ ሰኔ 2/2016 ዓ.ም ቀን ከ7፡00 ጀምሮ ማዘጋጀቱን #ዛሬ ግንቦት 27/2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ። #ዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ሶስት አልበሞችን እና የተለያዩ ዝማሬዎችን ከተለያዩ ዘማሪዎች ጋር በመስራት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያበረከተ ሲሆን «ሙጫ ካዮ» ከተሰኘ የህፃናት ህብረት ጋር በመሆን ሁለት ቪሲዲዎችን በመስራት ለአማኞች አድርሷል። በእለቱ ስለታማ ነገሮች ምግብ እና መጠጥ ይዞ መግባት እንደማይቻል የተገለፀ ሲሆን በሚሊኒየም አዳራሽ መጠጥ እና ምግብ በሽያጭ እንደተዘጋጀ ተነግሯል። በዚህ ፕሮግራም ለመሳተፍ የመግቢያ ዋጋው በነፃ ስለሆነ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮ እንዲገኙ ጥሪ አስተላልፈዋል። ፎቶ 📸 @ጥላሁን ደሳለኝ
إظهار الكل...
🔥 10👍 6 2🥰 1👏 1👌 1
Photo unavailableShow in Telegram
በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦራ መቱ ከተማ ለሃይማኖታዊ ስብከት አደባባይ ወጥተው የነበሩ የሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አባላት በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ተፈጽሞባቸው ጉዳት እንደደረሰ ለቢቢሲ ተናገሩ። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ግለሰቦች እንዳሉት ከሆነ የፀጥታ ኃይሎቹ በፈጸሙት ድብደባ የተጎዱት ሰዎች ከ20 በላይ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። የመቱ ከተማ ከንቲባ አቶ ተሻለ ኤጀርሶ በበኩላቸው የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ያካሄዱት የጎዳና ላይ ስብከት ከተገቢው የመንግሥት አካል ፈቃድ እንዳላገኘ ተናግረዋል። የሙሉ ወንጌል #ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ፓስተር ብርሃኑ ዘለቀ በበኩላቸው ከመቱ እና አካባቢዋ የመጡ የቤተክርስቲያኒቷ አባላት እሁድ ግንቦት 25/2016 ዓ.ም ለጎዳና ላይ ስብከት በወጡበት በፖሊስ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። “ወደ ከተማዋ ጎዳና የወጣነው ወንጌል ለመስበክ ነው። ከአንድ #ሺህ #ሰው በላይ ይሆናል በወቅቱ የወጣው። መንገድ ሳንዘጋ በጎዳናው ላይ እየተንቀሳቀስን እየሰበክን ነበር። ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው። የፀጥታ ኃይሎች መጥተው አስቆሙን” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የከተማው ከንቲባ በበኩላቸው “በዕለቱ በከተማችን የትኛውም የእምነት ተቋም በከተማዋ ጎዳና ላይ አምልኮ ለማካሄድ በሚል ፈቃድ አልጠየቀም፣ አልወሰደም። በከተማው ጎዳና ላይ ወጥተው የነበሩ ሰዎችን ፖሊስ አስቁሟቸዋል። ፖሊስ ያስቆማቸው ፈቃድ ስለሌላቸው እና የመሰባሰባቸው ምክንያት ባለመታወቁ ነው” ብለዋል። ፓስተር ብርሃኑ፣ የፀጥታ ኃይል አባላቱ ምዕመናኑን ካስቆሟቸው በኋላ እየዘመሩ የነበሩትን በመኪና ጭነው ወደ ፖሊስ ጣቢያ መውሰዳቸውንም ይናገራሉ። ሙሉ ዝርዝር መረጃ ከThe Christian news የfacebook ገፃችን ያንብቡ #ወንጌል #ለዓለም #ሁሉ
إظهار الكل...
😭 13👍 4🔥 2🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
የኮርያ እና አይቮሪ ኮስት አብያተ ክርስቲያናት ከእናት ሜቱዲስት ቤ/ክ  መገንጠልን ለምን መረጡ? በአሜሪካ ከሚገኙ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት መካከል የዩናይትድ ሜቱዲስት ቸርች ተጠቃሽ ናት። ስር መሰረቷን እንግሊዝ ሃገር ከተነሱ የ18ኛው ክ/ዘመን መጀመሪያ፣ እውቅ የስነ መለኮት መምህራን መካከል የሆኑት ጆን ዌስሊይ ያደረገችው ይህቺ ቤ/ክ ዛሬ በአሜሪካ እና መላው አለም በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ተክላ ወንጌል ስትሰራ ቆይታለች። ታሪካዊ በሆነ ውሳኔ፣ ይህቺ ጥንታዊት ቤ/ክ ልክ የዛሬ 1 ወር በፊት ነው፣ ግብረሰዶም የሆኑ አገልጋዮችን በቤቷ የፈቀደችው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየወሩ በአለም ዙርያ ያሉ አብረው ሰራተኛ አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ማድረጋቸውን እያቆሙ ነው። ለአብነትም የኮትዲቯር፣ እና ሌሎችም የአፍሪካ ሃገራት የሚገኙ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሏቸው ሃገራት ከአሜሪካዋ ሜቱዲስት ጋር ያላቸውን ህብረት ማቆማቸውን በግልጽ አውጀዋል። ይሄንኑ የቤ/ክኗ ውሳኔ ተከትሎ፣ በሃገረ አሜሪካ ብቻ የሚገኙ ከ77 መቶ በላይ አብያተ ክርስቲያናትም ህብረት ማቆማቸውን አሳውቀው ነበር። ይህም የአባላቱን ቁጥር ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በድምሩ ከ10 ሚሊዮን በላይ ያደርገዋል። የኮርያ ሜቱዲስት አብያተ ክርስቲያናትም የቤተ ክርስቲያኗን ውሳኔ ተከትለው “ክርስትና የስሜት ጉዳይ አይደለም!” ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል። መጽሃፍ ቅዱስ በግልጽ ሃጢያት ነው ብለው ያስቀመጠው ጉዳይ ላይ የግለሰቦች ሃሳብ በቤ/ክን ላይ መሰልጠን የለበትም ብለዋል አቋማቸውን ሲገልጡ። ቤተ ክርስቲያኗ ያላት #አንድ ተስፋ በአፍሪካ ብቻ ነው ብለዋል። በዚህ ውሳኔዋ ብቻ ከአባላቷ ሩብ ያክል ወደ 11 ሚሊዮን የሚገመቱ አባላትን የያዙ አብያተ ክርስቲያናት፣ ህብረታቸውን ከአሜሪካ ሜቱዲስት ጋር አቋርጠዋል።
إظهار الكل...
👍 17😭 8 2🔥 1