የሕግ ዜና
الذهاب إلى القناة على Telegram
⚖️ የሕግ ዜና | Legal News ወቅታዊ የሕግ መረጃዎች፣ የፍትሕ ለውጦች እና የሕግ መሻሻሎች የሚቀርቡበት መድረክ። ከሕግ አውጪው ውሳኔ እስከ ፍርድ ቤት ውሎ፤ እስከ ተበዳዮች መብት ድረስ📍 የጠበቆች ምክር እና የፍትሕ ክንውኖች https://www.facebook.com/share/17edCauY5V/
إظهار المزيد4 474
المشتركون
+424 ساعات
+207 أيام
+7030 أيام
أرشيف المشاركات
4 474
ከኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ጋር ተስማሚ የሆነ የሽያጭ መመዝገቢያ ስርዓት መጠቀም በሁሉም የሂሳብ መዝገብ በሚይዙ ታክስ ከፋዮች ላይ አስገዳጅ የሚያደርግ መመሪያ ወጥቷል።
የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አስተዳደሩን ለማዘመን እና የታክስ ስወራን በዘላቂነት ለመከላከል ያስችላል ያለውን "የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ ሥርዓት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1142/2018" አውጥቷል።
መመሪያው በዋናነት የታለመው የታክስ አስተዳደሩን ከዘመናዊው የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ለማጣጣም ነው።
እንደ መመሪያው ገለጻ፣ ማንኛውም የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ያለበት ታክስ ከፋይ በሚኒስቴሩ እውቅና ከተሰጠው የሽያጭ መመዝገቢያ ሶፍትዌር ጋር የተገናኘ የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ይኖርበታል።
ይህ አሰራር ግብይቶች በተከናወኑበት ወዲያውኑ (Real-time) ለሚኒስቴሩ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት ሪፖርት እንዲደረጉ የሚያስችል በመሆኑ፣ መረጃዎችን የመሰወርና ደረሰኞችን የማጭበርበር እድልን በእጅጉ እንደሚያጠፋው ይጠበቃል።
በአዲሱ መመሪያ መሰረት፣ የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ የሚሰጠው በሚኒስቴሩ ተገንብቶ በሚቀርበው ማዕከላዊ የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት አማካኝነት ነው።
እያንዳንዱ ደረሰኝ የደረሰኝ ምዝገባ ቁጥር (IRN) እና ፈጣን መላሽ ኮድ (QR Code) የሚሰጠው ሲሆን፣ ይህም ደረሰኙ ህጋዊ መሆኑን በገዢውም ሆነ በግብር ሰብሳቢው አካል በቀላሉ ለማረጋገጥ ያስችላል።
በተጨማሪም ደረሰኞች በዲጂታል አማራጮች እንደ ኢሜይል እና አጭር የፅሁፍ መልዕክት ለገዢው እንዲደርሱ የሚደረግ ሲሆን፣ እንደ አስፈላጊነቱ ታትሞ እንዲሰጥም መመሪያው ይፈቅዳል።
መመሪያው በሶፍትዌር አልሚዎች እና አገልግሎት አቅራቢዎች ላይም ጥብቅ የሆኑ መስፈርቶችን አስቀምጧል።
ማንኛውም የሽያጭ መመዝገቢያ ሶፍትዌር አቅራቢ ወይም የክላውድ (Cloud-based SaaS) አገልግሎት ሰጪ ድርጅት በሚኒስቴሩ እውቅና ማግኘት ይኖርበታል።
ለዚህም እንደ ዋስትና በባንክ ወይም በመድን የተረጋገጠ እስከ 50,000 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የመልካም አፈፃፀም ዋስትና እንዲያስይዙ ይጠየቃሉ።
ይህም በዘርፉ የሚሰማሩ ድርጅቶች ጥራት ያለውና አስተማማኝ ቴክኖሎጂ ለታክስ ከፋዩ ማቅረባቸውን ለማረጋገጥ የታለመ ነው።
ይፋ የተደረገው አዲስ መመሪያ፣ የኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ ሥርዓቱን በበላይነት የሚመሩና የሶፍትዌር ጥራቱን የሚቆጣጠሩ ሁለት ታላላቅ የባለሙያ ስብስቦች እንደሚቋቋሙ ይገልጻል።
በመመሪያው መሠረት፣ የ"ቴክኒክ ቡድን" እና የ"እውቅና ሰጭ ቦርድ" የሚባሉ አካላት የሚቋቋሙ ሲሆን፣ እነዚህ አካላት ማንኛውም በገበያ ላይ የሚውል የሽያጭ መመዝገቢያ ሶፍትዌር የታክስ ሕጉን ማክበሩንና ከመንግስት የመረጃ ቋት ጋር በአግባቡ መገናኘቱን የማረጋገጥ ከፍተኛ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
መመሪያው ከፍተኛ የቴክኖሎጂ አቅም ለሌላቸው ወይም አዲስ ወደ ንግድ ዓለም ለሚገቡ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ልዩ ድጋፍ የሚያደርግ የ"ክላውድ ሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓትም" (Cloud Sales Register System) ይፋ አድርጓል።
የኢንተርኔት ግንኙነት በማይኖርበት ወቅት ግብይቶች እንዳይስተጓጎሉ የ"ከመስመር ውጭ" (Offline) የሆነ አሰራርም ተዘርግቷል።
በተለይም የምግብ፣ የመጠጥ፣ የመድኃኒት እና መሰል መሰረታዊ የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ታክስ ከፋዮች የኢንተርኔት ግንኙነት ቢቋረጥ እንኳ ግብይቶችን መመዝገብ የሚችሉበትና ግንኙነቱ ሲመለስ መረጃው በራሱ የሚተላለፍበት ሥርዓት እንዲዘረጋ ተደንግጓል።
የመረጃ ደህንነትን በተመለከተም እያንዳንዱ ሶፍትዌርና የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) የደህንነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማግኘት እንዳለበት ታዟል።
በተጨማሪም የግል ታክስ ከፋዮች መረጃ ለሶስተኛ ወገን እንዳይጋለጥ እና ለመንግስት የሚተላለፈው መረጃ በሚስጥር (Encryption) የተጠበቀ እንዲሆን ጥብቅ ደንቦች ተቀምጠዋል።
ከኤሌክትሮኒክ ደረሰኝ መመዝገቢያ ሥርዓት ተስማሚ የሆነ የሽያጭ መመዝገቢያ ስርዓት መጠቀም በሁሉም የሂሳብ መዝገብ በሚይዙ ታክስ ከፋዮች አስገዳጅ ሲሆን ትግበራው ባለስልጣኑ በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚተገበር ይሆናል ተብሏል።
ይህ አዲስ መመሪያ ሰኔ 2/2018 ዓም በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ በድህረ ገጹ ላይ የተጫነ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
4 474
ክብርት ዳኛዋን በችሎት የገደለው እራሱን አጠፋ።
በችሎት አዳራሽ በሽጉጥ ክብርት ዳኛዋን እና ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ ከ3ኛ ፎቅ ላይ እራሱን ወርውሮ ህይወቱን አጠፋ።
ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በሆለታ ወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በችሎት አዳራሽ የቤተሰብ ክርክርን መዝገብ ስትመለከት የነበረችው ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ እንዲሁም የክርክሩ አካል የሆነች የተከሳሹ የቀድሞ ባለቤት ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸውን እንዲያልፍ ማድረጉ አይዘነጋም።
በዕለቱም እራሱ ላይ በመተኮስ ቆስሎ የነበረዉ አቅነዉ በቀለ የተባለው ግለሰብ በፖሊስ ጥበቃ እየተደረገ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል ላይ ነበር።
ሆኖም ግለሰቡ በዛሬው ቀን ሕክምናውን ጨርሶ ከሆስፒታሉ ለማውጣት ዝግጅት እየተደረገ ባለበት ጊዜ ላይ ከሆስፒታሉ ሕንፃ 3ኛው ፎቅ በመስኮት እራሱን በመወርወር እራሱን ማጥፋቱ ተረጋግጧል።
Via: ታሪክ አዱኛ
4 474
+1
ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ የወሰነላቸው የ76 ዓመቷ አዛውንት ከሦስት ቀናት መዘግየት በኋላ ከእስር ተለቀቁ።
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም ከሚኖሩበት ቀበሌ ተወስደው በመቐለ ታስረው የነበሩት የ76 ዓመቷ አዛውንት ወ/ሮ አኸዛ ሕሉፍ፣ ፍርድ ቤት የዋስ መብት ቢፈቅድላቸውም ፖሊስ ትእዛዙን ሳይተገብር ቆይቶ ዛሬ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ በዋስ መለቀቃቸው ታወቀ።
የሰባ እንደርታ ወረዳ ፍርድ ቤት ሰኔ 10/ 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት አዛውንቷ በ5 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አካላት የፍርድ ቤቱን ሕጋዊ ትእዛዝ በማዘግየት ዛሬ ከ3 ቀን በኃላ ተግባራዊ አድርገውታል።
የአዛውንቷን ውክልና በመያዝ "Access for Human Rights and Social Justice" የተባለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ፍርድ ቤት በመቅረብ የተሟገተ ሲሆን፣ ግለሰቧ የተከሰሱበት "የመኸተ አዋጅ" በትግራይ የሚገኘውን የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት የሚጥስና ሕገ-መንግሥቱ የማያውቀው በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት የለውም ሲል ተከራክሯል።
ፍርድ ቤቱም የቀረበውን የሕግ መከራከሪያ በመቀበል በአዛውንቷ ላይ የቀረበውን ክስ ውድቅ በማድረግ የዋስ መብታቸው ተጠብቆ እንዲፈቱ መወሰኑ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 474
+1
#የግብር_ጉዳይ
የኢትዮጵያ የፌደራል #ጠበቆች ማህበር ዝማኔ ኩነት ወይም Update on Current Affairs በሚል ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መደብዳቤ ማህበሩ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ጋር የጠበቆች ግብር አከፋፈልና ከሙያው ልዩ ባህርይ ጋርየተጣጣመ የግብር ማዕቀፍ እንዲኖር በተከታታይ ውይይቶች ማድረጉን አስታውቋል።
በእነዚህ ውይይቶች በተደረሰው መግባባት እና በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 በተደነገገው መሰረት ሊዘጋጅ የሚገባውን እና የባለሙያዎች የተቀናሽ ወጪ መመሪያ ለማዘጋጀት የሚረዳውን የፖሊሲ ግብዓት ሰነድ ማህበሩ የጥናት ቡድን በመመደብ ባለፉት አራት ወራት ሲሰራ ቆይቶ ስራውን አጠናቆ ሰነዱን ለገንዘብ ሚኒስቴር አስረክቧል ብሏል።
ከዚያም በላይ ማህበራችን ጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ ክትትል እያደረገ ይገኛል ብሏል።
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአዋጁ መሰረት የተቀናሽ ወጪ መመሪያው ጸድቆ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ ጠበቆች አመታዊ ገቢያቸውን በህጉ መሰረት በሚያሳውቁበት ወቅት ወጪያቸው ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር እንዲያዝላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በማስገባት ውጤቱን በመከታተል ላይ ይገኛል ብሏል።
ማህበሩ የጠበቆችን ሙያ ልዩ ባህርይ የሚያንጸባርቅ ፣ ፍትሃዊ ፣ ግልጽ እና ተገማች የግብር ማዕቀፍ እንዲኖር ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር የጀመረውን ስራ በቀጣይነት አጠናክሮ ይቀጥላል በማለት ፣
እንዲሁም የመመሪያውን ዝግጅትና አፈጻጸም በቅርብ በመከታተል ለአባላቱ ተገቢውን መረጃ በየጊዜው ያደርሳል ብሏል።
የሚበረታታና የሚደገፍ ጥረት ሲሆን ውጤቱ ደግሞ በጉጉት የሚጠበቅ ነው🙏🙏🙏
የሕግ ቤት
4 474
#ለመረጃ፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መረጃዎች የሚደራጁበት እና የሚተነተኑበት (የዋጋ ንረትን ጨምሮ) የኢትዮጵያ የስታቲስቲክስ አዋጅ ተሻሽሏል! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!
4 474
+1
በኢራን በአንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በስቅላት ተቀጡ።
በኢራን፣ ቆርቬህ ከተማ ውስጥ በአንድ የ14 ዓመት ወንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች፣ በተፈረደባቸው የሞት ፍርድ መሠረት ባለፈው ሰኞ ጎህ ሲቀድ በከተማው በሚገኝ ቆርቬህ ማረሚያ ቤት ውስጥ በስቅላት እንዲሞቱ ተደርገዋል።
የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ግለሰቦች የ52 ዓመቱ ታህማሴቢ እና የ37 ዓመቱ ኩህያር አባሲ የሚባሉ የከተማው ነዋሪዎች ናቸው።
ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በነሐሴ 2024 ዓ.ም ሲሆን በሞት የተቀጡት ፈሪድ ሳዴጊ የተባለ የ14 ዓመት ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር በመፈጸምና በቪድዮ በመቅረጽ በማስፈራራት እና ገንዘብ በመቀበል ወንጀል ተከሰው ነው።
ታዳጊው ከደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት እና የስነ-ልቦና ጉዳት የተነሳ ነሐሴ 12 ቀን 2024 ዓ.ም ህይወቱን በገዛ እጁ ማጥፋቱን ሄንጋው የተባለ በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰራ ድርጅት ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 474
"የፍትሕ ተቋማት" 6 ተቋማትን ያካትትል::
1. ፍርድ ቤቶችን
2. የዐቃቤ ሕግ ተቋማትን (ፍትሕ ሚ/ር፣ ፍትሕ ቢሮ)
3. የፖሊስ ተቋማትን
4. ማረሚያ ቤቶችን
5. የጥብቅና ተቋማትን
6. የተከላካይ ጠበቆች ተቋማትን
-አንቀጽ 18(2)፣ 23
*በዚህ አዲሱ Code (ዐዋጅ ቁ. 1410/2018) የጥብቅና ሙያ የፍትሕ ሥርዓቱ የተፈጥሮ/የባሕርይ አካል እንደሆነ በግልጽ በማረጋገጥ ማንኛውም ምድራዊ ኃይል ጠበቃን ነጋዴ ነው ብሎ ሊጠራው እንደማይችል አሥምሮአል::
ስለሆነም በጠበቆች ላይ የሚፈጸም ጥቃት በፍትሕ ተቋማት/በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የተፈጸመ ጥቃት ነው::👴🏽🧓🏾
ሀይሉ ሀሰና
4 474
የመጀመሪያው የአፋን ኦሮሞ የሕግ መዝገበ ቃላት ተመረቀ *****
ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም፣ (ሀገሬ ቴቪ)፤ በኢትዮጵያ የፍትሕ ስርዓት ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያ ነው የተባለው "ዋላቡ" የአፋን ኦሮሞ የሕግ መዝገበ ቃላት ተመረቀ።
ይህ መዝገበ ቃላት የፌደራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ጀስቲስ ፎር ኦል ከተሰኘ ድርጅት ጋር ባደረጉት የጋራ ጥረትና ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ተነግሯል።
በኢትዮጵያ አብዛኛው የሕግ ትምህርት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የሚሰጥ በመሆኑ የሕግ ባለሙያዎች ወደ ስራ ሲገቡ ቃላቱን በየግላቸውና እንደተረዱት ወደ አፋን ኦሮሞ ይተረጉሙ ነበር። ይህ ወጥነት የሌለው ትርጉም በፍትሕ አሰጣጡ ጥራት ላይ የራሱን አሉታዊ ተጽእኖ ሲፈጥር መቆየቱ ተገልጿል።
መዝገበ ቃላቱ የተዘበራረቁ የሕግ ቃላትን፣ ሀረጎችን እና ጽንሰ-ሀሳቦችን ወጥ በማድረግ ለሕግ ባለሙያዎችም ሆነ ለጠቅላላው ህብረተሰብ ግልጽ የሆነ የፍትሕ ስርአት እንዲኖር ትልቅ መሰረት እንደሚጥልም ተመላክቷል።
ባሳለፍነው ዓመት የአማርኛ የሕግ መዝገበ ቃላት ወደ ሥራ መግባቱ ተገልጿል፡፡
4 474
ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዕውቅና የሰጣቸው ብሔር ብሔረሰቦች ቁጥር 76 መሆኑን አስታወቀ
ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ) - በኢትዮጵያ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች ተወካዮች መድረክ የሆነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ እስካሁን ዕውቅና የሰጣቸው ብሔር ብሔረሰቦች ቁጥር 76 ብቻ መሆኑን ገለጸ።
የምክር ቤቱ አባል አቶ ክብሩ ማሞ፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የብሔር ብሔረሰቦች ቁጥር በተለያየ አሃዝ ሲገለጽ እንደቆየ አስታውሰዋል።
ይህ ቢሆንም ምክር ቤቱ ጉዳዩን የሚከታተልና መረጃዎችን የሚያጠና ቡድን በማዋቀር ባከናወነው ጥናት 76 ብሔረሰቦች ዕውቅና እንዳገኙ አረጋግጠዋል።
ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የማንነት ዕውቅና ይሰጠን ጥያቄ በተደጋጋሚ እንደሚቀርብ የጠቀሱት አቶ ክብሩ፣ በአሁኑ ወቅት የሚነሱ ጥያቄዎች ዋነኛ ምክንያት ፖለቲካዊ ፍላጎቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።
ቀደም ሲል የአንድ ብሔር አባል የነበሩ የማኅበረሰብ ክፍሎች አለመስማማት ሲፈጠር ወይም የፖለቲካ ኃይል ማግኘት ሲፈልጉ፣ በጎሳ ተደራጅተው ራሳቸውን እንደ ብሔር በመቁጠር ጥያቄ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል። ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ጥያቄዎች ሲቀርቡለት በጥንቃቄ እንደሚመረምር ተገልጿል።
ጥያቄ አቅራቢው ማኅበረሰብ የራሱ የሆነ ማንነት፣ መልክአ ምድርና ባሕል ያለው መሆኑ ከተጠና በኋላ ውሳኔ እንደሚሰጥም አቶ ክብሩ አብራርተዋል። ለዚህም እንደ ምሳሌ የስልጤ ዞንን ጥያቄ እና የተሰጠውን ምላሽ ጠቅሰዋል።
ጉዳዩን የፖለቲካ ኃይል ማግኛ የማድረግ ዝንባሌዎች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ ክብሩ መሰል ጥያቄዎች ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ምላሽ እንደሚያገኙ አመልክተዋል።
ምክር ቤቱ ከዕውቅና በተጨማሪ የማንነት ጉዳዮችን የመመልከት፣ ሕገ-መንግሥቱን የመተርጎም፣ የገቢ ክፍፍል ቀመር የመወሰንና በጀት የመመደብ ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣን እንዳለውም ተጠቅሷል።#Ahadu
4 474
የደቦ ፍርድ ከጎዳና እስከ ዲጂታል አደባባይ ለሕግ የበላይነት የፈጠረው ስጋት✍️✍️✍️በሀገራችን እየተለመደ የመጣው #የደቦ_ፍርድ (Mob Justice) ከጎዳና እስከ ዲጂታል መድረኮች ፍትሕን ከችሎት አውጥቶ አደባባይ ላይ በመጣል የሀገርን ገጽታና የዜጎችን ደኅንነት ከፍተኛ አደጋ ላይ ጥሎ ይገኛል፡፡ በማንኛውም ሥልጡን ማኅበረሰብ ውስጥ ፍትሕ የሚሰጠው በሕግ በተቋቋሙ የፍርድ አካላት እንጂ በቲክቶክ የዲጂታል ፍረጃ ወይም በጎዳና ስሜታዊ ስብስብ አይደለም፡፡ አለሕግ ስንል፤ አወ ሕግ ስላለ ነው፡፡ ሕግ ባለበት ሀገር ደግሞ ፍትሕ የማግኘት መብት የሁሉም ሰው ነው፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 መሠረት፣ የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤት እንጂ የቲክቶክ መንደር ወይም የሰፈር ቡድን አይደለም፡፡ ችሎት ማለት ዝም ብሎ አዳራሽ ወይም ወንበር አይደለም፤ ችሎት የሥልጣን፣ የጥበብ እና የውሳኔ መፍለቂያ ነው። በሕግ ቋንቋ ችሎት ማለት፡- 1. ክርክር የሚሰማበትና የሚደመጥበት፣ 2. ማስረጃ የሚመዘንበትና እውነታው የሚመረመርበት፣ 3. በዳኞች አማካኝነት የመጨረሻ ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጥበት የተቀደሰ ሥርዓት ነው፡፡ በሕገ-መንግሥታችን አንቀጽ 20 መሠረት፣ ማንኛውም ሰው ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ የመቆጠር መብት አለው፡፡ ሆኖም ዛሬ ወንጀለኛን ማጋለጥ በሚል ሰበብ፤ የግል ቂም በቀልንና ጥላቻን ለመወጣት የሚደረጉ የዲጂታል ስም ማጥፋት ዘመቻዎች ንጹሕ ዜጎችን ለከፋ ሥነልቦናዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እየዳረጉ ነው፡፡ በተለይ በቲክቶክ እና መሰል መድረኮች ላይ ፎሎወር እና ላይክ ለማግኘት ብቻ ፖሊስ ምርመራ ሳይጀምር ሰዎችን ማዋረድና እንደወንጀለኛ መቁጠር እንዲሁም ለጥቃት ማጋለጥ በራሱ ከባድ ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ ብዙዎች በቡድን ስንሆን አንጠየቅም ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፤ ይህ ግን ትልቅ የሕግ ስህተት ነው፡፡ በወንጀል ሕጋችን መሠረት በቡድን/በደቦ ነው የፈጸምኩት የሚል ምክንያት ከቅጣት አያድንም፡፡ • የጸጥታ አካላት ተጠርጣሪዎችን ሲይዙ የሚያሳዩት ከሥነምግባር ውጭ የሆነ አያያዝ ማኅበረሰቡ ሕግን በእጁ እንዲያጠናቅቅ በዝምታ የሚሰጥ ግብዣ ይመስላል፡፡ ሕግ የሚከበረው ሕግን አክብሮ በማስከበር ነው፡፡ • ወንጀለኛን ለሕግ አሳልፎ መስጠት እንጂ፣ በእራሳችን እርምጃ መውሰድ እና ራስን እንደ ዳኛ አድርጎ መቁጠር ሌላ የከፋ ወንጀል ነው፡፡ ዛሬ በሌላው ላይ የሚፈረደው የደቦ ፍርድ፣ ነገ የእኛንም በር ማንኳኳቱ አይቀርም፡፡ መደብደብ፤ መግደል፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች/በዲጂታል ስም ማጥፋት እና ለአሉታዊ ነገር ግለሰቦችን ማነሳሳት በቡድን/በደቦ በዘመቻ ስለተፈፀመ ተጠያቂነትን አያስቀርም 1. በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 15 ፤20 ፤ 24 እና 37 መሰረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገ በስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡ ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ ይቆጠራል፡፡ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ክርክሩ ወይም ጉዳይ ለፍርድ ቤት ቀርቦ ለማስወሰን መብት አለው፡፡ 2. በወንጀል ህጋችን አንቀጽ 538 እና ተከታዮቹ መሰረት በሰው ሕይወትና አካል ላይ የሚፈጸሙ በቡድን የታገዙ ጥቃቶች ከባድ ቅጣት ያስከትላሉ፡፡ 3. የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ 958/2008 መሰረት በዲጂታል መድረክ የሰውን ስም ማጥፋትና የሐሰት መረጃ ማሰራጨት በጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ 4. የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ አዋጅ 1185/2012 መሰረት በማስረጃ ያልተደገፈ ማንኛውም ሰው ወንጀለኛ እያሉ መሰየም ዘመቻ ከባድ የወንጀል ተጠያቂነት አለው፡፡ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! የፍርድ ቤት መዶሻን በእጃችን ከመያዝ እንቆጠብ። መንግሥት የሕግ ማስከበር ቁርጠኝነቱን በተግባር ሊያሳይ፣ ማኅበረሰቡም ለሕግ ተገዥነቱን ሊያረጋግጥ ይገባል፡፡ በዚህች ምድር ስንኖር ያለ ሕግ ፍትሕ የለም፤ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! በእውነት ዓምድ እንቁም! ሚኪያስ መላክ በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አለሕግ alehig.com አለ ሕግ 0920666595 ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak https://t.me/AleHig
4 474
#ethiotelecom
ኢትዮ ቴሌኮም በኦንላይን ሰነዶችን ለማረጋገጥ የሚያስችል የዲጂታል ፊርማ አገልግሎት አስጀምሯል።
ኢትዮ ቴሌኮም ተገልጋዮች በአካል ሳይገኙ ሰነዶችን በዲጂታል መንገድ እንዲፈርሙና ህጋዊ ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያስችለውን "ቴሌሳይን" (teleSign) የተሰኘ ሶሉሽን በይፋ ስራ አስጀምሯል።
- ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣
- ከፍትህ ሚኒስቴር
- ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር በመተባበር የቀረበው ይህ ሲስተም፣ ተገልጋዮች ካሉበት ሆነው የመንግስት አገልግሎቶችን በኦንላይን እንዲያገኙ ለማስቻል ያለመ ነው።
በተለይ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአካል ኤምባሲ ወይም የውክልና መስጫ ቢሮዎች ሳይገኙ የህጋዊ ውክልና ለመስጠትና ለተለያዩ ጉዳዮች የሚገጥማቸውን የጊዜና የጉዞ ወጪ ችግር ለመቅረፍ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
"ቴሌሳይን" ዜጎች ካሉበት ሆነው የሰነድ ማረጋገጥ፣ የውክልና ስልጣን እና የጠበቃ ፈቃድ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል።
በዲጂታል መንገድ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና አገልግሎቶች መካከል የውክልና ስልጣን አንዱ ሲሆን፤ ይህም የዲያስፖራው ማህበረሰብም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች በአካል ኤምባሲ ወይም ቢሮ ሳይገኙ የውክልና ስልጣን ለመስጠትም ሆነ ለማንሳት ያስችላል።
በተጨማሪም ድርጅቶችና ዜጎች ማንኛውንም ህጋዊ ሰነድ ካሉበት ቦታ ሆነው በዲጂታል መንገድ እንዲያረጋግጡ የሚያስችል የሰነድ ማረጋገጥ አገልግሎትን ያካተተ ሲሆን፤ የህግ ባለሙያዎችም የጠበቃ ፈቃድ ለማውጣትና ለማደስ የሚጠቀሙበት የተቀናጀና ወረቀት-አልባ አሠራር በሶሉሽኑውስጥ መካተቱ ተነግሯል።
ይህ የዲጂታል ፊርማ መድረክ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘ የቪዲዮ ማንነት ማረጋገጫን የሚጠቀም ሲሆን፣ ከብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር በመናበብም የፊርማውን ትክክለኛነት ያረጋግጣል።
ተገልጋዮች በቴሌብር አማካኝነት ክፍያቸውን ፈጽመው በቀን 24 ሰዓት አገልግሎቱን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል ለቀናት ይወስድ የነበረውን አሰራር ወደ ጥቂት ደቂቃዎች ዝቅ እንደሚያደርገው ተገልጿል።
አገልግሎቱ በኢትዮጵያ አዋጅ ቁጥር 1072 ለዲጂታል ፊርማ ከተቀመጠው ህጋዊ ማዕቀፍና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርዶች ጋር የተጣጣመ በመሆኑ በህግ ፊት ሙሉ ተቀባይነት እንዳለው ይፋ በማድረጊያ ስነስርዓቱ ወቅት ተነግሯል።
ተገልጋዮች የቴሌሳይን የሞባይል መተግበሪያን ወይም telesign.et የተሰኘውን የኩባንያውን ድረ-ገጽ በመጠቀም የዲጂታል ፊርማ አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።.
@tikvahethiopia
4 474
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ዜጎች የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
------------------------
(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 25፣ 2018 ዓ.ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ሳቢያ ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ10 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።
የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶን ጨምሮ፣ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር፣ የምክር ቤት አባላትና የጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች በዞኑ በአካል ተገኝተው የምክር ቤቱን አጋርነት አሳይተዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ሎሚ በዶ፤ በዞኑ በተከሰተው አደጋ ምክንያት በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናቸውን ገልፀው ለተጎጂ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።
ምክር ቤቱ ያለውን አጋርነት ለማሳየትም የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጋሞ ዞን አስተዳደር ያስረከቡ ሲሆን ዜጎቸን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ተግባር ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) ምክር ቤቱ ላሳየው ፈጣን ምላሽና አጋርነት በዞኑ ሕዝብና በአስተዳደሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ድጋፎች የተረጂዎችን ሞራል ከመገንባት ባለፈ፣ መልሶ የማቋቋም ሥራውን እንደሚያቀላጥፉ ጠቁመዋል።
(በ አገሪቱ ጌቴ)
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።
4 474
+2
" በዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መጥቷል፣ እስካሁንም በዜጎችና በሀገር ሀብት ላይ የ3.1 ቢሊየን ብር ጉዳት አድርሷል " - የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ የተገለጸ ሲሆን፤ ችግሩን ለመከላከል የሚያስችል የጥናታዊ ጽሑፍ እና ሀገራዊ የምክክር መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መምጣቱና እስካሁንም በዜጎችና በሀገር ሀብት ላይ የ3.1 ቢሊየን ብር ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
እንደ ፌዴራል ፖሊስ መረጃ፤ በ2013 ዓ.ም 16 ብቻ የነበረው የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር የወንጀል መዝገብ በ2017 ዓ.ም ወደ 1,647 አድጓል።
ይህም የወንጀሉን መጠንና የደረሰውን ጉዳት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረው መሆኑ ተመላክቷል።
በሀገሪቱ ከ18 ትሪሊዮን ብር በላይ አመታዊ የዲጂታል የገንዘብ ዝውውር መኖሩ ለዘርፉ እድገት ማሳያ ቢሆንም ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚፈጸሙ የማጭበርበር፣ የመረጃ ስርቆትና ማንነትን የመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባራት ግን ስጋት መሆናቸው ተገልጿል።
ይህንን እየተስፋፋ የመጣ የደህንነት ስጋት ለመከላከል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ስልታዊ መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ ሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ እንደገለጹት፣ ሀገራችን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ በምታደርገው ጉዞ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት መጨመሩ ለዜጎች ምቾትን ቢፈጥርም፣ ቴክኖሎጂን ከጥቃት የመከላከል አቅምን ማሳደግና የዜጎችን ንቃተ-ሕሊና ማጎልበት አሁን ላይ " የህልውና ጉዳይ " ሆኗል ብለዋል።
የፍትሕ ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሃና አርአያሥላሴ በበኩላቸው፣ የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር የዜጎችን ሀብት ብቻ ሳይሆን በፋይናንስ ስርዓቱ ላይ ያለውን እምነት የሚሸረሽር በመሆኑ፣ ጠንካራ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በማድረግ ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 474
የኬንያው ኬሲቢ በኢትዮጵያ የሚገዛውን ባንክ ለየ
በሀብት መጠኑ የኬንያ ቁንጮ የሆነው ኬሲቢ ግሩፕ፣ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናቆ የሚገዛውን የሀገር ውስጥ ባንክ መለየቱን በይፋ አስታውቋል። ባንኩ በ2025 ያስመዘገበው የ544 ሚሊዮን ዶላር ሪከርድ ትርፍ ለዚህ ትልቅ ኢንቨስትመንት ጉልበት ሆኖታል። ኬሲቢ አዲስ ባንክ ከመክፈት ይልቅ ነባር ባንክን በመግዛትና የአብላጫ ባለቤትነት ድርሻን በመያዝ፣ የኢትዮጵያን 120 ሚሊዮን ሕዝብ ያቀፈ ግዙፍ ገበያ በአጭር ጊዜ ለመቆጣጠር አቅዷል።
ባንኩ የገዛውን የኢትዮጵያ ባንክ ማንነት በዚህ ዓመት መጨረሻ ይፋ የሚያደርግ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሂደቱን እስከ 2026 ማብቂያ አጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቃል። ኬሲቢ እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሁሉ ትኩረቱን በዲጂታልና በሞባይል ባንክ አገልግሎት ላይ በማድረግ ሰፊ የቅርንጫፍ ግንባታ ወጪዎችን ለማስቀረት ወጥኗል። ይህ የኬሲቢ ግስጋሴ እንደ ስታንዳርድ ባንክ እና አብሳ ግሩፕ ያሉ ሌሎች የአፍሪካ የፋይናንስ ግዙፎችም ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት አይናቸውን በጣሉበት ወቅት የተሰማ ትልቅ ዜና ሆኗል።
4 474
የጠበቃ አበል ክርክር ከቀረበበት ሀብት ግምት 10 በመቶ መብለጥ ይችላል?
ሰበር መዝገብ ቁጥር.94364
መጋቢት 10 ቀን 2005
በተለምዶ የጠበቆች አበል የክርክሩ ንብረት ግምት 10 በመቶ ተደርጎ ይወሰዳል ፡፡ ይሁን እንጂ የጠበቆች አበል ከክርክሩ ንብረት ግምት ከ10 በመቶ መብለጥ የለበትም የሚል ህግ የለም፡፡
ስለሆነም አንድ ደንበኛ ከጠበቃ ጋር ከ10 በመቶ በላይ ለመክፈል ስምምነት ካደረገ አገልግሎቱን ከተቀበለ በኋላ ከ10 በመቶ በላይ መሆን የለበትም በሚል አልከፍልም ማለት ወይም ጉዳዩን ወደ ህግ ወስዶ ይቀነስ ሊል የሚችልበት አግባብ የለም፡፡ ከ10 በመቶ መብለጥ የለበትም የሚል ክርክር በራሱ ተቀባይነት የለውም ፡፡
ነገር ግን ፍቤቶች ክርክሩ የሚወስደውን ጊዜ ፣ የሚጠይቀውን ድካም የጉዳዩ አዲነትና አስቸጋሪነትን ለተመሳሳይ ጉዳይ የሚከፈለውን እና መሰል መመዘኛዎች አይቶ በስምምነት የተገለጸውን ከ10 በመቶ በላይም ሆነ በታች የሆነ የጠበቃ አበል ሊቀንሱ ይችለሉ፡፡
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
