ar
Feedback
Renaissance School®

Renaissance School®

الذهاب إلى القناة على Telegram

Renaissance School

إظهار المزيد
1 951
المشتركون
+124 ساعات
+97 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content

#Update የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈ
#Update የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል። የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡  1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦ - እንግሊዘኛ፣ - ሒሳብ፣ - እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ - ኬሚስትሪ፣ - ፊዝክስና ባዮሎጂ ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦ - እንግሊዘኛ፣ - ሒሳብ፣ - እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ - ታሪክ፣ - ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው። 2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡ 3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ 4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ 5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር 💠 🔴ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ! ✈️https://t.me/Tmhrt_Minister ✈️https://t.me/Tmhrt_Minister

#National_ID የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (Nationa
#National_ID የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል። " ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል። " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል። ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦ - የተማሪ ቤተሰብ - መምህራን - የትምህርት አመራሮች - የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። #National_ID ትምህርት ሚኒስቴር 💠 🔴ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ! ✈️https://t.me/Tmhrt_Minister ✈️https://t.me/Tmhrt_Minister

ሬነሳንስ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ልጆቻችሁን ለምታስተምሩ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ
ጉዳዩ፡- የስብሰባ ጥሪ
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሚመለከት መመሪያና ስትራቴጂክ እቅድ ስለወረደ በዚህ ላይ ለመወያየት ቅዳሜ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቤተ መፅሐፍት እንድትገኙ በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- በስብሰባው ላይ ካልተገኙ ጉባኤውን በተካፈሉት/በተገኙት ውሳኔ ሙሉ ድጋፍ የሰጣችሁና እንደተስማማችሁ ተደርጎ ት/ቤቱ የሚወስን መሆኑን እንገልፃለን፡፡

photo content

ሬነሳንስ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አዲስ አበባ
ለተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች የትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 15/2018 ዓ.ም ባወረደው መመሪያ መሰረት አጠቃላይ የተማሪዎች እና የወላጅ ፕሮፋይል ተሞልቶ እንዲላክ የተጠየቀ በመሆኑ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመጠቀም ገብታችሁ ቅጹን እስከ ሐሙስ መስከረም 29/2018 ዓ.ም ሞልታችሁ እንድትልኩልን ከአደራ ጭምር መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ ት/ቤቱ link 👉🏽 https://bit.ly/RISData

photo content

የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ። ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል። 1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የRemedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት አለባቸው። 2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ። የመቁረጫ ነጥብ ፦ ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216 ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204 ➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165 #MoE

ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባ
ዓርብ መስከረም 23/2018 ዓ/ም የኢሬቻ በዓል ዋዜማ በመሆኑና መንገዶች ስለሚዘጋጉ ሙሉ ቀን ት/ት የማይኖር መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ

photo content

photo content

Grade 12 Social Students Placement Choice.pdf5.69 KB

photo content

Grade 12 Natural Students Placement Choice.pdf6.47 KB

photo content

This is your university placement choice. If you would like to change any of your selections, please come to the school IT Lab between 3:00 – 6:00 local time. Renaissance School

This is your university placement choice. If you would like to change any of your selections, please come to the school IT Lab between 3:00 – 6:00 local time.

photo content

photo content