Natinael Mekonnen
ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን Facebook.com/natnaelmekonnen.et Instagram.com/natnaelmekonnen21 Telegram https://t.me/NatinaelMekonnen21
إظهار المزيد7 968
المشتركون
+2624 ساعات
+787 أيام
+5630 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
12:03
Video unavailableShow in Telegram
የፌደራል ፖሊስ ዲጂታል ሪፎርም ስራዎች ዜጎች በወንጀል መከላከል ስራ ይበልጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ እድል የፈጠሩ ናቸው::
ጠሚ አቢይ አህመድ
❤ 2
ሩሲያ ከሞስኮው የሙዚቃ ድግስ ጥቃት ጋር በተያያዘ 20 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አዋለች
ባለፈው መጋቢት ወር ለተፈጸመው ለዚህ ጥቃት አይኤስ-ኮራሳን ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ገልጾ ነበር።
https://am.al-ain.com/article/russia-arrests-20-suspects-in-connection-crocus-mall-attack
ሩሲያ ከሞስኮው የሙዚቃ ድግስ ጥቃት ጋር በተያያዘ 20 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አዋለች
የሩሲያው ኤፍኤስቢ ኃላፊ ከጥቃቱ ጀርባ የዩክሬን እጅ አለበት የሚለውን ቀደም ሲል የቀረበውን ክስ ደግመውታል
👍 1
በጎጃም ኮማንድ ፖስት የተሰማራው ክፍለጦር በወሰደው እርምጃ 32 የፅንፈኛው አባላት ሲደመሰሱ 16 መቁሰላቸውን አስታወቀ።
ክፍለጦሩ በተሰማራበት የሰሜን ጎጃም ዞን መራዊ ወረዳ ከብራቃት እስከ ሪም ከተማ ባደረገው አሰሳ 32 የፅንፈኛው አባላት ሲደመሰሱ 16 በማቁሰል 10 ኤ ኬ ኤም መሳሪያ ተማርኳል ።
በርካታ የድሽቃ ፣ የፒ ኬ ኤም እና የኤ ኬ ኤም ጥይቶች ፣ 40 የደረት ትጥቆችና አልባሳት ፣ አንድ ከህዝብ ተዘርፎ በጫካ የተደበቀ ተሽከርካሪ ፣ 10 ሞተር ሳይክሎች፣ 1 ጀኔሬተር፣ 2 የላብላቶሪ ቴሌስኮፕ ፣ 4 ካርቶን የተለያዩ መድሃኒቶች፣ 10 ፍራሽ፣ 10 ኩንታል የእንጀራ ድርቆሽ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን በቁጥጥር ስር አውሏል ።
በክፍለጦሩ የተሰማሩ ሬጅመንቶች ብራቃት፣ ሮብ ገበያ፣ ቦሮቦር ስላሴ ገዳም፣ ዴንሳ ባታ፣ ኢዞራ አካባቢዎች ባካሄዱት ስምሪት ውጤት መገኘቱን የገለፁት የክፍለጦር አዛዥ ኮሎኔል አለሜ ታደለ ፣ ከአዴት - ባህር ዳር ፅንፈኛው የሚዘጋቸውን የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በማስከፈት ህብረተሰቡ እንዲገለገል አድርገናል ሲሉ ገልፀዋል።
ኮሎኔል አለሜ ታደለ ክፍለጦሩ በቀጣይ ስምሪቶች ከአካባቢው የክልሉ የፀጥታ ሀይልና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት በፅንፈኛው ላይ የምንወስደው ፈልጎ የመደምሰስና የማፅዳት ኦፕሬሽኖች ይቀጥላሉ ብለዋል።
❤ 6👍 4
10:26
Video unavailableShow in Telegram
ኢትዮጵያ ውስጥ በፍጥነት ሪፎሪም ያደረገ ተቋማት ውስጥ አንዱ ፌደራል ፖሊስ ነው:: የፌደራል ፖሊስ ወንጀልን በመከላከል ረገድ እያሳየ ያለው ጥረት እና በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የሰለጠኑ ሃገራት የደረሱበት ቴክኖሎጂዎች ላይ ለመድረስና ለመዘመን እያደረገ ያለው ቀልጣፋና ዉጤታማ ሥራዎቹ የሚደነቅ ነው::
የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ እና የድሬዳዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በሀዋሳ ከተማ ተገናኙ።
ከዛሬ ሁለት ወር በፊት የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ የፀጥታ ልዑካናቸውን ይዘው በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የፀጥታው ሁኔታ የልምድ ልውውጥ ያደረጉ ሲሆን አሁን ደግሞ አቶ ከድር ጀዋር በሀዋሳ ከተማ በመገኘት ጠንካራ ያሉት የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ሂደትን ተመልክዋል።
አቶ ከድር ጀዋር ወንድማማችነት የማበልፀግ በርካታ ስራዎችንን እንሰራልን የሃገር የዜጎቿን ደህንነት ከአሁኑ የበለጠ ጠንካራ የፀጥታ ዘርፍ መገንባት የሚያስፈልገው የጋራ ትብብር ማድረግ ይገባል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ አክለውም ድሬዳዋ ማለት ሁለተኛዋ ቤታችንን ናት ድሬዳዋ ከተማ ማለት እንደ ሀዋሳ ከተማ ሁሉ የሁሉም ብሔር መናኸሪያ በመሆኗ ሁሉን አካታች ተቆማትንን ለመገንባት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ ብልፅግና መንግስታችንን በፈጠረው ሁሉን አካታችነትን እና የጋራ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ከሁሉም አከባቢዎች ጋር እና መንግስት ጋር ለህዝባችንን ጥቅም በሁሉም መስክ የምስራ ይሆናል ብለዋል።
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አቶ ጀዋር ከድር የወልቂጤ ከተማ እና የድሬዳዋ ከተማ ጨዋታን በሜዳ ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን ድሬዳዋ ከተማ በሰፊ የጎል ልዩነት አሸናፊ የሆኑ ሲሆን ለከንቲባ ከድር የሲዳማ ቡና እና የሀዋሳ ከነማ ማለያ በስማቸው በስጦታ መልክ ተሰጥቷቸዋል።
👍 9❤ 1
أرشيف المشاركات