ar
Feedback
የሱሀቦች ዘመን

የሱሀቦች ዘመን

الذهاب إلى القناة على Telegram
3 847
المشتركون
+324 ساعات
+127 أيام
+5330 أيام
أرشيف المشاركات
🕌 ቢላል ኢብን ረባህ (ረዐ) – የማይናወጥ እምነት ✨ ቢላል ኢብን ረባህ (ረዐ) በኡመያ ኢብን ኸለፍ እጅ ከባድ ስቃይ ቢደርስበትም እምነቱን ፈጽሞ አልተወም። በሞቃታማው ፀሐይ ስር ትልቅ ድንጋይ
🕌 ቢላል ኢብን ረባህ (ረዐ) – የማይናወጥ እምነት ✨ ቢላል ኢብን ረባህ (ረዐ) በኡመያ ኢብን ኸለፍ እጅ ከባድ ስቃይ ቢደርስበትም እምነቱን ፈጽሞ አልተወም። በሞቃታማው ፀሐይ ስር ትልቅ ድንጋይ በደረቱ ላይ ተጭኖበት ሳለ፣ "አሐድ! አሐድ!" (አላህ አንድ ነው! አላህ አንድ ነው!) ብሎ መጮሁን ቀጠለ። ይህ ጽናት በእስልምና ታሪክ ውስጥ የትዕግስት፣ የእምነት እና የአላህን ፍቅር የሚያሳይ ከታላላቅ ምሳሌዎች አንዱ ሆኗል። ኋላም አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረዐ) ለአላህ ብለው ነፃነቱን ገዝተው ነፃ አወጡት። 📖 ማስታወሻ:"የእምነት ጣፋጭነት የስቃዩን መራራነት አስረሳኝ" (حلاوة الإيمان أنستني مرارة العذاب) ሚለው አባባል ቆንጆ ትርጉም ቢኖረውም፣ ትክክለኛ ሐዲስ ወይም ከቢላል (ረዐ) በተረጋገጠ ሰንሰለት የተዘገበ ሐዲስ አይደለም። አላህ በእውነት ላይ ጸንተን እንድንቆይ ያድርገን። 🤲 #BilalIbnRabah #BilalRA #EthiopianMuslims #ኢስላም #ቢላል #IslamicHistory #Muslim #TikTokIslam http://tiktok.com/@goldenislamicage

በደስታ። ይህ የተጅዊድ መሠረታዊ ትምህርት በተጨማሪ የሚረዳዎት ነው፦ የተጅዊድ ዓላማ ቁርአንን እንደተወረደ በትክክል ማንበብ። የእያንዳንዱን ፊደል መብት (حق الحرف) እና ባህሪ (مستحق الحرف) መስጠት። የፊደላት ባህሪያት (صفات الحروف) ከተጅዊድ ውስጥ አስፈላጊ የሆኑ ባህሪያት፦ همس (ሀምስ) – የቀለለ ድምፅ جهر (ጀህር) – ጠንካራ ድምፅ شدة (ሺዳ) – ጠንካራ መዝጋት رخاوة (ርኻዋ) – ለስላሳ ፍሰት استعلاء (ኢስቲዕላእ) – ወፍራም (ከባድ) ድምፅ استفال (ኢስቲፋል) – ቀጭን (ቀላል) ድምፅ ወፍራም የሚነበቡ ፊደላት (حروف التفخيم) እነዚህን ፊደላት "خص ضغط قظ" በሚለው ቃል ያስታውሳሉ፦ خ، ص، ض، غ، ط، ق، ظ እነዚህ በከባድ (ወፍራም) ድምፅ ይነበባሉ። ቀጭን የሚነበቡ ፊደላት (حروف الترقيق) ከላይ ከተጠቀሱት 7 ፊደላት ውጭ ያሉት ፊደላት በአብዛኛው ቀጭን ድምፅ ይነበባሉ። የቀልቀላ ፊደላት (حروف القلقلة) "قطب جد" በሚለው ቃል ይታወሳሉ፦ ق، ط، ب، ج، د እነዚህ ፊደላት ሱኩን ሲኖራቸው ትንሽ የሚያንጸባርቅ ድምፅ ይሰማል። የጉና ፊደላት (حروف الغنة) ن م እነዚህ ፊደላት ሸዳ ሲኖራቸው በአፍንጫ የሚወጣ ድምፅ (غنة) ይኖራቸዋል። ምክር ተጅዊድን ለመማር በየቀኑ 10–15 ደቂቃ ልምምድ ያድርጉ፣ ከተካነ አስተማሪም ሆነ ከቃሪእ ጋር በመስማትና በመከተል ያንብቡ። ይህ አነባበብዎን በፍጥነት ያሻሽላል።

የአረብኛ ተጅዊድ (التجويد) ማለት ቁርአንን እንደተወረደ በትክክል የመንበብ ሕጎችን ማወቅ ነው። አጠቃላይ ትምህርቱ ይህን ይጨምራል፦ 1. የአረብኛ ፊደላት (حروف الهجاء) አጠቃላይ 29 ፊደላት ናቸው፦ ا، ب، ت، ث، ج، ح، خ، د، ذ، ر، ز، س، ش، ص، ض، ط، ظ، ع، غ، ف، ق، ك، ل، م، ن، هـ، و، ي، ء 2. ሐረካት (الحركات) َ ፈትሓ (Fatḥah) = بَ ِ ከስራ (Kasrah) = بِ ُ ደማ (Ḍammah) = بُ 3. ተንዊን (التنوين) ً ፈትሐተይን = بً ٍ ከስረተይን = بٍ ٌ ደመተይን = بٌ 4. ሱኩን (السكون) ፊደሉ ያለ እንቅስቃሴ ይነበባል፦ بْ 5. ሸዳ (الشدة) ፊደሉ ሁለት ጊዜ የተጠናከረ ይነበባል፦ بّ 6. ማድ (المد) የድምፅ ማራዘሚያ፦ ا و ي 7. የፊደላት መውጫ (مخارج الحروف) ፊደላቱ ከሚወጡበት ቦታ ይማራሉ፦ ጉሮሮ ምላስ ከንፈር አፍንጫ የአፍ ውስጥ 8. የተጅዊድ ዋና ሕጎች ኢዝሃር (إظهار) ኢድጋም (إدغام) ኢቅላብ (إقلاب) ኢኽፋእ (إخفاء) ቀልቀላ (قلقلة) ጉና (غنة) ማድ (المدود) ወቅፍ (الوقف والابتداء) ለጀማሪዎች የሚመከረው የመማር ቅደም ተከተል የአረብኛ ፊደላት ሐረካት ሱኩን ሸዳ ተንዊን ማድ መኽራጅ (የፊደላት መውጫ) የተጅዊድ ሕጎች ከዚያም ቁርአንን በተግባር መንበብ ቃዒደቱ ኑራንያ (القاعدة النورانية) ወይም ቃዒደቱ በግዳዲያ (القاعدة البغدادية) በመጀመር ተጅዊድን ለመማር በጣም የተሻሉ መንገዶች ናቸው።

📖"አላህም በጉዳት ቢነካህ ለእርሱ (ለጉዳቱ) ከእርሱ በቀር ሌላ #አስወጋጅ የለም፡፡ በበጎም ነገር ቢነካህ እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 6፡17)፡፡ 📖"አላህም ጉዳትን ቢያደርስብህ ከእርሱ ሌላ ለእርሱ #ገላጭ የለውም፡፡ በጎንም ነገር ቢሻልህ ለችሮታው መላሽ የለም፡፡ ከባሮቹ የሚሻውን በእርሱ ይለይበታል፡፡ እርሱም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡" (ሱረቱ ዩኑስ 10፡107)፡፡ 📖"ከአልረሕማን (ቅጣት) በሌሊትና በቀን #የሚጠብቃችሁ ማነው? በላቸው፤ በውነቱ እነሱ ከጌታቸው ግሣጼ (ከቁርአን) ዘንጊዎች ናቸው።" (ሱረቱል አንቢያእ 21፡42) 📖"ከአላህ ሌላ የምትግገዟቸውን (ጣዖታት) አያችሁን? (ነገሩኝ) አላህ በጉዳት ቢፈልገኝ እነሱ ጉዳቱን #ገላጮች ናቸውን? ወይስ በችሮታው ቢፈቅደኝ እነርሱ ችሮታውን አዘጋጆች ናቸውን? በላቸው። አላህ በቂዬ ነው፤ በርሱ ላይ ተመኪዎች ይመካሉ፤ በል።" (ሱረቱ-ዙመር 39፡38)፡፡ 📖"እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ፣ በእርግጥ ካዱ፤ የመርየምን ልጅ አልመሲሕን እናቱንም በምድር ያለንም ሁሉ ለማጥፋት ቢሻ ከአላህ #ማዳንን የሚችል ማነው? በላቸው።" (ሱረቱል ማኢዳህ 5፡17)፡፡ 📖"ከየብስና ከባሕር ጨለማዎች በግልጽና በምስጢር የምትጠሩት ስትኾኑ «ከነዚህ ቢያድነን በእርግጥ ከአመስጋኞች እንኾናለን (ስትሉ) የሚያድናችሁ ማነው» በላቸው፡፡አላህ ከሷና ከጭንቅም ሁሉ ያድናችኋል፡፡ ከዚያም እናንተ ታጋራላችሁ በላቸው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 6፡63-64)፡፡ 📖በጣም የሚገርመው ነገር አንድን ነገር ስትፈራው ከሱ ትሸሻለህ፡ አላህን ስትፈራው ግን ወደሱ ትጠጋለህ፡- "ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለናንተ ከርሱ ግልፅ አስጠንቃቂ ነኝና (በላቸው)።" (ሱረቱ-ዛሪያት 51፡50)፡፡ 📜ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ አለ፡- "ከአላህ መልክተኛ ኋላ ሁኜ እያለ እንዲህ አሉኝ፡- አንተ ልጅ ሆይ! እኔ እነዚህን ቃላት አስተምርሃለሁ፡፡ አላህን (ህጉን) ጠብቅ ይጠብቅሃልና፣ አላህን (ህጉን) ጠብቅ ፊት ለፊትህ ታገኘዋለህና፣ ስትለምን አላህን ብቻ ለምን፣ እገዛን ስትሻ በአላህ ብቻ ታገዝ፣ ሕዝቦች አንተን ለመጥቀም ቢሰባሰቡ አላህ የጻፈልህን ካልሆነ በስተቀር በምንም ነገር ሊጠቅሙህ እንደማይችሉ ዕወቅ፡፡ አንተን ለመጉዳትም ቢሰባሰቡ አላህ የጻፈብህን ካልሆነ በስተቀር በምንም ነገር ሊጎዱህ እንደማይችሉ እወቅ፡፡" (ቲርሚዚይ 2516)፡፡ 📖"እላንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገቢዉን መጠንቀቅ ተጠንቀቁት፤ እናንተም ሙስሊሞች ሆናችሁ እንጅ አትሙቱ።" (ሱረቱ አሊ-ዒምራን 3፡102) 📖"እላንተ ሰዎች ሆይ! ያንን ከአንዲት ነፍስ (ከአደም) የፈጠራችሁን… ጌታችሁን ፍሩ።" (ሱረቱ-ኒሳእ 4፡1) 📖"እላንተ ያመናችሁ ሆይ አላህን ፍሩ፤ ትክክለኛውንም ንግግር ተናገሩ።" (ሱረቱል አሕዛብ 33፡70)፡፡ ━━━━━🍃🌸🍃━━━━━ 🌺 የሱሀቦች ዘመን 🌺 ━━━━━🍃🌸🍃━━━━━ https://t.me/lYllYi ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ ✍ ሙሀመድ & ሳኒ ይመር ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA

የአረበኛ ፊደላት (ሂጃኢያ) መጀመሪያ እንዲህ ናቸው፦ ا = አሊፍ (Alif) ب = ባ (Bā') ت = ታ (Tā') ث = ሳ / ታ በነጥብ ሶስት (Thā') ج = ጂም (Jīm) ح = ሐ (Ḥā') خ = ኸ (Khā') د = ዳል (Dāl) ذ = ዛል (Dhāl) ر = ራ (Rā') ز = ዛይ (Zāy) س = ሲን (Sīn) ش = ሺን (Shīn) ص = ሷድ (Ṣād) ض = ዷድ (Ḍād) ط = ጧ (Ṭā') ظ = ዟ (Ẓā') ع = ዐይን ('Ayn) غ = ገይን (Ghayn) ف = ፋ (Fā') ق = ቃፍ (Qāf) ك = ካፍ (Kāf) ل = ላም (Lām) م = ሚም (Mīm) ن = ኑን (Nūn) هـ = ሃ (Hā') و = ዋው (Wāw) ي = ያ (Yā') በቅደም ተከተል ለማንበብ፦ ا ب ت ث ج ح خ د ذ ر ز س ش ص ض ط ظ ع غ ف ق ك ل م ن هـ و ي

#ዒሳ (ዐ,ሰ) አንድ ትልቅ ተራራ ላይ አላህን እያመለከ ሳለ ኢብሊስ መጣ ወደ ዒሳም ጠጋ ብሎ፦"አንተ አይደለህ እንዴ ሁሉ ነገር በቀዳ እና በቀደር ነው እያልክ የምትሰብከው" አለው። ዒሳም፦"አዎና" አለው ኢብሊስም፦" እስቲ ከዚህ ተራራ ዝለል'ና ቀደር ነው በል" አለው።ዒሳም፦" አንተ እርጉም..! አላህ ባሪያዎቹን ይፈትናል እንጂ ባሪያዎች አላህን አይፈትኑም" አለው። (ሱረቱ አል-ኢስራእ - 61,62) 📜ለመላእክትም ለአደም ስገዱ ባልናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ ወዲያውም ሰገዱ፤ ኢብሊስ ብቻ ሲቀር፡፡ «ከጭቃ ለፈጠርከው ሰው እሰግዳለሁን» አለ፡፡«ንገረኝ ይህ ያ በእኔ ላይ ያበለጥከው ነውን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ብታቆየኝ ዘሮቹን ጥቂቶች ሲቀሩ ወደ ስህተት በእርግጥ እስባቸዋለሁ» አለ፡፡ (ሱረቱ አል-ኢስራእ - 63,64,65) 📜(አላህም) አለው «ኺድ፤ ከእነሱም የተከተለህ ገሀነም የተሟላች ቅጣት ስትኾን ፍዳችሁ ናት፡፡«ከእነሱ የቻልከውንም ሰው በድምጽህ አታል፡፡ በእነሱም ላይ በፈረሰኞችህ፣ በእግረኞችህም ኾነህ ለልብ፡፡ በገንዘቦቻቸውም፣ በልጆቻቸውም ተጋራቸው፣ ተስፋ ቃልም ግባላቸው፡፡ ሰይጣንም ማታለልን እንጂ ተስፋ ቃልን አይገባላቸውም፡፡«ባሮቼ በእነሱ ላይ ፈጽሞ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ መጠጊያም በጌታህ በቃ፡፡» ━━━━━🍃🌸🍃━━━━━ 🌺 የሱሀቦች ዘመን 🌺 ━━━━━🍃🌸🍃━━━━━ ✍ ሙሐመድ ይመር ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ https://t.me/sohabaa

#ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዳወሱት አንድ የአይሁድ ሰው እንዲህ አላቸው፡ - የምእመናን አዛዥ ሆይ! በመጽሐፋችሁ ውስጥ አንድ አንቀጽ አለ፣ ታነቡታላችሁ። (ግና) እኛ የአይሁድ ማህበረሰብ አባላት ይህ አንቀጽ እኛ ላይ ቢወርድ ኖሮ ያንን ቀን ክብረ-በአል (ዒድ) አድርገን እንይዘው ነበር፡ ' 'የትኛዋ አንቀጽ ነች? በማለት ጠየቁ ዑመር።    #ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ ። ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ። (ቁርዓን 5፡3)    #ዑመርም (ረ.ዐ) (መልስ) ሰጡ ያለምንም ጥርጥር ያንን ቀን እናውቀዋለን። (አንቀጹ) በነቢዩ ላይ የወረደበትን ቦታም (እናውቃለን)።፡በዕለተ ጁሙዓ በዐረፋ በቆሙበት ወቅት ነው። #ጀሪር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ነበርን። ሙሉ ጨረቃ ባለበት ምሽት ወደ ጨረቃ ተመለከቱ “ይህን ጨረቃ (ያለምንም ችግር) እንደምትመለከቱት ሁሉ (በገነት ውስጥም) ጌታችሁን ያለ አንዳች ግፊ ትመለከቱታላችሁ።” ስለዚህ (ይህን ዕድል ለማግኘት) ፀሀይ ከመውጣቷ (ሱቡሒ) እና ከመግባቷ በፊት (ዐስር) ባሉ ሶላቶች ላለመሸነፍ በርቱ። (በእንቅልፍና በሕይወት እንቅስቃሴ አትታለሉ።) ከዚያም ይህን (አንቀጽ) አነበቡ፡ “ጌታህንም ከማመስገን ጋር ፀኃይ ከመዉጣቷ. በፊት ከመግባቷም በፊት አወድሰው።' ' (ቁርዓን 50-39) ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ ✍ሙሀመድ  & ሳኒ ይመር ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ https://t.me/sohabaa

#ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዳወሱት አንድ የአይሁድ ሰው እንዲህ አላቸው፡ - የምእመናን አዛዥ ሆይ! በመጽሐፋችሁ ውስጥ አንድ አንቀጽ አለ፣ ታነቡታላችሁ። (ግና) እኛ የአይሁድ ማህበረሰብ አባላት ይህ አንቀጽ እኛ ላይ ቢወርድ ኖሮ ያንን ቀን ክብረ-በአል (ዒድ) አድርገን እንይዘው ነበር፡ ' 'የትኛዋ አንቀጽ ነች? በማለት ጠየቁ ዑመር።    #ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ ። ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ። (ቁርዓን 5፡3)    #ዑመርም (ረ.ዐ) (መልስ) ሰጡ ያለምንም ጥርጥር ያንን ቀን እናውቀዋለን። (አንቀጹ) በነቢዩ ላይ የወረደበትን ቦታም (እናውቃለን)።፡በዕለተ ጁሙዓ በዐረፋ በቆሙበት ወቅት ነው። #ጀሪር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ነበርን። ሙሉ ጨረቃ ባለበት ምሽት ወደ ጨረቃ ተመለከቱ “ይህን ጨረቃ (ያለምንም ችግር) እንደምትመለከቱት ሁሉ (በገነት ውስጥም) ጌታችሁን ያለ አንዳች ግፊ ትመለከቱታላችሁ።” ስለዚህ (ይህን ዕድል ለማግኘት) ፀሀይ ከመውጣቷ (ሱቡሒ) እና ከመግባቷ በፊት (ዐስር) ባሉ ሶላቶች ላለመሸነፍ በርቱ። (በእንቅልፍና በሕይወት እንቅስቃሴ አትታለሉ።) ከዚያም ይህን (አንቀጽ) አነበቡ፡ “ጌታህንም ከማመስገን ጋር ፀኃይ ከመዉጣቷ. በፊት ከመግባቷም በፊት አወድሰው።' ' (ቁርዓን 50-39) ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ ✍ሙሀመድ  & ሳኒ ይመር ┄┄┉┉✽‌»‌🌹✿🌹»‌✽‌┉┉┄┄ https://t.me/joinchat/Vu1GglMumUw6ORpA

የ ሕፃን ልጅ ሕይወት ለመታደግና የአንድን አባት እምባ ለማበስ በጋራ አንቁም!! 🌙"የወንድሙን ችግር የፈታ አላህ የቂያማ ቀን ችግሩን ይፈታለታል " ክብራት ና ክብራን ወንድም አህቶቻችን፦ ዛሬ የአንድ የህፃን ልጅ ሕይወት ለመታደግና የአንድን አባት እምባ ለማበስ በጋራ ቆመናል። ህፃን ዘከሪያ ሸምሰዲን በጠና ታሞ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚገኝ ሲሆን፣ አሁን ካለበት አስቸጋሪ ሁኔታ ለመውጣት በአስቸካይ ወደ ህንድ ሀገር ሄዶ መታከም እንዳለበት በሀኪሞች ተወስናል። ለዚህም ከፍተኛ የህክምና ወጪ ያስፈልጋል፤ይህ ደግሞ ከአባቱ ከሸምሰዲን አብዱ እና ከቤተሰቡ አቅም በላይ ሆኖባቸዋል። የአላህ መልእዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ )አንዲህ ብለዋል ፦ "ሙስሊም የሙስሊም ወንድም ነው....የወንድሙን ችግር የፈታ አላህ የቂያማ ቀን ከችግሮቹ አንዱን ይፈታለታል ።" (ቡካሪና ሙስሊም) ጌታችን አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይላል፦"መልካም ነገርንም ስሩ፤ ትድኑ ዘንድ።"(አል -ሐጅ :77) ሰደቃ በሽታን ይከላከላል :እድሜን ይጨምራል ፤የአላህንም ቁጣ ያበርዳል ።ዛሬ የምናበረክታት ጥቂት ሳንቲም ለህጻን ዘከሪያ ነገ ትልቅ ተስፋ ናት :: የ መረጃ አካውንት ቁጥር፦ 🏦 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) 📌 1000380970582 🏦 ህብረት ባንክ 📌3459111371313012 🏦 ዳሽን ባንክ 📌2904914060011 👤 ሸምሰዲን አብዱ ወንድሞችና አህቶች! አቅማችን በፈቀደው በገንዘብ፣ ካልሆነም መልዕክቱን ለሌሎች በማጋራት (share) በማድረግ እና በዱዓ አንረባረብ ። "አንድ ሰው ወንድሙን በመርዳት ላይ አስካለ ድረስ አላህ ያንኑ ሰው በመርዳት ላይ ይሆናል።" https://t.me/c/3937766766/2451 https://t.me/sohabaa

የሱሀቦች ዘመን - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @sohabaa