597
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ውድ የዶንቦስኮ ካቶሊክ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች እንኳን ለ1441ኛው ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። በዓሉን ስታከብሩ ራሳችሁን ከኮረና ቫይረስ እንድትጠብቁ አደራ እንላለን!!!
በ"ትምህርት በቤቴ“ መርሃ ግብር በአጭር የፅሁፍ መልእክት ለተሳተፉና ጥሩ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የ8455 የሽልማት መወዳደሪያ መልዕክት መላኪያ ላይ የአሸናፊ ተማሪዎች ሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ግንቦት 13/2012 ዓ/ም የተካሄደ ሲሆን በዚህ መርሃ ግብር ከ7ኛ --12ኛ ክፍል ላሉ 30 አሸናፊ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው ላፕ ቶፕ ኮምፒውተር እና ለቤተሰቦቻቸው 43 ኢንች ቴቪ የተሸለሙ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ደሞ የኛዋ የ10A ክፍል ተማሪ የሆነችው ሄኖን ማሩ አንዷ ነች! ውድ ተማሪያችን ሄኖን ከነ ቤተሰቦችሽ እንዃን ደስ አላችሁ እንላለን!!! ቤተሰብሽን፣ት/ቤትሽን፣ መምህራኖችሽን፣ ጓደኞችሽን አኩርተሻል! ኮርተንብሻል!! በርቺልን!!! ከዚህ የበለጠ ቦታ ላይ እንደምናይሽና ት/ቤትሽን እንደምታስጠሪ ባለ ሙሉ ተስፋ ነን።
ውድ ተማሪዎቻችን እንደምን ዋላችሁ
ለ3 ተከታታይ ቀናት የላክንላችሁን first self assessment test በሚገባ እንደሰራችሁ እናምናለን። በዛሬው ዕለትም በወጣው ኘሮግራም መሠረት የማመሳከሪያ መልስ የላክንላችሁ ሲሆን የሰራችሁትን ከተላከላችሁ መልስ ጋር በማመሳከር እና በማረም በጥንቃቄ እንድታስቀምጡ በድጋሚ አደራ እንላለን
መልካሙን ሁሉ ይሁንላችሁ!!
