ar
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 740
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
-530 أيام
أرشيف المشاركات
የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ወቅቱን ያማከለ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በICT ዲፓርትመንት የተጀመረውን የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝድ የማድረግ ስራ በስፋት እንዲከናወን ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄደ:: በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አንደኛው በትኩረት ከተያዙ ጉዳዮች ውስጥ የትምህርትና ስልጠና አሰጣጡን ዲጂታላይዝድ ማድረግ ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም እሁን ላይ የትኛው ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሲደረግ የአይ.ሲ.ቲ መሰረት ልማትና የግሪን ኢነርጂ ላይ ትኩረት እዲደረግ ይጠይቃልም ብለዋል:: ICT ላይ ቀድሞ የተጀመረና የዲጂታል ኮንቴንት (E-learning System) ላይ የተሰራ ስራ መኖሩን ያስትትወሱት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የተጀመሩትን ስራዎች ኮሌጁ የልህቀት ማዕከል በሆነባቸው ዘርፎች ላይ እያሰፋን እስከ ፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ድረስ በኮሌጁ ያሉትን እንቅስቂሴዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ለመቀየር እሰራለንም ብለዋል:: በኮሌጁ የICT ዲፖርትመንት አማካኝነት የትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን እየተሰራ ያለው ስራ ይበልጥ ለማስፋት የተዘጋጀውን ሰነድ በዲፓርትመንቱ ተጠሪ አሰልጣኝ መ/ር አቤል ፋንታሁን አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይም በICT አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም በኮሌጁ ሀላፊዎች ውይይት የተካሄደበት ሲሆን በተቀመጠው Action plan መሰረትም ወደ ትግበራ እንደሚገባ ከመድረኩ ማወቅ ተችሏል:: የE-Learning system/ የትምህርትና ስልጠናውን ከማዘመኑም በተጨማሪ ሰልጣኝ ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ቆይታቸው ስልጠናቸውን እንኪያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ የትምህርትና ስልጠና መረጃቸውን ሲሰተሙ የሚይዝ በመሆኑ የስልጠናቸውን ሁኔታና አፈጻጸም እንዲሁም የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት በማስጠበቅ ረገድ የራሱን እስተዋፅኦ እንደሚያደርግም ይታመናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ሚያዚያ 2/2017 ዓ.ም

የ2017 ዓ.ም "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት 3ኛ ዙር ስልጠና በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተጀመረ። በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት ከወረዳዎች ተመልምለው የተላኩ ወጣቶች በዛሬው እለት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል:: ለ12 ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና 12ኛ ክፍልና ከ12ኛ ክፍል በታች ትምህርታቸውን ላቋረጡ ወጣቶች የህይወት ክህሎትና የሥራ ላይ ልምምድ ስልጠና እንዲያገኙ የሚደረግም ይሆናል:: በስልጠናው ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 25 ዓመት ያሉ ወጣቶች ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን የፕሮግራሙ ዋነኛ ዓላማም ለወጣቶች የሥራ ዕድል በማመቻቸት የሥራ አጥ ቁጥር እንዲቀንስ ማስቻል እንደሆነም ተገልፇል:: በንድፈ ሐሳብና በተግባር ተደግፎ የሚሰጠው ስልጠና ስልጠናውን በወሰዱ የኮሌጁ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን በኮሌጁ ለ12 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ ኢንዱስትሪዎች ላይ ተመድበው የሥራ ላይ የተግባር ልምምድ የሚያደርጉም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 29/2017 ዓ.ም

ወጣቶች የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ርብርብ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ ዲፖርትመንቶች ለተወጣጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኤች.
+9
ወጣቶች የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ርብርብ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ ዲፖርትመንቶች ለተወጣጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ:: በመድረኩ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው ይህን ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በሀገራችን በአሳሳቢ ሁኔታ እየጨመረ የመጣው የቫይረሱን ስርጭት አስመልክቶ በተቋሙ ወጣት ሰልጣኝ ተማሪዎች ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራት በማስፈለጉ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን አክለውም ሰልጣኞች የተፈጠረላቸውን ግንዛቤ በየአካባቢያቸው መረጃውን በማካፈል የተሻለ ግንዛቤ ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር በሚደረገው ርብርብ ተሳታፊ ሊሆኑ ይገባልም ብለዋል:: በእለቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ለሰልጣኞች የሰጡት አቶ ፈቲ መሀመድ የተዘጋጀውን ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም "የስሜት ብልህነት" በሚል ርዕስ ራስን ስለማወቅ እንዲሁም ራስን ስለመምራትና ስለመቆጣጠር ለመድረኩ ተሳታፊዎች ስልጠና ተሰጥቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 27/2017 ዓ.ም

እንኳን ደስ አላችሁ!! #የድል_ዜና በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች በተሳተፉበት የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊ ሆኑ:: በክልል/በአስተዳደር ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂ ውድድር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ወክለው የተወዳደሩ ቴክኖሎጂዎች ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቀቁ:: ለቴክኖሎጂ ጥራት መሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበት በየሁለት አመቱ የሚዘጋጀው የቴክኖሎጂ ውድድር ዘንድሮም በደማቅ ሁኔታ የተካሄደ ሲሆን በክልል ደረጃ በሁለቱ ፖሊቴክኒኮች መካከል በተደረገው ውድድር ኮሌጃችንን ወክለው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች መሳተፍ የቻሉ ሲሆን ውድድሩንም በአሸናፊነት አጠናቀዋል:: በውድድሩ አጠቃላይ ውጤትም በኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህራን የተሰሩ ቴክኖሎጂዎች 1ኛ እና 2ኛ በመውጣት ውድድሩን በፍፁም የበላይነትና አሸናፊነት ማጠናቀቅም ችለዋል:: በውድድሩ 1ኛ በመሆን ያሸነፈውና በኮሌጃችን አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት በሀገራችን የሚስተዋለውን የነዳጅ ችግር መነሻ በማድረግ የተሰራው ከእፅዋትና ከተለያዩ ግብአቶች የተመረተ የነዳጅ ዘይት የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል:: በውድድሩ 2ኛ በመሆን ያጠናቀቀው ደግሞ በኮሌጃችን አሰልጣኝ መ/ር ሲሳይ ምንዳ፣ አሰልጣኝ መ/ር አበበ ተረፈ እና አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም የተሰራውና የአርሶ አደሩን ችግር በዘላቂነት የሚፈታ የእርሻ ማረሻ መሳሪያ ውድድሩን በ2ኛ ደረጃ አጠናቋል:: በተጨማሪም በውድድሩ ኮሌጁን ወክሎ የተወዳደረውና በአሰልጣኝ መምህር ግሩም ታምራት እንዲሁም አሰልጣኝ መምህር አበበ ተረፈ የተሰራው ዘመናዊ የእንቁላል ማስፈልፈያ ኢንኩቤተር በውድድሩ 5ኛ በመውጣት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብም ችሏል:: በዚህም መሰረት የውድድሩ አሸናፊ ቴክኖሎጂ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄድው የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ አስተዳደራችንን ድሬዳዋን በመወከል በሚደረገው የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ የሚሳተፍም ይሆናል:: በክልል ደረጃ ኮሌጃችንን በመወከል አሸናፊ የሆናችሁ የቴክኖሎጂ ባለቤቶች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እያልን በሀገር አቀፍ ደረጃ ድሬዳዋን ወክላችሁ የምታደርጉት ውድድርም በውጤት የታጀበ እንዲሆን ኮሌጁ መልካም ምኞቱን ይገልፃልም:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 26/2017 ዓ.ም

photo content
+9

#ዜና| የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በዛሬው እለት በቢሾፍቱ ተፈራረመ:: የመግባቢያ ስምምነ
+5
#ዜና| የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በዛሬው እለት በቢሾፍቱ ተፈራረመ:: የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ በዋነኝነት ሁለቱ ተቋማት በምህንድስናው ዘርፍ ለሚያደርጉት ቀጣይ ግንኙነት መሰረት የሚጥል መሆኑን በዩኒቨርሲቲው በኩል  የስምምነት ሰነዱን የፈረሙት የዩኒቨርሲቲው ኘሬዝዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ ገልፀዋል፡፡ ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ አያይዘውም በቴክኖሎጂ እና ምህንድስናው ዘርፍ በጋራ የፈጠራ ስራን የሚያዳብሩ ትብብሮችን  ስምምነቱ ከመፍጠሩ ባሻገር፤ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የሰሯቸው የምርምር ስራ ውጤቶች  ለፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ በአማራጭ ግብዓትነት እንዲቀርቡ የሚያስችል መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ይህም ለሁለቱም ተቋማት የገበያ ትስስርን እንደሚፈጥርም ኮማንዳንቱ ጠቁመዋል፡፡ የኢንጅነሪንግ ኮሌጅ አዛዥ ኮሎኔል ኢዶሳ ቱፋ በበኩላቸው በኮሌጁ በምርምሩ ዘርፍ በርካታ የምርምር ስራዎችን ያበረከቱ መምህራን የሚገኙበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የመግባቢያ ስምምነቱ በሁለቱ ተቋማት ያለውን ሀብት በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ሲሉም አዛዡ አክለዋል፡፡ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኩል የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን የፈረሙት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመስራት ላሳየው መልካም ፈቃድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ተግባር ተኮር ለሆኑ የምህንድስና ዘርፍ የትምህርት መስኮች ዩኒቨርሲቲው አስተዋፆው የጎላ እንደሆነም የኮሌጁ ዲን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ

በአስተዳደር ደረጃ የ2017 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር መካሄድ ጀመረ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምርና ስልጠና ኤጀንሲ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ በጋራ ባዘጋጁት የ2017 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር በአስተዳደሩ በሚገኙት የመንግስትና የግል ኮሌጆች በቴክኒክና ሙያ  ስልጠና ተዋናዮች (በሰልጣኝ፣ አሰልጣኝ እና አንቀሳቃሾች እንዲሁም ተቋማት) በተጨማሪም የአጠቃላይ ት/ቤት ተማሪዎችና መምህራን የሚያሳትፍ ይሆናል፤ የውድድሩ ዋና አላማም በአስተዳደሩ የሚገኙ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ችሎታ ያላቸውን ወጣቶችና የሙያ ባለቤቶች መካከል ከፍተኛ የውድድር ተነሳሽነትን መንፈስ በመፍጠር በመሰረታዊ  የስራ ፈጠራ፤ ተግባራዊ ምርምር እና ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት፣ የማሻሻል፣ የመፍጠር፣ የማለማመድ እና የማሸጋገር ስራዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የጥራት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር ይታሰባል፤ በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት በዘርፉ ፖሊሲ በተመላከተው መሰረት የክህሎትና የቴክኖሎጂ አቅምን ሊያሳዩና ሊያሳድጉ የሚችሉ ውድድሮችን ማድረጉ በዘርፉ ተሳታፊ የሆኑ አካላትን ከማነቃቃት በዘለለ ከኢንደስትሪው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ሲሆን አስተዳደሩም የተለየ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ የኢፌዲሪ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ ባስተላለፉት መልዕክት ቴክኖሎጂ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን አንስተው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ተወዳዳሪዎችን አበረታተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነባሩን የኮሌጁን መለያ ሎጎ በአዲስ ለመተካት በማስፈለጉ ምክንያት ዘርፉን በሚፈለገው ልክ የሚገልፅ ሎጎ በማሰራት በመጋቢት 19/2017 ዓ.ም ለኮሌጁ ቦርድ አቅርቦ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነባሩን የኮሌጁን መለያ ሎጎ በአዲስ ለመተካት በማስፈለጉ ምክንያት ዘርፉን በሚፈለገው ልክ የሚገልፅ ሎጎ በማሰራት በመጋቢት 19/2017 ዓ.ም ለኮሌጁ ቦርድ አቅርቦ የፀደቅ በመሆኑ ተቋማች መለያ ሎጎው በዚህ መልኩ የቀየረ መሆኑን እናሳውቃለን::

እንኳን አደረሳችሁ!! የኮሌጃችን ሰራተኞች እንዲሁም በመላው አለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የ
+1
እንኳን አደረሳችሁ!! የኮሌጃችን ሰራተኞች እንዲሁም በመላው አለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በዓል  እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ #መልካም_በዓል #ኢድ_ሙባረክ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ           

photo content
+5

photo content
+9

photo content
+9

ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ በክህሎት የዳበረ ዜጋ የማፍራት ተገባርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ:: የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሳይንስ ትምህርቶችና ፈጠራ ላይ ዝንባሌ ያላቸው የ STEM ክበብ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ጉብኝት በኮሌጁ አካሄዱ:: ኮሌጁ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ የፈጠረውን ግንዛቤ በተጠናከረ መልኩ ውጤታማ ለማድረግ በት/ቤቶች ላይ የቴክኒክና ሙያ ክበብ እንዲቋቋም የተደረገ ሲሆን በዚህም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎች የቴክኒክና ሙያ ክበቡን እንዲቀላቀሉ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል:: ለተማሪዎቹ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልእክታቸውም በቅድሚያ በቀጣይ የክህሎት ባለቤት ወደ ምትሆኑበት ኮሌጃችሁ እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ኮሌጁ ት/ቤቶች ላይ በስፋት ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውሰው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ የሚንቀሳቀሱ ተማሪዎችን በዘላቂነት በክህሎት ለማብቃት ታሳቢ በማድረግ ይህን የቴክኒክና ሙያ ክበብ በየት/ቤቶች እንዲቋቋም አድርገናልያሉ ሲሆን ተማሪዎች በቀጣይም በኮሌጁ የሚኖራችሁን ቆይታ በምትፈልጉት ሙያ መስክ ራሳችሁን ለማብቃት ልትጠቀሙበት ይገባልም ብለዋል:: ተማሪዎች ኮሌጁ ያለውን የማሰልጠን አቅም ተዘዋውረው ከጎበኙ በኃላም በቀጣይ ለክበብ አባላቱ የህይወት ክህሎትና STEMን መሰረት የደረጉ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም የSTEM አባላቱ ከመደበኛ ትምህታቸው ጎን ለጎን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጠርላቸዋልም ብለዋል:: በተጨማሪም ተማሪዎቹ በኮሌጁ ቆይታቸው የጥናት፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ አስተባባሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት ስለ STEM power ፅንሰ ሀሳብ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን በተጨማሪም በክፍሉ አስተባባሪነት በኮሌጁ የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተማሪዎቹ እስጎብኝተዋል:: የSTEM ክበብ አባላት በተቋሙ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በየዲፖርትመንቶቹ ስለሚገኙ የሙያ ስልጠናዎች በተመለከተም በአሰልጣኝ መምህራ ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: በቀጥይ የቴክኒክንይ ሙያ STEM ክበብ አባላት በኮሌጁ በሚዘጋጅላቸ የሙያ ስልጠናዎችን የሚወስዱ ሲሆን ይህም የ2ኛ ደረጃ ትምህታቸውን ከማጠናቀቃቸው አስቀድሞ ቢያንስ የአንድ ሙያ ባለቤት እንዲሆኑም የሚያስችላቸው እንደሚሆን ተግልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 19/2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+9