Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 740
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
-530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from N/a
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ ልዑክ በዛሬው እለት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ የስራ ጉብኝት አካሄደ፡፡
ግንቦት 28/2017 ዓ.ም
በሚኒስትር ዴኤታው የተመራው ልዑካን ቡድን በኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ ዲኖች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን ቡድኑ በነበረው ቆይታም በበጀት አመቱ በኮሌጁ የተሰሩ ዋና ዋና ትግባራትን እንዲሁም በተቋሙ እየተከናወኑ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የለውጥ ስራዎችንም ተመልክተዋል::
በበጀት አመቱ በኮሌጁ የተከናወኑ አጠቃላይ ተግባራትን ዝርዝር ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለልዑካን ቡድኑ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱም ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ፣በቴክኖሎጂ ፈጠራዎች፣በስራ ዕድል ፈጠራዎች፣ በእንተርፕራይዞች ድጋፍ ጨምሮ ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አኳያ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ተብራርተዋል::
በመስክ ምልከታው ልኡክ ቡድኑን የመሩት ሚንስትር ዴኤታው ከሱፐርቪዥኑ በኃላ በሰጡት አስተያየት በተቋሙ በነበራቸው ምልከታ የተሻለ የሚባል አፈፃፀምና የስራ እንቅስቃሴ መመልከታቸውን ገልፀው በቀጣይም ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አንፃር በኮሌጁ የተጀመሩ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ በትኩረት መስራት ይጠበቃልም ብለዋል::
በእለቱ በኮሌጁ የተካሄደው ድጋፋዊ ሱፕርቪዥን ምልከታም በሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለተቋሙ በመስጠት ተጠናቋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ወጣቶች በሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ቅጥርን ሳይጠብቁ ስራ ፈጣሪ ዜጋ መሆን እንዲችሉ ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ተባለ::
ግንቦት 25.2017 ዓ.ም
ADRA ኢትዮጵያ ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በኮሌጁ በSolar PV Installation Maintenance ሰልጥነው ለተደራጁ ማህበራት ወደ ስራ እንዲገቡ የሚያስችላቸውን የማቴሪያል እና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አደረገ::
በSolar Maintenance እቃዎችና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ መርሀ-ግብሩ ላይ ለወጣቶች መልዕክት ያስተላለፉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በንግግራቸውም በዛሬው እለት ከፍተኛ ድጋፍ ከፕሮጀክቱ ያገኙ ወጣቶች የተፈጠራላቸውን ምቹ እጋጣሚ በአግባቡ ተጠቅመው በቀጣይ በዚህ መንገድ ለሚመጡ ወጣቶች አርአያ የመሆን ከፍተኛ ሀላፊነት አብሮ እንደተጣለባቸው የገለፁ ሲሆን አክለውም በተገኘው የማቴርያልና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ በአስተዳደሩ የከተማ ወረዳና የገጠር ክላስተሮች በዘርፉ ያልተነካውን የስራ እድል በአግባቡ ተጠቅመው ራሳቸውን ብሎም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ምክራቸውን ለግሰዋል::
በፕሮጀክቱ እንደ ግብ የተቀመጠው 120 ሰልጣኞችን በSolar PV Installation Maintenance አሰልጥኖ ከስራ ጋር ማስተሳሰር መሆኑን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲጨርሱ እንደትቋም በራሳቸው ስራ ፈጥረውና ተደርጅተው እዲሰሩ አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ኮሌጁከፕሮጀክቱ ጋር በመተባበር የማቴሪያል ድጋፉ በADRA ፕሮጀክት አማካኝነት እንደተደረገ ገልፀው እንደተቋም ለወጣቶቹ ድጋፍ በማድረግ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመነጋገር ኮሌጁ ለንግድ አገልግሎት የሰራቸውን ቤቶች ወጣቶቹ ተደራጅተው እንዲሰሩበት እድርገናልም ብለዋል::
በእለቱ በሁለት ማህበራት ለተደራጁ 21 ወጣቶች ከ450ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ የSolar Maintenance እቃዎች ድጋፍ የተደረገላቸው ሲሆን ወጣቶቹም....
በInstallation
በMaintenance
የSolar እቃዎችን በማቅረብ እንዲሁም ተዛማችነት ያላቸውን ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚሰሩ ማወቅ ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
በEASE ፕሮጀክት(ኢትዮጵያ) ዋና ሀላፊ ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገ/እግዚአብሔር የተመራ ልዑክ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ጉብኝት አካሄደ፡፡
ግንቦት 22.2017 ዓ.ም
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ በነበረው የስራ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደትና እስካሁን የተሰሩ ተግባራትን ጨምሮ በኮሌጁ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የለውጥ ስራዎች በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም በኮሌጁ ይEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ገልፃ ተደርጎላቸዋል::
የፕሮጀክቱ ዋና ሀላፊ የተመሪው ልዑክም በኮሌጁ ባደረጉት ምልከታና የተደረገላቸውን ገለፃ መነሻ በማድረግ ውይይቶች የተካሄደዱ ሲሆን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ ያሳየው አፈፃፀም ለሌሎችም ፕሮጀክቱ ለሚተገበርባቸው ተቋማት ምሳሌ መሆን የሚያስችል መሆኑንም ዋና ሀላፊው ሀሳባቸውን ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና ዎርክ ሾፖችን ጨምሮ የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ ዋና ሀላፊ ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገ/እግዚአብሔር አማካኝነት ለኮሌጁ በቀጣይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ የስራ አቅጣጫን በመስጠት ጉብኝቱን አጠናቀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ::
ግንቦት 22.2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ከፌደራል በመጡ የፕሮጀክቱ ተጠሪዎች አማካኝነት የፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ ከኮሌጁ ጋር አብረው ለሚሰሩ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክትም ይህ ስልጠና በዋነኛነት በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ ጉልህ ሚና ላላቸው ባለድርሻ አካላት እንደተዘጋጀ ጠቅሰው ኮሌጁ ብቻውን የሚፈልገውን ውጤት ማሳካት እንደማችልና የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ በመሆኑ በተለይም ድሬዳዋ ላይ እንዲሳኩ የምንፈልጋቸውን ተግባራት እውን ለማድረግ እንዲያስችለን ሁላችንም የየድርሻችንን መወጣት ይጠበቅብናልም ብለዋል::
በዕለቱ ስልጠናውን ለተሳታፊዎች የሰጡት የEASE ፕሮጀክት(ኢትዮጵያ) የማህበራዊ ልማት ባለሙያ አቶ መለስ ይመር ሲሆኑ የፕሮጀክቱን ዋና ዋና አላማዎችን በዝርዝር ለመድረኩ ተሳታፊዎች የሚገልፅ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ አፈፃፅም ወቅት የኮሌጁ እንዲሁም የባለድርሻ አካላትን ሚና ምን ምን እንደሆኑ ለይተው በማስቀምጥ ግንዛቤ ሰጥተዋል::
በመቀጠልም በፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያ በሆኑት አቶ ሰለሞን አሊ አማካኝነት በEnvironmental Screening ላይ ለተሳታፊዎች ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ መስጠትም ተችሏል::
በቀረበው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድን መነሻ በማድረግም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የመደረኩ ተሳታፊዎች በፕሮጀክቱ አላማና አተገባበር ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲያገኙ ያስቻለ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል::
#ጥብቅ ማሳሰቢያ
ለ፡-ሁሉም የአስተዳደሩ ተቋማት የሰው ሀብት ኃላፊዎች
ቀደም ሲል ግንቦት 20 በካሌንደር ዝግ ሆኖ ይውል የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን እለቱን ካሌንደር የማይዘጋው እና መደበኛ የስራ ቀን መሆኑን አውቃችሁ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ እንዲገኙ እንድታደርጉ ያሳስባል።
የድሬዳዋ አስተዳደር
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ
****
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን ሐሙስ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ የሚካሄድ ይሆናል።
በዚህም ስራ ፈላጊ ምሩቃን የተለያዩ ድርጅቶች በቅጥር ሥራ የምታገኙበትን ሁኔታ ሊያመቻቹ እናንተን ስለሚጠብቁ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በመያዝና በአካል በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የድሬዳዋ አስተዳደር
ሥራና ክህሎት ቢሮ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የሥራ እድል ፈጠራን ዲጅታላይዝ በማድረግ አሰራራችንን ቀልጣፋ ማድረግ እና ውጤታማ ነትን ማረጋገጥ ያስችለናል።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
ካይዘንን በስራ ቦታና አካባቢ በቀጣይነት ተግባራዊ ማድረግ ምቹና ተስማሚ የስራ ቦታ መፍጠር ከማስቻሉ በተጨማሪ ዉጤታማ የጥራት አስተዳደር ስርዓትን በማሳደግ የስልጠና ጥራትን ማረጋገጥ ያስችላል ተባለ።
ግንቦት 05/09/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካይዘን ትግበራን በኮሌጁ በዘላቂነት መተግበር እንዲያስችል በተዘጋጀው የማስተግበሪያና የአፈፃፀም መከታተያ መመሪያ ላይ ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የካይዘን ማስተግበሪያ መመሪያው በኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት የካይዘን ክፍል ተጠሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በተሰጠው ግንዛቤ መሰረትም በቀጣይ ለዚሁ ትግበራ በየክፍሉ በተመደቡ ባለሙያዎ አማካኝነት ካይዘንን በተቋሙ በተደራጀ መልኩ የመተግበርና የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራም በመድረክ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
+9
ካይዘንን በስራ ቦታና አካባቢ ተግባራዊ ማድረግ ብክነቶችን ከማስቀረት በተጨምሪም ቀልጣፋ የስራ እንቅስቃሴ እንዲኖር ያስችላል ተባለ::
ግንቦት 05/09/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካይዘን ትግበራን በኮሌጁ በዘላቂነት መተግበር እንዲያስችል በተዘጋጀው የማስተግበሪያና የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የካይዘን ማስተግበሪያ መመሪያው በኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት የካይዘን ክፍል ተጠሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በተሰጠው ግንዛቤ መሰረትም በቀጣይ ለዚሁ ትግበራ በየክፍሉ በተመደቡ ባለሙያዎ አማካኝነት ካይዘንን በተቋሙ በተደራጀ መልኩ የመተግበርና የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ የማኑፋክቸሪንግ አሰልጣኝ መምህራን በደረጃ አራት በማሽኒግ እና ሜካኒክስ ሙያዎች ሀያ አሰልጣኝ መምህራን በመመዘን ላይ መሆናቸውና በቀጣይ ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገለጸ።
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ
“ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ሐሳብ ሲካሄድ የነበረው 4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ተካሂዷል፡፡
በውድድሩ 1ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች 500 ሺህ ብር፣ 2ኛ ለወጡ 400 ሺህ ብር እንዲሁም 3ኛ ለወጡ 300 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡
ከድሬዳዋ አስተዳደርም በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ እና በተግባራዊ ጥናትና ምርምር አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኝ ተማሪዎች እና ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በውድድሩም ሰልጣኝ ተማሪ ዮሐንስ ሞላ በሀርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ መስክ ተወዳድሮ አንደኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳልያ እና የ500 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል ለዚህም በተገኘው ውጤት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 2/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
