Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 740
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+17 أيام
-630 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታ እና አካታችነትን ለማሳደግ በተዘጋጀው ጥናት ላይ ከፑል አመራር አባላትና ሴት አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት በቅድሚያ በአለም አቅፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ ለሚከበረው የሴቶች ቀን(March 8) እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆኑ በዚህ ቀን ስርዓተ-ፆታን በኮሌጃችን ለማዳበር በተዘጋጀ ጥናት ላይ ውይይት ማድረጋችን ቀኑን ልዩ ያደርገዋልም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በተቋማችን በስርዓተ-ፆታ እና በአካታችነት በርካታ ፍላጎቶች መኖራቸውን አስታውሰው ከዚህ ቀደም የተወሰኑ ስራዎች ቢሰሩም በሚነሱት ፍላጎቶች ልክ በአግባቡ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ እንዳልነበሩ ጠቅሰው በዚህም በስርዓተ ፆታ እና አካታችነት ላይ መስራት በሚገባን መጠን ለመንቀሳቀስ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት አድርጎ መነሻ የሚሆን መመሪያ ማዘጋጀት አስፈልጏልም ብለዋል::
በተጨማሪም በሁለቱ ጉዳዮች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለማድረግ በተመረጡ ቡድኖች አማካኝነት ጥናቱ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው በዛሬው እለትም የጥናት ቡድኑ የደረሰበት በመድረኩ አቅርቦ በቀረበው ጥናት ላይ አስተያየት እንዲሰጥበትና መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች ማካተት እንዲቻል የተዘጋጀ መድረክም ነው ብለዋል::
የስርዓተ ፆታ እና እካታችነትን ለማሳደግ በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ውስጥ ለሚኖረው ትግበራ መነሻ ሚሆነውን መመሪያ ለማዘጋጀት የተደረገውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት አዘጋጆቹ የደረሱበትን ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን በቅድሚያ በአካታችነት ላይ የተደረገውን የፍላጎት ዳሰሳ በአሰልጣኝ መምህር ዮናስ ሙሉጌታ ለተሳታፊዎች ቀርቦ በጥናቱ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ እንደ ተቋም የተለዩ ክፍተቶችን በዝርዝር አመላክቷል::
ቀጥሎም በስርዓተ-ፆታ ላይ የተዘጋጀውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በወ/ሮ ራሄል እሸቱ እና ኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው ጥናትም በስራ እካባቢ ለሴቶች የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች የማሟላት ክፍተት፣ ስርዓተ ፆታ ላይ በቂ ግንዛቤ ለኮሌጁ ሰራተኞች አለመፍጠር፣ ሴቶችን የማበረታታትና ወደ አመራርነት እንዲመጡ ተገቢውን ድጋፍ ያለማድረግ እንዲሁም የማማከር አገልግሎት ሚያገኙበት አግባብ ያለመኖሩ የሚሉት በጥናቱ ከተገለፁት ውስጥ ተጠቃሽ ነጥቦችም ነበሩ::
በመጨረሻም በቀረቡት ጥናቶች መነሻነት ከተሳታፊዎ በርከት ያሉ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተደረገበት ሲሆን ጥናቱንም ለማዳበር ተጨማሪ ግብአቶች የተገኙበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 29/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
የውይይት መድረኩ የመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደግለፁት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የትምህርትና ስልጠናው የመጀመሪያ ተርም ተጠናቆ ሁለተኛውን ተርም ምንጀምርበት ወቅት ላይ እንደመሆናችን የነበሩ ክፍተቶችን በሚገባ ለይቶ መፍትሄ ለማበጀትና በሁለተኛው ተርም ላይ በድጋሚ እንዳይስተዋሉ ለማድረግ ይህ የውይይት መድረክ አስፈልጎናልም ብለዋል::
ም/ዲኑ አክለውም ቀደም ብለው ከአካዳሚክ አባላት ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው ከዛ በተገኘው ግብዓት መነሻነት እንዲሁም ከአሰልጣኝ መምህሩ የሚነሱ ሀሳቦችንም ጨምሮ በመወያየትና መፍትሄዎችንም በማስቀመጥ ለሁለተኛው ተርም በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባም ገልፀዋል::
በመድረኩ ተሳታፊ ከነበሩት አሰልጣኝ መምህራንም የትምህርትና ስልጠና ሂደቱን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን ከተነሱት ሀሳቦች ውስጥም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል ውስንነት፣ ከትብብር ስልጠና ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮችን እንዲሁም በምሽት ስልጠና ላይ ያልተመጣጠነ የመምህራን ክፍያ ችግርን ጨምሮ ትምህርትና ስልጠናውን ውጤታማ እንዳይሆን መንስኤ ናቸው ያሏቸውን በርካታ ክፍተቶችን በመጥቀስና አያይዘውም የመፍትሄ ሀሳብ ይሆናሉ ያሏቸውንም በመድረኩ አቅርበዋል::
በመጨረሻም አጠቃላይ ከመድረኩ በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት በማድረግ እንዲሁም ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸው መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 28/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
የውይይት መድረኩ የመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደግለፁት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የትምህርትና ስልጠናው የመጀመሪያ ተርም ተጠናቆ ሁለተኛውን ተርም ምንጀምርበት ወቅት ላይ እንደመሆናችን የነበሩ ክፍተቶችን በሚገባ ለይቶ መፍትሄ ለማበጀትና በሁለተኛው ተርም ላይ በድጋሚ እንዳይስተዋሉ ለማድረግ ይህ የውይይት መድረክ አስፈልጎናልም ብለዋል::
ም/ዲኑ አክለውም ቀደም ብለው ከአካዳሚክ አባላት ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው ከዛ በተገኘው ግብዓት መነሻነት እንዲሁም ከአሰልጣኝ መምህሩ የሚነሱ ሀሳቦችንም ጨምሮ በመወያየትና መፍትሄዎችንም በማስቀመጥ ለሁለተኛው ተርም በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባም ገልፀዋል::
በመድረኩ ተሳታፊ ከነበሩት አሰልጣኝ መምህራንም የትምህርትና ስልጠና ሂደቱን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን ከተነሱት ሀሳቦች ውስጥም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል ውስንነት፣ ከትብብር ስልጠና ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮችን እንዲሁም በምሽት ስልጠና ላይ ያልተመጣጠነ የመምህራን ክፍያ ችግርን ጨምሮ ትምህርትና ስልጠናውን ውጤታማ እንዳይሆን መንስኤ ናቸው ያሏቸውን በርካታ ክፍተቶችን በመጥቀስና አያይዘውም የመፍትሄ ሀሳብ ይሆናሉ ያሏቸውንም በመድረኩ አቅርበዋል::
በመጨረሻም አጠቃላይ ከመድረኩ በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት በማድረግ እንዲሁም ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸው መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 28/2017 ዓ.ም
የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ከሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ጋር በኢንዱስትሪ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ::
የምክክር መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ባስተላለፉት መልዕክትም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ወደ ኢንዱስትሪ የሚገቡትን ብቻ ሳይሆን ኢንዱስትሪው ላይ እየሰሩ የሚገኙትን ባለሙያዎችን ጭምር የሚፈለገው ደረጃ ላይ እንዲደርሱ አሰልጥኖ ማብቃት እንዱ ተግባሩ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም እንዲረዳ በየትኛው ዘርፍ ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ ይቻላል የሚሉትን ጉዳዮች በቀጥታ ከእናንተ ከጉዳዩ ባለቤቶቹ ጋር ለመወያይትና መረጃዎችን ለመሰብሰብ ይህ የምክክር መድረክ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በሚኖረን የምክክር መድረክ ላይ ብዙ ግብዓቶች ከተሳታፊዎች እንደሚጠብቁ ገልፀው በኢንዱስትሪው ውስጥ ምርታማነትን ከማስፋፋት አንፃር እንዲሁም በትክክል የኢንዱስትሪውን እድገት እየጎተቱ ያሉ ጉዳዮችን ከቴክኒክና ሙያ ዘርፉ አኳያ ሊፈቱ የሚችሉትን በዝርዝር መረጃ እዲሰጡም ጠይቀዋል::
የዳሰሳ ጥናት ሰነዱን ለተሳታፊዎች ሰፋ ባለ ማብራሪያ ያቀረቡት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በዚህ ጉዳይ እስካሁን በነበረው የተናጠል እንቅስቃሴ የሚጠበቅውን ውጤት ማስመዝገብ እንዳልተቻለ አስታውሰው ከጅምሩ በቅንጅት ሲሰራ ብዙ አዳዲስ ነገሮችን መፍጠር እንደሚቻልና ለሚስተዋሉ ችግሮችም የመፍትሄ አካል መሆን ስለሚቻል ሁላችንም በንቃት ልንሳተፍ ይገባልም ብለዋል::
ከመድረኩ በተደረገው ገለፃ መሰረትም አምራችና አገልግሎት ሰጪ እንዱስትሪዎች እንደየዘርፋቸው በቡድን ተከፋፍለው የምክክር መድረኩ የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በየድርጅቶቻቸው የተለዩ ፍላጎቶችን እንዲሁም የመፍትሄ ሃሳቡ ይሆናሉ ያሏቸውን ለመድረኩ አወያዮች በማቅረብ ለፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ ግብዓት ማግኘትም ተችሏል::
በተጨማሪም በመድረኩ የዳሰሳ ጥናት ፎርም አጠቃቅም በተመለከት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አስተባባሪ አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም ለዚህ ተግባር በተመደቡ ባለሙያዎች አማካኝነት በየኢንዱስትሪዎቹ በመሄድ ለዳሰሳ ጥናቱ የሚያስፈልገውን መረጃ የሚያደረራጁ መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለውን ምቹ አጋጣሚ በመረዳትና ዘርፉንም በመቀላቀል በወርቃማ ጊዜያቸው አምራችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ዜጋ የሚያደርጏቸው አማራጮች ላይ በንቃት ሊስተፉ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሰራውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በሳብያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዷል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት በሰፊው ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ለተማሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የሚያስመዘግቡትን ውጤት ተከትሎ ዩኒቨርሲቲ በመግባትና ባለመግባት አቅማቸው እንደማይለካ በመናገር የቴክኒክና ሙያም ሌላኛው የተሻለው አማራጭ መሆኑንም ከወዲሁ መረዳት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲ ከሚገቡትም ይልቅ በቴክኒክና ሙያ ውስጥ የሚያልፉ ዜጎች በየትኛው መመዘኛ የተሻለ እድል ያላቸው መሆኑንም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
አክለውም በተሻሻለው ፖሊሲ መሰረት የትኛውም በቴክኒክና ሙያ የሚያልፍ ሰልጣኝ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊያሳካ የሚችለውን የመጨረሻውን የPHD (Level 8) ድረስ እራሱን እያሻሻለ መድረስ የሚያስችለው አሰራርም መዘርጋቱን የገለፁ ሲሆን ተማሪዎችም የወደፊት እጣፈንታቸውን የሚወስኑበት ምርጫቸውን በጥንቃቄና ብስለት በተሞላበት መንገድ እንዲወስኑ ምክር ለግሰዋል::
የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በኮሌጃችን ውስጥ እንዲያዳብሩ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን የገለፁት በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በት/ቤቱ ውስጥ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶችን በማቀናጀት የቴክኒክና ሙያ ክበብ እንደሚቋቋም ጠቅሰው ኮሌጁም ከዚህ ጋር ተያይዞ አስፈላጊው ድጋፍ ያደርጋልም ብለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር አዘጋጅነት ለሚካሄደው 4ኛው ዙር የ2017 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በአስተዳደር ደረጃ ለማካሄድ ለተወዳዳሪዎች በውድድር መስፈርቱ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በቀጣይም በተለያዩ ሙያዎች ላይ በአስተዳደር ደረጃ ውድድር የሚያካሄድ ሲሆን ውድድሩን በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች አስተዳደሩን በመወከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር አልፎም እስከ አለም አቀፍ ድረስ የሚዘልቅ እድል ተመቻችቶላቸዋል፤ በዋናነት የስልጠና ጥራትን ከማሳደግ አንፃር ጉልህ አስተዋፅኦ የሚኖረውም ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
