ar
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 755
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
+1130 أيام
أرشيف المشاركات
………………………………………………… የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂና ክህሎት ውድድር ላይ ኮሌጃችንን ብሎም አስተዳደሩን ወክለው በመሳተፍና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ተቋሙን እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩን ላኮሩት አሰልጣኝ መምህራኖች እና ሰልጣኝ ተማሪዎች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ኘሮግራም በማዘጋጀት ጀግኖቹን አመስግኗል። ተሸላሚዎችም ለተደረገላቸው እውቅናና ሽልማት በማመስገን እንዲ አይነት ማበረታቻዎች በቀጣይ በበለጠ ጠንክረው እንዲሰሩና ከዚህም የላቀ ውጤት ለማምጣት የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው ገልፀዋል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ ይላል። #መልካም_የፋሲካ_በዓል

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ …………………… ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰናዳው የቴክኖሎጂ እና ቴክኒካል ክህሎት ውድድር ላይ ድሬዳዋን እንዲሁም ተቋማችንን በመወከል የተወዳደረው አሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ በተወዳደረበት ዘርፍ(CNC) ከመላው ኢትዮጵያ ከመጡ ተወዳዳሪዎች 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ እና የ30ሺህ ብር ተሸላሚ መሆን ችሏል። በዚህም አሰልጣኝ መምህራችን ያስመዘገበው ላቅ ያለ ውጤት የተቋማችንን እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደርን ስም በክብር ያስጠራ በመሆኑ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተገኘው ድል ደስታውን እየገፀ ለአሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ ላቅ ያለ ክብርና ምስጋና ያቀርባል።👏👏👏

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ …………………… ▶በ 2013 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የቴክኖሎጂ እና ክህሎት ውድድር ላይ ኮሌጃችንን እንዲሁም ድሬዳዋን ወክለው የተሳተፉ የተቋማችን አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ በድል ተመልሰዋል። ▶በዚህ በተገኘው አኩሪ ውጤትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንኳን ደስስስ አላችሁ እንኳን ደስስ አለን ማለት ይወዳል። ▶በውድድሩ ውጤት ያስመዘገቡ የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች:- 💥አሰልጣኝ መምህር #ስንታየሁ_ቀጭኔ በተወዳደሩበት ዘርፍ 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ። 💥አሰልጣኝ መምህር #ደረጀ_ሽፈራው በተወዳደሩበት ዘርፍ 3ኛ በመውጣት የነሀስ ሜዳልያ ተሸላሚ። 💥አሰልጣኝ መምህር #ብሩክ_አንለይ በተወዳደሩበት ዘርፍ 3ኛ በመውጣት የነሀስ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆነዋል። በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።👏👏👏

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

በፌደራል ቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ካምፓስ የ2013 ዓ.ም የሳተላይት ዲግሪ ፕሮግራም ፅጩ ተመራቂ ተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት በፎቶ📷📷… በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓🎓🎓

ኮሌጃችን የእምነቱ ተከታይ ለሆኑ ሰራተኞቻችንና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 2013ዓ.ም የገና በዓል ሰላም አደረሳቹ ይላል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲስ መልክ የተሻሻለውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፓሊሲና ፕሮግራም ለተቋሙ ሰራተኞች የማቅረብያ መድረክ በማዘጋጀት የተቋሙ ሰራተኞች በፖሊሲና ፕሮግራሙ ላይ አስተያየት እንዲሰጡበት አድርጓል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአስተዳደሩ የጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በገጠር ቀበሌዎች የሚታየው የመፀዳጃ ቤት ችግርን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከገጠር ቀበሌዎች ለተወጣጡ 20 ሰልጣኞች በሳኒተሪ ማርኬቲንግ አርማታ ስላብ(የመፀዳጃ ቤት መቀመጫ አሰራር) በአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም በማሰልጠን ሰልጣኞች የአካባቢያቸውን የመፀዳጃ ቤት ችግር እንዲቀርፉ እውቅና ሰቷል።