Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 739
المشتركون
-124 ساعات
+17 أيام
-730 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቤተል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለተማሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ትኩረት አድርጎ እየሰራባቸው ከሚገኙ ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመግባታቸው አስቀድሞ ከት/ቤቶች ጋር በመተባበር ለተማሪዎቹ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ የማድረግ ስራ ሲሆን በዛሬው እለትም በቤተል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማካሄድ ተችሏል::
በመድረኩ ተገኝተው የግንዛቤ ማስጭበጫውን ያካሄዱት የኮሌጃችን ዲኖች ሲሆኑ በመድረኩም ለተማሪዎቹ በቴክኒክና ሞያ ዘርፍ ያሉ ምቹ አጋጣሚዎችን በዝርዝር በማስቀመጥ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ሲጨርሱ በዘርፉ ሊያገኙ የሚችሉትን ወርቃማ እድል ከወዲሁ ተረድተውት ትክክለኛውን ውሳኔ እንዲወስኑ የሚረዳቸውን መረጃና ግንዛቤ ለተማሪዎች ማስጨበጥ ተችሏል::
ይህን መሰል መድረኮች ቀጣይነት የሚኖራቸው ሲሆን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎቹን ግንዛቤ ከማስጨበት ባሻገር ወደ ኮሌጃችን በመጋበዝ የተለያዩ ስልጠናዎችን እንዲሰለጥኑና ለቀጣይ ምዕራፋቸው መሰረት እዲጥሉ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ግንቦት 19/2016 ዓ.ም
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የአስተዳደሩን ፀጋ መሰረት ያደረገ ክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል፥ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ
ግንቦት 6/2016 ዓ/ም
የክህሎት መር ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር ተያይዞ ገበያ ተኮር አጫጫር ስልጠናዎች አፈጻጸም ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚመክር መድረክ ተካሄደ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት በተዘጋጀው መድረክ ላይ የአስተዳደሩ የከተማ ወረዳዎችና የገጠር ክላስተር አመራሮች፤ የአንድ ማዕከላት አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ከስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር በሁሉም ወረዳዎች ፀጋን መሰረት ያደረገና ክህሎት መር በሆነ መንገድ ማህበራትን በማደራጀት በተለይ ኮሌጆች በሚሰጧቸው ስልጠናዎች ተጠቃሚ ለመሆን በቅንጅት ሁሉም አካላት በመናበብ የሚሰሩበት ሁኔታ መፈጠር አለበት ብለዋል።
በመጨረሻም ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በአስተዳደሩ እስከ አሁን ስልጠና እየተሰጠ ካለባቸው የተወሰኑ ዘርፎች በተጨማሪ በሌሎች ዘርፎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በየአካባቢው ወደ ስራ ያልገቡ ወጣቶችን በመለየት ወደ ስራ እንዲገቡ በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባው በመግለጽ ቀጣይ ሥራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ማጠቀለያ ሰጥተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ ባለሙያዎች በ E-LMIS ሲስተም አተገባበር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ምክትል ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ እንዲሁም የዲፖርትመንት ተጠሪዎችና በሂደቱ ስር የሚገኙ ባለሙያዎች በተገኙበት ስለ ሲስተሙ አሠራር፣ ፋይዳ እና ዉጤት ከዉጭ ሃገር ሥራ ስምሪትና የውስጥ ሥራ እድሎችን በማመቻቸት ላይ እንዲሁም የተለያዩ ብልሹ አሠራሮችን ለማስቀረት የስርዓቱ ሚና የጎላ መሆኑንና ለዜጎች በE-LMIS ሲስተም ምን ጥቅሞች እና እንዴት በቀረበላቸው ሲስተም መጠቀም እንደሚችሉ ጥልቅ የሆነ ግንዛቤ ተሰጥቷል።
እንዲሁም የE-LMIS ሲስተም ተጠቃሚ ለመሆን እንዴት በራስ መመዝገብ እንደሚቻል እና በቀረቡት ብዙ አማራጮች ተጠቃሚ መሆን ኢንደሚችሉም በቂ የሆኔ ግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በአል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል::
#መልካም_የፋሲካ_በዓል
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጎ አድራጎት ክበብ መጪው የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ::
የበጎ አድራጎት ክበቡ ያዘጋጀውን የአስቤዛ እና የገንዘብ ድጋፍ የኮሌጁ ዲኖች ተገኝተው ለአቅመ ደካሞች ያስረከቡ ሲሆን አያይዘውም ለመጪው የትንሳዔ በዓል መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል::
በዚህ ክበቡ ባደረገው የአስቤዛ እና የገንዘብ ድጋፍ ተጠቃሚ የሆኑት አካላት በኮሌጁ ማህበረሰብ ጥቆማ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ለተለዩ 20 እቅመ ደካሞች የአስቤዛና የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት የተዘጋጀና በተማሪዎች ቅበላ መጠነ መቀነስ ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀረበ::
ስራ ሂደቱ በአዲስ መልክ በ2016 ዓ.ም በሰው ሀይል ተደራጅቶ ስራ ከጀመረባቸው ዘርፎች ውስጥ የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋነኞቹ ሲሆን በሂደቱ ጥናትና ምርምር ላይ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራን ከድሬድዋ ዪኒቨርስቲ መምህራን ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ጥናታዊ ጽሁፍ የተማሪዎች ቅበላ መጠነ መቀነስ ጋር ተያይዞ መንስኤ ይሆናሉ ተብለው የተለዩ ጉዳዮችን ላለፉት ወራት ጥናት በማድረግ በዛሬው እለት ለኮሌጁ ፑል አመራር እና ባለ ድርሻ አካላት በጥናቱ ያገኙትን ውጤት አቅርበዋል::
በመድረኩ የቀረበውን ጥናታዊ ጽሁፍ መነሻ በማድረግም ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ገንቢ አስተያየቶች የተሰጡበት ሲሆን የጥናቱ ባለቤቶችም በቀጣይ እነዚህ ከመድረኩ የተሰጡ ግብአቶችን በማካተት ከኮሌጅ አልፎ እንደ ሀገር የተሻለ ችግር ፈቺ ጥናታዊ ጽሁፍ ለማዘጋጀት እንደሚያግዛቸው በመጠቆም በቀጣይ የታዩ ውስንነቶችን በመሙላት ጥናታዊ ፅሁፉ ተጠቃሎ እንደሚቀርብ ለመድረኩ ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ላይ ባተኮረ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ላይ ተሳትፈው የውድድሩ አሸናፊ ሆነዋል::
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀውና ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በቀረቡበት ውድድር ላይ የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር ነዋይ ይልማ እና አሰልጣኝ መምህር አቤል ዘገየ የተሳተፉ ሲሆን ያቀረቡት ጥናትና ምርምርም የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ የውድድሩን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ በአሸናፊነት ማጠናቀቅ ችለዋል::
በዚህም ውድድር ላይ በዘርፉ በተለይም በኮሌጆች የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ ስርዓት፣ የሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላና መጠነ ማቋረጥ፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጋር የተያያዙ በዋናነት መሠረታዊ የዘርፉን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ ጥናቶች ቀርበው ውድድር የተካሄደባቸው ሲሆን በውድድሩ አንደኛ ሆኖ ያጠናቀቀውና በኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር ነዋይ ይልማ የተዘጋጀው ጥናትና ምርምር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ድሬዳዋን ወክሎ የሚሳተፍም ይሆናል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተመዘገበው ውጤት እንደ ተቋም የተገኘ ውጤት በመሆኑ ውድድሩን በበላይነት ላጠናቀቁ አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም ለኮሌጁ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት ይወዳል::
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
አድራ ኢትዮጵያ (ድሬዳዋ) በ"Solar Pv instalation and maintenance እያሰለጠናቸው የሚገኙ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ በመሆኑ በቀጣይ ምእራፍ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እያሰለጠናቸው የሚገኙ 48 ሰልጣኞች ዋና ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውና ወደ ምዘና ለመግባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ሰልጣኞች ወደ ስራ አለም ሲገቡ የሚያግዛቸውን የኢንተርፕረነርሺፕ ስልጠና ተሞክሮ ባላቸው ባለሙያዎች እየሰለጠኑም ይገኛሉ።
ስልጠናው ለስራ እድል ፈጠራ የሚያግዛቸውን ክህሎት በማግኘት ተለዋዋጭ የሆነውን የንግዱን ስርአት ለመቀላቀል ትልቅ አቅም ከመሆኑም ባሻገር በራስ መተማመናቸውን እንዲያጎለብቱ ታሳቢ ተደርጎ እየተሰጠ የሚገኝ ስልጠና ነውም ተብሏል።
ከዚህም ጋር በተያያዘ ሰልጣኞችን ወደ ስራ ለማሰማራት የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከ"Job Box " ዝግጅት እና የራስን ስራ ከመፍጠር ጋር ተያይዞ ሰልጣኞችን በማደራጀት ወደ ስራ የሚገቡበትን አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት የተደረ ሲሆን በቀጣይም በቅንጅት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል::
በዚህ መሰረትም ሰልጣኞች ከአሰልጣኞቻቸው ጋር በመሆን በገጠር ና በከተማ ያለውን የሶላር ጥገና ስራ እንዲሰሩና ከተቋማት ጋር በፕሮጀክት መልክ ተሰማርተው አቅማቸውን እንዲያሳዩ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በራሳቸው ተደራጅተው የራሳቸውን የስራ እድል የሚፈጥሩበት ሁኔታ ተለይቶ እንዲመቻችላቸው መደረጉም ተገልፆል።
በመጨረሻም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞች በተወሰነ መጠን የመንግስት ተቋማት ላይ የሚቀጠሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እንዲቻል ለሚመለከታቸው አካላት ሀላፊነት በመስጠት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 18/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
