ሃይማኖታችንስ✞?
✞የኦርቶዶክስ ቻናል✞ > የየዕለቱ ስንክሳር >ኦርቶዶክሳዊ ጥያቄዎች ከነመልሱ > በቅርብ የጀመረው አስተማሪ ታሪኮች > መንፈሳዊ ዝማሬዎች > የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ > መንፈሳዊ ፊልሞች > መንፈሳዊ ትምህርቶችና የተለያዩ ፁፎች #ሁሉም_በየእለቱ
إظهار المزيد962
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-330 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Photo unavailableShow in Telegram
†
🕊 💖 ሰ ላ ም ታ 💖 🕊
❝ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ❞
🕊
❝ ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ❝ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ❞ ]
❝ [ አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ንጉሠ ነገሥት ወእግዚኣ አጋእዝት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት… ኦ ትዕግሥት ወአርምሞ በፍቅረ ዚአነ በጽሐ እስከ ለሞት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ወንሕነኒ ንግበር በዓለነ ቅድስተ ፋሲካ በሐሴት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ገባሬ ሕይወት ክርስቶስ ፤
ትርጉም ፦ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ … ወዮ ትዕግሥትና ዝምታ ፣ እኛን ከመውደዱ የተነሣ እስከ መሞት ደረሰ ፣ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ እኛም የተቀደሰች በዐላችንን ፋሲካን [ ትንሣኤን ] በደስታ እናክብር ፣ ሕይወትን የሠራ [ የፈጠረ ] ክርስቶስ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ። ❞
[ ድጓ ዘፋሲካ ]
🕊
❝ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን ከይዶ መቃብሪሁ ለአዳም ወበትንሣኤሁ ገብረ ለነ ሰላመ ለጻድቃን አብርሃ ፤
ትርጉም ፦ የአዳምን መቃብር ረጋግጦ ክርስቶስ ከሙታን ተነሣ ፣ በትንሣኤውም ለጻድቃን ብርሃን የሚሆንን ሰላምን ለእኛ አደረገልን። ❞
[ድጓ ዘፋሲካ]
† † †
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ † 🕊
† አናንያ : አዛርያና ሚሳኤልን እንዲያው በቀድሞው አጠራር ሠለስቱ ደቂቅ [ሦስቱ ሕጻናት] እንላቸዋለን እንጂ ለእኛስ በእድሜም : በጸጋም : በትሩፋትም አባቶቻችን ናቸው::
ቅዱሳኑ የወቅቱ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጆች ናቸው:: ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ ሕዝቡን ሲማርክ አብረው ተማርከው ባቢሎን ወርደዋል::
ንጉሡ ከምርኮ ወጣቶች ለቤተ መንግስት ሲመርጥ ሦስቱ ቅዱሳንና ዳንኤል ተመርጠው የምቾት ሕይወት ተዘጋጅቶላቸው ነበር:: ነገር ግን በምግብና በአምልኮ ከአሕዛብ ጋር መተባበርን አልፈለጉምና ምርጫቸው ጾምና ጸሎት ከቆሎ ጋር ሆነ:: ምንም እንኳ በቤተ መንግስት ውስጥ ቢኖሩ : ምንም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑ ለእነርሱ ከእግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ አልነበረምና በጥሬ ቆሎ ተወስነው ኖሩ::
አምላካቸው ከሃሊ ነውና በውበትም ሆነ በጥበብ በባቢሎን ምድር ከነርሱ የሚደርስ አልተገኘም:: ንጉሡም በባቢሎንና በአውራጃዋ ላይ ሾማቸው:: ስማቸውንም በአማልክቱ ስም ሲድራቅ : ሚሳቅና አብደናጐ አላቸው::
ከነገር ሁሉ በኋላ አሕዛብ ቀንተውባቸዋልና የክፋት አዋጅን አሳወጁ:: ናቡከደነጾር ፷ [60] ክንድ ቁመት ያለውን የወርቅ ምስል አቁሞ "ስገዱ" ቢላቸው አይሆንም በማለታቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ እሳት ተፈረደባቸው:: ነበልባሉ ከጉድጓዱ ወደ ላይ ፵፱ [49] ክንድ ቢነድም ቅንጣት ያህል ፍርሃት አልጎበኛቸውም::
ወደ እሳቱም ሲጥሏቸው መልዐከ አድኅኖ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ አዳናቸው:: ከሆነው ነገር የተነሳ አሕዛብ አፈሩ:: ናቡከደነጾር ግን ከዙፋኑ ተነስቶ የቅዱሳኑን አምላክ እግዚአብሔርን ባረከ::
ከዚያች ቀን በኋላ አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል በአት አጽንተው : በጾምና በጸሎት ተወስነው ኑረዋል:: ነፍሳቸው ከሥጋቸው ስትለይ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆኗል:: ቅዱስ ዳንኤልና ናቡከደነጾር ተሯሩጠው ቢሄዱ ሦስቱም በአንድነት ዐርፈው ተገኝተዋል:: ንጉሡ በእጅጉ ይወዳቸው ነበርና በወርቅ በተለበጠ ሳጥን ቀብሯቸዋል:: ስሞት ከመካከላቸው ቅበሩኝ በማለቱ ዛሬ ድረስ ለበቁ አባቶች የአራቱ መቃብር ባቢሎን ውስጥ ይታያል::
ቅዱሳን አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል [ሲድራቅ : ሚሳቅና አብደናጐ] ያረፉት ግንቦት ፲ [10] ቀን ሲሆን ዘመኑም ከክርስቶስ ፭፻ [500] ዓመት በፊት ነው::
† አምላካቸው ከእሳት ባወጣቸው ቀንም :-
"ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ::
ስቡሕኒ ውዕቱ ወልዑልኒ ውዕቱ ለዓለም::" የሚለውን ምስጋና ፈጣሪ ገልጾላቸው ደርሰውታል:: [በእሳቱ ውስጥ ሆነው ተናግረውታል::]
ድርሰታቸው ፪ [2] ወገን ሲሆን ባለ ስድስት አንቀጹ ምስጋናቸው ከ፮፻ [600] ዓመት በኋላ ክርስቶስ እንደሚወለድ የሚያሳይ ነው:: ሌላኛውና ፴፫ [33] አንቀጾች ያሉት ምስጋናቸው ደግሞ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ለ፴፫ [33] ዓመታት እንደሚመላለስ ያጠይቃል::
ቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ ካረፉ ከ፱፻ [900] ዓመታት በኋላ [ማለትም ከክርስቶስ ልደት በ፬፻ [400] ዓመታት] ታላቁ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ቤተ ክርስቲያንን አንጾላቸው ነበርና አጽማቸውን ሊያገኝ ተመኘ::
ወዳጁን ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ጠርቶ "አባ! አጽመ ቅዱሳንን ባቢሎን ወርደህ አምጣልኝ?" አለው:: ቅዱሱ ሐጺር ዮሐንስም በደመና ተጭኖ ባቢሎን ገባ:: በቅዱሳኑ መቃብር ፊትም ሰግዶ አለቀሰ:: ሠለስቱ ደቂቅም "ወዳጃችን! ምን ሆንክ?" አሉት::
ቅዱሱም መልሶ "ወደ ግብጽ እንሒድ:: አባ ቴዎፍሎስ ይፈልጋቹሃል" አላቸው:: እነሱም "ለቅዱሱ ቴዎፍሎስ እንዲህ በለው:: እግዚአብሔር ዋጋህን ይክፈልህ:: ግን አጽማችን እስከ ዓለም ፍጻሜ ባቢሎንን አይለቅም:: ለክብርህ ግን እንመጣለን::"
"ለምልክትም ይሆን ዘንድ መብራት ሳታበራ በሌሊት ጠብቀን በለው" ብለው ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ባርከው ሸኙት:: ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርም መጥቶ መልእክቱን አደረሰ:: በዕለተ ቅዳሴ ቤታቸው ቅዱሳን:- ቴዎፍሎስ : ቄርሎስ : ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርና ሌሎችም ከምዕመናን ጋር በጨለማ ሳሉ ቤተ ክርስቲያኑ ቦግ ብሎ በራ::
እጅግ የሚደነቅ ብርሃንም ከበባቸው:: በብርሃኑ መካከል ሠለስቱ ደቂቅ ሲያልፉ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ሕዝቡም በደስታና በዝማሬ የቅዱሳኑን ቅዳሴ ቤት አክብሯል::
† በረከታቸው ይደርብን::
🕊
[ † ግንቦት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ሠለስቱ ደቂቅ ቅዱሳን [አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል]
፪. ቅዱስ አብርሃም ጸራቢ [ሰማዕት]
፫. አባ ሚካኤል ገዳማዊ
፬. አባ ይስሐቅ ግብጻዊ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፬. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፭. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፮. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፯. ቅዱስ ዕፀ መስቀል
† " ናቡከደነፆርም መልሶ:- መልአኩን የላከ : ከአምላካቸውም በቀር ማንንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን : የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን : በእርሱ የታመኑትን ባርያዎቹን ያዳነ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ:: " † [ዳን.፫፥፳፰] (3:28)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
01:45
Video unavailableShow in Telegram
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ፍ ኖ ተ አ በ ው ! ]
የእውነተኞቹ አባቶቻችን የተጋድሎ ሕይወት ይህ ነው !
❝ የቀደሙ አባቶቻችን ጻድቃን ቅዱሳን በእምነታቸው የእሳቱን እቶን አቀዘቀዙት፡፡ በዚያም በባዕድ ሀገር ባርነቱን ፣ መከራውን ፣ ሥቃዩን ሁሉ ታግሠው ኖሩ፡፡
እኛ ጥቂቱን መከራ እንኳ ያለመታገሣችን ምክንያቱ እምነታችን ጎዶሎ ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ትዕግሥት ከእኛ ዘንድ የራቀ ሆነ፡፡ ❞
[ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ]
❝ ቅዱሳን በጾምና በጸሎት በልመናና በስግደት በሰላም ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገሩ ፤ በመስቀሉም ታምነው ወደ ርስታቸው ገቡ ፤ እኛም በታላቋ ዕለት በዚያች ሰዓት ይምረን ዘንድ እርሱን እንታመን። ❞
[ ቅዱስ ያሬድ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
Photo unavailableShow in Telegram
†
🕊 💖 † † † 💖 🕊
[ ክርስቶስ ነጻነት አወጣን ! ]
🕊
†
❝ በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን ፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ። ❞
[ ገላ . ፭ ፥ ፩ ]
[ 💖 የ ነ ፍ ስ ነ ፃ ነ ት 💖 ]
] † [
🕊 ምክረ ቅዱሳን 🕊
🕊 [ በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ]
† † †
💖 🕊 💖