Tomi
الذهاب إلى القناة على Telegram
2 324
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
2 324
Repost from YeneTube
"የሬሜዲያል ፕሮግራም ተመዝጋቢዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እስከ ህዳር 12 ድረስ ማስተካከል ይችላሉ" - የትምህርት ሚኒስቴር
በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የሬሜዲያል (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤቱ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ህዳር 12 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በዚህ ዓመት የሬሜዲያል ፕሮግራም አዲስ አበባ፣ ሀዋሳ፣ አርሲ፣ ኮተቤ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሮግራሙን የማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
2 324
ማስታወቂያ
የ2016 የት/ት ዘመን ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 7 እንደሆነ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም ክልል ት/ት ቢሮ ባስተላለፈው መሰረት የ2016 የት/ት ዘመን ት/ት የሚጀመረው መስከረም 14 መሆኑን አውቃችሁ ላልሰሙትም በማሰማት የመማሪያ ቁሳቁሶችንና የደንብ ልብሳችሁን በአግባቡ በመልበስ በተባለው ቀን በት/ት ገበታችሁ ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
2 324
ለመላው የBNB ት/ት ማዕከል ቤተሰቦች በ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ባገኘነው ውጤት እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ ከሲዳማ ክልል 10 ክፍተኛ ውጤቶች መካከል አንደኛ የሆነውን ውጤት ጨምሮ አራቱ የት/ት ቤታችን ተማሪዎች ሆነዋል፡፡ ይህንን ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ ባጠቃላይ የት/ት ቤታችን ማህበረሰብ የሁላችን የድካም ውጤት ነውና በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡
2 324
ማስታወቂያ
ለBNB የትምህርት ማዕከል አዲስ ለምትመዘገቡ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የመግቢያ ፈተና ምዝገባ የሚካሄደዉ ነሐሴ 1 እና 2 ሆኖ ፈተናዉ የሚሰጠዉ ነሐሴ 4/2015 ዓ.ም ይሆናል፡፡ ፈተናዉን ያለፉ ተማሪዎች ምዝገባ ነሐሴ 5/12/2015 ብቻ ይፈጸማል፡፡
2 324
ማስታወቂያ
ለBNB የትምህርት ማዕከል ነባር ተማሪዎች በሙሉ፡-
የ2016 የትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሄደዉ ከሐምሌ 24 እስከ 28 ብቻ መሆኑን እየገለጽን በተጠቀሱት ቀናት በማይመዘገብ ነባር ተማሪ ቦታ በነሐሴ 1 እና 2 በአዲስ ተማሪ ተክተን ምዝገባዉን የምንዘጋ መሆኑን በጥብቅ እናሳዉቃለን፡፡
