ሃይማኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
الذهاب إلى القناة على Telegram
767
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
#የአንባቢ_ጥያቄ
'' የቅዱስ ኤፍሬም ምስል ላይ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን በመስቀል ስትባርከው ይታያል እና እመቤታችን መስቀል ማሳለም ትችላለች ?''
ቅዱሳን ሲሳሉ መስቀል የሚይዙት ክርስቲያን ሆነው ለክርስቶስ የታመኑ መሆናቸውን ለመግለጽ ነው። ሰማዕታት ደግሞ ዘንባባንም ይይዛሉ። ስለ ድል መንሳታቸው።
እመቤታችን መስቀል መያዟ ልክ እንደ ካህናት ባለ ሳይሆን እስሷ ጸጋ ሙሉ እመቤት ነችና ጸጋን የምትሰጥ መሆኗን ለማሳየት ነው ለሚጠሯት ጸጋን ትሰጣለችና። እጅግ ለሚወዳት ቅዱስ ኤፍሬምም ጸጋዋን ሰጠችው። ባረከችው።
አንድም በሐዲስ ኪዳን የመጡ ልዩ ልዩ ጸጋዎች የተገለጡት ከክርስቶስ የመስቀል ሞት በኋላ ነውና የልጇን መስቀል ይዛ ጸጋዋን ታካፍለናለች።
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ በከበረ ካህንና ነቢይ ምልጃና ጸሎት ይማረን። አሜን።
ሰኔ ፴
'' እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።'' - ዮሐ 14:28
'' እግዚአብሔር ከዓለም በፊት እስከ ዘለዓለምም ድረስ፤ እግዚአብሔር በሦስትነቱ አለ፣ እግዚአብሔር በመለኮቱ፣ እግዚአብሔር በመንግስቱ አለ ።
ከጎሕና ከጽባሕ በፊት፣ ከመዓልትና ከሌሊት በፊት፣ መላእክት ሳይፈጠሩ እግዚአብሔር በመንግስቱ አለ ።
ሰማያት ሳይዘረጉ፣ የየብስም ፊት ሳይታይ፣ ሐመልማላት ሳይበቅሉ እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ ፡፡
ከፀሓይና ከጨረቃ፣ ከከዋክብትም በፊት፣ ከብርሃናትም መመላለስ በፊት እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ ፡፡
ከሚንቀሳቀሱ እንስሳት በፊት፣ ከሚበሩም አዕዋፍ በፊት፣ ከባሕር አራዊት በፊት እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ ፡፡
አዳምን በርሱ አምሳልና አርኣያ ሳይፈጥረው፣ ትእዛዛቱንም ሳያፈርስ እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ ፡፡
ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል፤ ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለምም ፡፡''
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ
+ #እይታዬ ~ ፮ +
'' እስቲ ኢየሱስ ጌታ ነኝ አምላክ ነኝ ያለበትን ቦታ አሳዩን ''
( የሙስሊሞች ጥያቄ)
+ ጌታና አምላክ ያለበትን ቦታ ስናሳያቸው ደግሞ '' አይ ጌታ ለመባልማ ሌሎች ሰዎችም ጌታ ተብለዋል ፤ ሙሴም አምላክ ተብሏል '' ብለው ይመልሳሉ።
በቋንቋ ወስጥ language limitation አለ። ሰውም ፈጣሪም በእንድ ቃል ጌታ አምላክ ሊባሉ ይችላሉ፥ የቃላቱን አግባብና ፍቺ መለየትና መገንዘብ ያለብን እኛ ነን። የክርስቶስ ጌትነት አምላክነት የባሕርይ ነው ማለትም አብና መንፈስቅዱስ በሚጠሩበት የጌትነትና የአምላክነት ክብር ኢየሱስም ጌታ አምላክ ተብሎ ይጠራል። ቅዱሳን ሰዎች ጌታና አምላክ ቢባሉ በጸጋ ነው ወይም እግዚአብሔር የሰጣቸው ሥጦታ ነው ልክ ሙሴ በፈርዖን ላይ አምላክ እንደሆነ። ሙሴ አምላክ ሲባል እንደ እግዚአብሔር #ፈጥረከናል እየተባለ እንዳልሆነ ልብ በሉ።
🍊 ማንም ቅዱሱ ሰው ቢኖር ከአብ እኩል የባህርይ አምላክ ነው የተባለ የለም፥ እነርሱ አምላክ ቢባሉ በጸጋ ነውና። የክርስቶስ ኢየሱስ አምላክነት ግን የባሕርይ ስለሆነ እንደ አብ ባለ የአምላክነት ክብር አብሮ አምላክ እየተባለ ይጠራል -+- " ለሚወጣ ሁሉ በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት።" (2ኛ ዮሐ1:9) -+-
=> በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው #አምላክ_የለውም ~ ስለዚህ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር ሰው ደግሞ አምላክ አለው ማለት ነው። አሁን መገንዘብ ያለብን ነገረ << አምላክ>> በሚለው ቦታ ''የአብና የወልድ'' ስም ገብቷል --- '' በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት'' ስለዚህ ከዚህ የምንረዳው ነገር ቢኖር :-
🍋 ወልድ ከአብ እኩል አምላክ መባሉን ይህም እንደ ፍጡራን የጸጋ አምላክነት ሳይሆን አንደ አብ የባሕርይ አምላክ መሆኑን።
🍋 ማንም ፍጡር ከአብ እኩል አምላክ ተብሎ እንዳልተጠራ ፤ ወልድ ግን ፈጣሪ ነውና የባሕርይ አምላክ መሆኑን ለማስገንዘብ ከአብ እኩል አምላክ ተባለ።
ፍቅሩ ይደርብን።
አቤቱ ተወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፦
የምንኮራበት ክብራችን ፡ የምንደምቅበት አክሊላችን አንተ ነህ ፤ ቀና ያልንብህ ትምክህታችን ፡ ያረፍንብህ ክንዳችን አንተ ነህ ፤ እግራችን እንዳይሰናከል የምትጠብቀን፡ እንዳንባዝን የምታረጋጋን አንተ ነህ፤
ጌታችን ሆይ ፦ ፍቅርህን የሚመስለው የለም፡፡ እንዳንወድቅ የምትጠብቀን ብንወድቅ የምታነሳን አንተ ነህ ፤ እንዳንደክም የምትራራልን ብንደክም የምታበረታን አንተ ነህ ፤ እንዳንታመም ባንተ እንታመናለን ብንታመምም ስላንተ ተስፋ አለን፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? እንዳንሰናከል መላእክቱን ስለእኛ አዘጋጀልህን ፡ ጠላቶች እንደበዙብን አይተህ ወዳጆችን አበዛኅልን ፤
ፈተናወቻችንን አይተህ መውጫውን ደግሞ አመላከትከን ፡ የቀደመውን ፍቅራችንን ብንቀንስ ያንተን ፍቅር አበዛህልን ፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ራቅንህ ፡ አንተ ወደኛ ቀረብክ፤ በግብራችን ናቅንህ አንተ ግን እኛን አከበርክ፤ ያለአንተ መኖር እንደማንችል ታውቃለህና ክፋታችንን ሳታይ ራራህልን ስንፍናችንን ሳታይ ቀረብከን ፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ተወዳጅ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ማንም የለንምና ክብራችንን አውቀን እንኖር ዘንድ አንተን ሳናስብ የምንውልበት ጊዜ አይኑረን፡፡
ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን፡፡
(ቅዳሴ ያዕቆብ ዘስሩግ)
'' ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ''
'' ኢየሱስም፡— ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።''
- ማርቆስ 10:18 -
ይህንን ቃል የተናገረው ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። አንዳንድ ወገኖች ይህንን ቃል በመጥቀስ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር አይደለም ፤ ቸር እግዚአብሔር ብቻ ነው ፥ ስለዚህ እርሱ እግዚአብሔር አይደለም ( ሎቱ ስብሐት) ይላሉ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር እግዚአብሔር እንደሆነ ምንም ጥርጥርም የለው። እንኳን ጌታችን፤ ብዙ ሰዎችም ሳይቀር ቸር ተብለዋል...እኛ ቸሮች እንድንሆንም ታዘናል።
🌿 '' ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ፤ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ ትገኛለህ፤'' (መዝ 17:25)
🌿 '' ቸር ሰው ይራራል ያበድራልም፥ በፍርድም ነገሩን ይፈጽማል።'' ( መዝ 110:5)
🙌 የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት ሰው እንኳ ከሚሰራው ሥራ አንዱ የቸርነት ሥራ ነው።
'' የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፣'' (ገላ 5:22)
እንዲህ ከሆነ የጌታችን ንግግር እንዴት ይታያል?
ጌታችን ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር
አምላክ ነውና በሰዎች ልቡና ያለውን ተንኮልና ቀናነት በራሱ ስለሚያውቅ ( ዮሐ 1፡49 ፣ ዮሐ 4፡18 ) የዚህንም ሰው የልቡን ሐሳብ አወቀ። ይህ ሰው በልቡ የኢየሱስን እግዚአብሔርነት ሳያምን እንዲሁ በአፉ #ቸር_መምህር-ሆይ ብሎ የተጠራው። ጌታችንም ከእግዚአብሔር በቀር ሰው በባሕርዩ ቸር ሊባል አይገባውም አለው ( ቅዱሳን ቸር ቢባሉ በጸጋ ነውና)
ጌታችንን ቸር ያለው ሰው እርሱ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ እንደሆነ ሳያውቅ - ሳያምን ነበርና እንዲሁ ቸር ብሎ የጠራው።
ስለዚህ አምላክነቴን እግዚአብሔርነቴን ሳታውቅ ሳትረዳ ስለምን ቸር ትለኛለህ? አምላክነቴን ተረድተህ ቸር በለኝ። ከእግዚአብሔር( ከእኔ) በቀር ቸር ማንም የለምና ማለቱ ነው።
👏 ኢየሱስ ቸር እንደሆነ
'' የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።'' (2 ቆሮ 8:9)
የኢየሱስን እግዚአብሔርነቱን አምነን ቸሩ አማኑኤል ሆይ እንበለው።
ይቆየን።
@WwEotc
'' እውነተኛ አምላክ #ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።''
- ዮሐ 17:3
#ብቻ የሚለው ቃል የወልድና የመንፈስ ቅዱስን አምላክነት ውድቅ አያደርገውም። አብ አውነተኛ አምላክ ብቻ ነው ማለት እንደ ወልድ ሥጋን እንዳልተዋሐደ ወይም ሰው እንዳልሆነ ለማሳየት ነው። ወልድ ደግሞ እውነተኛ አምላክና ፍጹም ሰው ተብሎ ይጠራል ፤ ሥጋን ተዋሕዷልና። አብ ግን አውነተኛ አምላክ ብቻ ተብሎ ይጠራል።
ወልድ እውነተኛ አምላክ ስለመባሉ:-
'' የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።''
- 1 ዮሐንስ 5:20
https://t.me/zikirekdusn
✝✝✝ እንኩዋን አደረሳችሁ ✝✝✝
"✝' በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ "✝'
+*" ሰማዕታተ ኢትዮጵያ "*+
አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡
ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢሱስ ክርስቶስ፡፡
ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡
ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡"
አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡
አሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡
ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡"
በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡"
በረከቶሙ: ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡
ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ፡፡
ምስለ ሰማዕታት ዘግብጽ መከራቲክሙ ዘሐብራ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶሳዊት ሐራ፡፡
እፎ ክህልክሙ ተዐግሦ ጽኑዕ መከራ፡፡
እስከ ክሳውዲክሙ በአሲስ ተመትራ፡፡
(ኢያዕመርኩ ከመ መኑ ጸሐፎ)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
በቅድስት ቤተክርስቲያን የቅዱሳት ስዕላት አሳሳል ሥርዓት መሠረት -- የቅዱሳን መላእክት ቅዱሳት ስዕላት ሲሳሉ ገላቸው/ ጡንቻቸው ታይቶ አይሳልም። ሙሉ ልብስን (የካህናትን ልብስ) ይለብሳሉ እንጂ ይህም ሃይላቸው ሃይለ እግዚአብሔር መሆኑን ለማሳየት ነው። ሰይጣንን ድል ቢነሱ እኛንም ቢረዱን ቢያድኑን ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ሃይል ነውና። ገላቸው እየታየ የሚሳሉ ከሆኑ ግን በራሳቸው ማዳን ይችላሉ ማለት ነውና ስእላትን ለጸሎትና ለተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎት ስንጠቀም ይህንን እንወቅ።
መልካም ቀን።
እነዚህ ጃማይካውያን ናቸው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በራሳቸው ቋንቋ ተምረው በራሳቸው ቋንቋ እያገለገሉ ነው።
የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ክልላዊት ሳትሆን ኩላዊት ቤተክርስቲያን ነች።
አንድ ሲኖዶስ!
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት ከሰጠው ጸጋ አንዱ ልሳን መናገር ሲሆን ይህም በአለም የሚገኙ ሰዎችን በየቋንቋቸው እንዲያስተምሩ ነው። ቤተክርስቲያንም በነቢያትና ሐዋርያት መሰረት ላይ የሆነች እውነተኛ ተቋም ነችና ይህንን አገልግሎት ዛሬም እያከናወነች ነው።
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትርያርክ
አንድ ቤተክርስቲያን
