ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 369 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 754 في فئة النقل والمرتبة 2 531 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 369 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 19، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 40.59‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 423 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 060 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 369
المشتركون
+1924 ساعات
+677 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
photo_2021-04-12_11-16-19.jpg0.86 KB

photo_2021-04-12_11-16-20.jpg0.81 KB

photo_2021-04-12_11-16-21.jpg0.40 KB

photo_2021-04-12_11-16-22.jpg0.36 KB

photo_2021-04-12_11-16-29.jpg0.82 KB

photo_2021-04-12_11-16-30.jpg1.10 KB

የጅግጅጋ ገለለሽ -ደገሃምዶ -ሰገግ የአሰፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንታባ ፕሮጀክት

ከአምስት ወራት በፊት የተጀመረው የጅግጅጋ ገለለሽ -ደገሃምዶ -ሰገግ የአሰፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንታባ ፕሮጀክት ክንትራት ሁለት በመፋጠን ላይ ነው። በስፍራው የሚገኙ የመንገድ የግንበታ ፕሮጀከቶችን የስራሰ እንቅስቃሴ የተመለከተ የመስክ ቅኝት ሰሞኑን ተካሂዳል። በዚህም የጅጅጋ ገለለሽ ደገሃምዶ ሰገግ በጥሩ ደረጃ እየተገነባ መሆኑ ተመላክቷል ። የስራ ተቋራጩ የካፕ ግንባታን ጨምሮ ለግንባታ ሂደት የሚዉሉ የተለያዩ ማሽነሪዎች ተከላን አጠናቆ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ ስራዎች፤የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት ፤ የዉሃ መፋሰሻ ቱቦዎች ማምረት ብሎም የአስፋልት ጠጠር መፍጫ ማሽን ተከላ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ግንባታው እስከ 32 ሜትር እርዝመት ያላቸው አምስት ድልድዮች ስራንም ያካተተ ነው። በአጠቃላይ አሁናዊ የግንባታ እቅድ አፈጻጸሙ 11 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህም ቃል እንደተገባው ፕሮጀከቱን ፈጥኖ ለማጠናቀቅ እንደሚያስችል ታምኖበታል። ። መንገዱን በአንድ ቢሊየን ስምንት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊየን ብር በላይ ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን እያከናወነ ያለው ቤአኤካ ጄኔራል ቢዝነስ የተባለው አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ፤ የፕሮጀከቱን የማማከርና ቁጥጥር ሰራዉን የሚያካሄደዉ ደግሞ ሲ ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ ነዉ፡፡ የጅግጅጋ-ገለለሽ_ደገሀምዶ ሰገግ መንገድ 109.82 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። ለግንባታ የሚያስፈልገውን ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል የመንገድ ፕሮጀክቱ በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ተጠናቆ ለህዝቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል። በተያያዘ ዜናም በመስክ የስራ ቅኝቱ የዚሁ የመንገድ ከፍል የሆነው እና 52.2 ኪ.ሜ የሚረዝመው ኮንትራት ሶስት የደገሃምዶ -ሰገግ የመንገድ ግንባ በጥሩ የስራ አፈጻጻም ላይ ይገኛል ። የመንገድ ፕሮጀከቱ የሰብ ቤዝ ስራ፤የአፈር ቆረጣ ፤ የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት እንዲሁም የውሀ ማፍሰሻ ቦዮችን የመገንባት ስራ እየተካሄደ ነው፡፡ ግንባታውን የሚያካሂደው ማርካን ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየሰራ የሚገኘው ብርሀን ኮንስትራክሽን ዲዛይን ኮንሰልታንት ኃ/የተ/የግል ማህበር ነው፡፡ የአስፋልት ኮንክሪት መንገዱ እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 768 ሚሊየን 698ብር በጀት ነው። በኮንትራቱ ዉል መሰረት የመንገድ ግንባታዉ በሶስት ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሚሆን ይሆናል፡፡ የጅግጅጋ ገለለሽ ደጋሃመዶ -ሰገግ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጂጋ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር ዘመናዊ በሆነ የአስፋልት መንገድ ተደራሽ የሚያደርግ ነው በክልሉ በርካታ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን የሚያስተሳሰር በመሆኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳው የላቀ ያደረጋዋል። በተለይም በአካባቢው ያሉትን አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍሎች የእንሰሳት ሀብታቸውን በቀላሉ እና በተሻለ ዋጋ ወደ ማዕከላዊ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ። የዚሁ የመንገድ አካል የሆነው የጅግጅጋ-ገለለሽ 55.4 ኪ.ሜ ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ከወራት በፊት ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት መሆኑ ይታወሳል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በባህር ዳር ከተማ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን ድልድይ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ የፌደራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የኢትዮጵያ መነገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢነጂነር ሀብታሙ ተገኝ ታድመዋል ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የድልድዩ ግንባታ መጠናቀቅ ዘመናዊ እና አማራጭ የመጓጓዣ መንገድ እንዲኖር በማስቻል የወጪ ንግድ ቀጠናን ውጤታማነትን ያቀላጥፋል ብለዋል። የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት ከባድ እና ፈታኝ የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች የኮንክሪት ሙሌት የላይኛው ክፍል ስራ በቅርቡ መጀመሩ ይታወሳል። በአሁኑ ወቅት አራቱም የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚያርፈዉ የመጀመሪያዉ የኮንክሪት ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው /የገርደር /ወይም የላይኛው የድልድዩ ክፍል የኮንክሪት ሙሌት ስራ የተጀመረው። ይህን የተመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶከተር አበይ አህመድ አጠቃላይ ስራው ወደ ላቀ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው ብለዋል። በዘመናዊነቱ በሀገራችን ተጠቃሽ የሆነዉና 380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለዉ የባህር ዳር አባይ ወንዝ ድልድይ ግንበታ ከአንድ አመት በፊት ነው የተጀመረው ። ቀጣይ የድልድዩን የግንባታ ክፍሎችንም በብቃት ለማከናወን አሁን የደረሰበት የግንባታ ደረጃ የላቀ ሚናን ያበረክታል። የግንባታው ቀጣይ ሂደት በተንሸራታች ፎርም ወርክ ወደ ግራና ወደ ቀኝ በስምንት አቅጣጫ ለመገንባት እየተሰራ ነው። አዲሱ ድልድይ ነባሩንና በአገልግሎት ብዛት ለጉዳት የተዳረገውን ድልድይ የሚተካ ሲሆን፥ ግንባታው በቻይናው ኮሙዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ እንዲሁም የቱርኩ ቦቴክ እና የሃገር ውስጥ አማካሪው እስታዲያ በተቆጣጣሪነት እና በአማካሪነት እየሰሩ ነው

1. System administrator 2. Office Project Manager 3. Project Manager 4. Project /Group/ Member 5. Client 6. Project Owner 7. CEO

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የዱርቤቴ-ቁንዝላ-ገላጎ-መተማ መንገድ ግንባታ አካል የሆነዉ፣ የዱርቤቴ-ቁንዝላ-ሻኁራ-ፍንጅት ምዕራፍ አንድ እና ገላጎ-ገንደውሃ ምዕራፍ ሶስት የመንገድ ግንባታን አስጀመሩ። በዱር ቤተ ከተማ በተከናወነው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለስልጣናት ታድመዋል። በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነቡት ሁለቱ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አምስት ቢሊዮን ሶስት መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን ብር ዋጋን የሚጠይቁ ሲሆን 261 ኪ.ሜ ርዝመት አላቸው። አጠቃላይ የግንባታ ወጪው የሚሸፈነውም በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቶቹን ግንባታ ስራ የሚያካሄደዉ ዚዢያንግ ኮሚኒኬሽን ኮንስትራክሽን ግሩፕ የተባለ የዉጭ ሀገር የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ በመድረኩ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ይህ ፕሮጀክት ሀገራዊና ቀጠናዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ህብረተሰቡ ለፕሮጀክቱ ስኬት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ አሳስበዋል። የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው የዱርቤቴ-ገላጎ-መተማ መንገድ በምርታማነትቱ ለሚታወቀው ምዕራብ አቸፈር ወንድዬ እና ለጎንደር አካባቢ ጠቀሚታው ከፍተኛ ስለመሆኑ ያነሱት ደግሞ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ናቸው። የወሰን ማስከበር ጉዳይ ለፕሮጀክቱ ስኬት እንቅፋት እንዳይሆን ጠንክረው እንደሚሰሩ በአካባቢው ህብረተሰብ ስም ቃል ገብተዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ በበኩላቸው መንገዱ ለነባሩ ከአዲስ አበባ-ባህርዳር-ጎንደር-መተማ መንገድ እንደ አማራጭ ሆኖ የሚያገለግል ከመሆኑም ባሻገር ለምዕራብ አቸፈር እና ለጎንደር ህዝብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ብለዋል። ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የህብረተሰቡ ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ የአካባቢው የመስተዳድር አካላትና ነዋሪዎች አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። ይህ መንገድ ተጠናቆ ለህዝቡ አገልግሎት መስጠት ሲጀምረ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም የገቢ ወጪ ዋና መስመር የሆነዉን መተማን ከሱዳን ጋራ በማገናኘት የሁለቱን ሃገራት የንግድ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስርን የበለጠ ያጠናክራል፡፡ ከዚህም ባሻገር በዋነኛነት ነባሩን የደብረማርቆስ-ባህርዳር ጎንደር-አዘዞ-መተማ መንገዶችን ያስተሳስራል። አርሶ አደሮች የሚያመርታቸውን የአዝዕርት ምርቶች በተለይም ፣ ሰሊጥ ፣ ጤፍ ፣ ለውዝ ፣ ገብስ ፣ በቆሎ ፣ ጥቁር አዝሙድ እና ሌሎች ምርቶቹንም በቀላሉ ወደ ገቢያ በማድረስ ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅርፍ ህብረተሰቡ ተሽከርካራዎችን ተጠቅሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ጊዜን በማሳጠር ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በመንገዱ መበላሸት ምክንያት ለአላስፈላጊ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ይወጣ የነበረ ወጪን ይቀንሳል፡፡ በመንገድ መሰረተ ልማት እጥረት ተራርቀው ለነበሩ የአካባቢው ህብረተሰቦች በቅርበት የመገናኘት እድልን ከመፍጠሩም ባሻገር በመስመሩ ያሉ ትንንሽ መንደሮች ወደ ከተማ እንዲያድጉ እና ይበልጥ በኢኮኖሚ እንዲነቃቁ ይረዳቸዋል፡፡ ለበርካታ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጠርላቸዋል፤ በተያያዘም የጤና ፣ የትራንስፖርት ፣ እና የሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን ተደራሽነት ያስፋፋል፡፡ በጥቅሉ የዚህ መንገድ መገንባት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳለጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ የራሱን ጉልህ ሚና ይጫወታል ፡፡

የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት ከባድ እና ፈታኝ የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች የኮንክሪት ሙሌት የላይኛው ክፍል ስራ ተጀመረ። በአሁኑ ወቅት አራቱም የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚያርፈዉ የመጀመሪ
+5
የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት ከባድ እና ፈታኝ የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች የኮንክሪት ሙሌት የላይኛው ክፍል ስራ ተጀመረ። በአሁኑ ወቅት አራቱም የቋሚ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚያርፈዉ የመጀመሪያዉ የኮንክሪት ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው /የገርደር /ወይም የላይኛው የድልድዩ ክፍል የኮንክሪት ሙሌት ስራ የተጀመረው። ይህም ፕሮጀክቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ እንዲሸጋገር አስችሎታል። በዘመናዊነቱ በሀገራችን ተጠቃሽ የሆነዉና380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለዉ የባህር ዳር አባይ ወንዝድልድይ በግንባታ ሂደት ላይ እንደሆነ ይታወሳል። ቀጣይ የድልድዩን የግንባታ ክፍሎችንም ብቃት ለማከናወን አሁን የደረሰበት የግንባታ ምዕራፍ የላቀ ሚናን ያበረክታል። የግንባታው ቀጣይ ሂደት በተንሸራታች ፎርም ወርክ ወደ ግራና ወደ ቀኝ በስምንት አቅጣጫ ለመገንባት እየተሰራ ነው። በቀጣይም ሙሉ ግንባታውን በተባለው ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የደምበጫ-ሰቀላ እና የቢቡኝ ወረዳ አገናኝ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ፡፡ በደጋዳሞት ወረዳ ፈረስ ቤት ከተማ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር ፣የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ ብናርፍ አንዱአለም ፣ የምክር ቤት አባላት የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ታድመዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መንግስት በመደበው ከ1 ነጥብ 7ቢልየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የደምበጫ-ሰቀላ እና የቢቡኝ ወረዳ አገናኝ 70 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የህዝቡን የአመታት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል። ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የአካባቢው ነዋሪ ሲቸገር መቆየቱን አስታውሰው ይህ ታሪክ ሊሆን በመቃረቡ ለመላው ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር የክልላችን የመንገድ ጥያቄ ደረጃ በደረጃ ምላሽ እያገኘ ነው ለዚህም በዛሬው እለት የተጀመረው የደምበጫ-ሰቀላ እና ቢቡኝ አገናኝ መንገድ አንዱ ማሳያ በመሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል ፡፡ መንገዱን ዛሬ በይፍ እንዳስጀመርነው ሁሉ ፍጻሜውን ያገኘ ዘንድ መላው የአካባቢው ህዝብ እንዲሁም አመራሩ ያልተቆጠበ ትብብርና ድጋፉን እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ በበኩላቸው የደምበጫ-ሰቀላ እና የቢቡኝ ወረዳ አገናኝ ኮንትራት 1 መንገድ በተባለው ጥራትና ጊዜ እንዲጠናቀቅ ኢመባ አስፈላጊውን ድጋፍ ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚደረግ አረጋግጠዋል፡፡ በዚሁ መርሀ ግብር ላይም ከሰቀላ -አዴት የሚዘልቀው 60 ኪ.ሜትር መንገድ በቀጣይ ወደ ስራ ለማስገባት በሂደት ላይ እንደሚገኘ ጠቁመዋል። መላው የአካባቢው ነዋሪ የስራ ተቋራጩም ሆነ አማካሪ ድርጅቱ ፕሮጀክቱን በጥራትና በብቃት እንዲያጠናቅቅ የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡም አሳስበዋል፡፡ የመንገድ ግንባታውን የሚያካሂደው የአማራ መንገድ ስራዎች ድርጅት ሃላፊ አቶ አስማማው አለማየው ተቋማቸው ግንባታውን በጥራትና በቅልጥፍና ሰርቶ እንደሚያስረክብ ቃል ገብተዋል ፡፡ አገር በቀሉ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር ይሳተፋል፡፡ የደምበጫ- ሰቀላ እና ቢቡኝ አገናኝ ኮንትራት 1 የጠጠር መንገድ በአገልግሎት ሳቢያ በከፍተኛ ሁኔታ የተበላሸ ነው። ፕሮጀክቱ በቀጣይ ከሚኖረው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አንጻር የመንገዱ የጎን ስፋት በወረዳ ከተሞች 29.5 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠሩ ክፍል 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ደረጃውን ጠበቆ ይገነባል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ አካባቢው ከፍተኛ የግብርና ምርቶች ፣ የቁም እንስሳት እና የቀርክሃ ምርት ውጤቶች ወደገበያ አውጥቶ በመሸጥ አምታችንና ሸማችን የጋራ ተጠቃሚ ያደርጋል ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በደጀን ደብረማርቆስ በዳንግላ አድረጎ ባህርዳር የሚገባው መንገድ እና በአዲስ አበባ ደጀን ደብረወርቅ መርጦ ለማርያም ወደ ባህርዳር የሚዘልቀውን ሌላኛውን ዋና መንገድ በአቋራጭ የሚያገናኝ ግዙፍ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት ክፍል ነው ፡፡ በመስመሩ የሚገኙትን ዞኖችና ወረዳዎች በቅርበት በማስተሳሰር ከዚህ ቀደም ከደምበጫ ተነስቶ ሰቀላ ድረስ 70 ኪ. ሜትሩን በተሽከርካሪ ለመጓዝ ይፈጅ የነበረውን አራት ሰዓት ከግማሽ በታች ያሳጥረዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በሚገነባበት አካባቢ የሚገኙትን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ገዳማት፣ የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ የሚል ስያሚ የተሰጠው 4100 ሜትር ሚረዝመው የጮኬ ተራራ መገኛ ስፍራ በመሆኑ የመንገዱ ደረጃ ማደግ የቱሪስት ፍሰቱን ከመጨመር አኳያ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረክታል ፡፡ ፕሮጀክቱ በውል ስምምነቱ መሰረት በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል፡፡