ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 373 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 753 في فئة النقل والمرتبة 2 530 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 373 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 131، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.97‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.25‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 211 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 039 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 375
المشتركون
+424 ساعات
+707 أيام
+13130 أيام
أرشيف المشاركات
የመረዋ - ሶሞዶ - ሰቃ እና ሶሞዶ - ሊሙ መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራን ዛሬ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በይፋ አስጀመሩ። በሊሙ ኮሳ በተካሄደው በዚሁ መርሃ ግብር
+6
የመረዋ - ሶሞዶ - ሰቃ እና ሶሞዶ - ሊሙ መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራን ዛሬ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በይፋ አስጀመሩ። በሊሙ ኮሳ በተካሄደው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህ ፕሮጀክት ከጅማ፣ ከአምቦ፣ ከበደሌ፣ ከነቀምት፣ ከከፋ ፣ከጉራጌ ከሸዋ ጋር በቅርበት እርስ በእርስ ከማስተሳሰር አንፃር ኢኮኖሚያዊና እስትራቴጂካዊ ፍይዳው የላቀ ነው ብለዋል። ስለሆነም በዛሬው ዕለት በይፋ ግንባታው የተጀመረውን ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥረት ውሳኝ በመሆኑ ተባብረው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3773709106003385

የወራቤ- ቦዣባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ በይፈ ተጀመረ። በዛሬው እለት የሰላም ሚንስትር መፈርያት ካሚል፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ዳግማዊት ሞገስ፣የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ ምክትል ርዕሰ መ
+7
የወራቤ- ቦዣባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ በይፈ ተጀመረ። በዛሬው እለት የሰላም ሚንስትር መፈርያት ካሚል፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ዳግማዊት ሞገስ፣የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ድኤታ ወ/ሮ ህይወት ሞሲሳ እና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የክልል እና የፌደራል የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት የፕሮጀክቱን ስራ በይፋ አስጀምረዋል። በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ላይ የሚጀምረው ፕሮጀክቱ 40.5 ኪ.ሜ ርዝመት አለው። ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። https://www.facebook.com/265596510148013/posts/3767581139949515/?app=fbl

በደቡብ ብሄር ብሄርሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በመንገድ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት፤ የተገኙ ዉጤቶች፤ ተግዳሮቶች እና የቀጣይ አካሄዶችን በተመለከተ በሃዋሳ ከተማ ዉይይት ተካሄደ፡፡ የዉይይት መ
+3
በደቡብ ብሄር ብሄርሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በመንገድ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት፤ የተገኙ ዉጤቶች፤ ተግዳሮቶች እና የቀጣይ አካሄዶችን በተመለከተ በሃዋሳ ከተማ ዉይይት ተካሄደ፡፡ የዉይይት መድረኩን በይፋ የከፈቱት የደቡብ ብሄር ብሄርሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ ዕርስቱ ይርዳዉ በመንገድ ዘርፍ በክልሉ ብሎም በሃገር አቀፍ ደርጃ ተጨባጭ ለዉጦች መመዝገባቸዉን አንስተዋል፤ ይህም ዉጤት ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ አስቀምጦ የማስተግበር አስፈላጊነቱን አሳስበዋል፡፡ በዉይይት መድርኩም የትራንስፖርት ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፤ ክብርት የትራንስፖርት ሚንስተር ዴኤታ ኢንጅነር ህይወት ሞሲሳ እና ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኝ የኢትዮጽያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የፌደራል፤የክልል እና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ የዚህ መድርክ ዋና ዓላማ በከልሉ በሚከናወኑ የመንገድ ፕሮጀክቶች ለይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን፤ በዋነኛነት የወሰን ማስከበር እና አልፎ አልፎ ከፀጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮች በመለየት እና መፍትሄ በማስቀመጥ በዘርፉ የላቀ ዉጤት ማስመዘገብ የሚቻልበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንደሆነ ተገልፆል፡፡ በዚህም ርገድ በክልሉ በትግበራ ሂደት ለይ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች በዝርዝር ቀርበዉ በስፋት ዉይይት ተካሄዶል፡፡ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አኩያ በጥራትና በፕሮጀክቶች መዘግየት በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመቅርፍ ጠንካራ የክትትል ስርአት በመዘርጋት እየተሰራ መሆኑ ተገልፆል፡፡ https://www.facebook.com/265596510148013/posts/3765172516857044/?app=fbl

Call For Books Donation
Call For Books Donation

140.2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የጎሬ-ማሻ-ቴፒ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ ። በመንገዱ ጅማሮ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የክልሉ እና የፌደራል የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋ
+1
140.2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የጎሬ-ማሻ-ቴፒ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ ። በመንገዱ ጅማሮ መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የክልሉ እና የፌደራል የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የጎሬ-ማሻ-ቴፒ ፕሮጀክት የደቡብ ፣ የጋምቤላ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በአቋራጭ የሚያገናኝ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱን በ4.5 ቢሊዮን ብር ለመገንባት ጨረታዉን አሸንፎ ወደ ስራ የገባዉ የደቡብ ኮሪያው ሃዮንዳይ ዴቨሎፕመንት ካምፓኒ ነው። የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ደግሞ ሱሶንግ ኢንጂነሪንግ ከሃገር በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በጋራ ያከናውናሉ፡፡ የግንባታዉ ሙሉ ወጪ የሚሸፈነዉም በኢትዮጵያ መንግስት እና በኮሪያው ኤግዚም ባንክ ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጅማ አድርጎ በመቱ ወደ ጋምቤላ የሚዘልቀው ዋና መንገድ እና ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጅማ በኩል ወደ ሚዛን ቴፒ የሚሄደውን ሌላ ዋና መንገድ በአቋራጭ የሚያስተሳስር ነው። የመንገዱ ስራ በአራት ዓመት ከስድስት ወራት ዉስጥ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ መርሃ ግብር ተይዞለታል ። የመንገዱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ 19 ሜትር እና በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የመንገድ ዘርፉ የግብርና ፣ የማዕድን ፣ የባህልና ቱሪዝም ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፣ የብሄራዊ ሎጂስቲክስ እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎችን በሚደግፍ መልኩ እንዲተገበር ለማስቻል የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ይህ መንገድ እነዚህን ዘርፎች በሚደግፍ መልኩ ታስቦ የሚገነባ ነው፡፡ https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3751995924841370

+1
ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያ የሆነችውን Ethiopian Remote Sensing Satellite - 01 /ETRSS-1/ የተሰኘች ሳተላይት በዛሬው እለት አስመነጠቀች። በዚሁ አጋጣሚ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እና ይህንን ታሪክ እውን ላደረጉት አካላት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።

ከጎሀፅዮን ደጀን ድረስ የሚዘልቀው መስመር ላይ አዲስ ድልድይ ይገነባል ተብሎ በማህበራዊ ሜዲያዎች ላይ የሚነገረው ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን እውቅና ውጪ መሆኑን እንገልፃለን ።

መልካ ምድራዊ አቀማመጡ አሰቸጋሪ የሆነውን የጎሃፅዮን ደጀን የመንገድ አውታርን ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ነው። ከአዲስ አበባ ባህርዳርና ጎንደር የሚያገናኘው የአባይ በረሃ
መልካ ምድራዊ አቀማመጡ አሰቸጋሪ የሆነውን የጎሃፅዮን ደጀን የመንገድ አውታርን ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ነው። ከአዲስ አበባ ባህርዳርና ጎንደር የሚያገናኘው የአባይ በረሃ መንገድ በሚደርስበት የመሬት መንሸራተት ምክንያት በተደጋጋሚ መስመሩ እክል ይገጥመዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን በሰፍራው ተጠባባቂ የራስ ሀይል ጥግና በማድረግ የትራንስፖርት ፍሰቱ እንዳይሰተጓጎል እያደረገ ቢሆንም ዘላቂ መፍትሄ እንደሚያስፈለገው በጥናት አረጋግጧል። የዚህን የመንገድ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችለም የጃፓን ባለሙያዎች በቦታዉ ተሰማርተው ጥናት ማድርግ ጀምረዋል። በባለስልጣኑ የአለም ገና መንገድ አዉታር እና ደህንነት ዳይሬከተር አቶ ኡመር ሁሴን እንዳሉት የአባይ በረሃ መንገድ በመሬት መንሸራተት ምክንያት በየጊዜዉ ብልሽት ስለሚገጥመዉ ችግሩን ለመፍታት ባለስልጣኑ ከጃፓን ባለሙያዎች ጋር ጥናት እያደረገ ነዉ ብለዋል፡፡ የጥናቱ ውጤት እንደተጠናቀቀም ሊወሰድ የሚችለው ዘላቂ መፍትሄ ለመንግስት ቀርቦ በቀጣይ ውሳኔ እንደሚያገኝም ይጠበቃል።

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሀላፊነታችንን ይብልጥ ለመወጣት እንጥራለን አሉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ሰራተኞች ። ሰራተኞቹ ይህን ያሉት ዛሬ በመንግስት አጠቃላይ አገራዊ ጉዳዮች እና በቀጣይ አስር
+2
ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሀላፊነታችንን ይብልጥ ለመወጣት እንጥራለን አሉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ሰራተኞች ። ሰራተኞቹ ይህን ያሉት ዛሬ በመንግስት አጠቃላይ አገራዊ ጉዳዮች እና በቀጣይ አስር አመት የሚተገበረውን የእቅድ ዝግጅትን በተመለከተ በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ በቀጣይ የሚተገበሩ ሀገራዊ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተካሄዶበታል ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂንር ሀብታሙ ተገኝ መንግሰት አጠቃላይ ለውጡን ተከትሎ በተለያዩ ዘርፎች ማሻሻያዎችን እና ተጨባጭ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አንሰተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ በየደረጃው አስፈላጊውን ግንዛቤ መፍጠርና በተለይም የመንግሰት ሰራተኛውን በሀገራዊ እቅዱ ዙሪያ ግለጽ ውይይትን በማድረግ ለተግባራዊነቱ ይበልጥ እንዲሰራ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ ልትደረሰበት ላቀደችው እድገት የመንገድ ሴክተሩ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት በመሆኑ ይህን በላቀ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ በመስኩ በርካታ አዳዲስ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተከናወኑ ሲሆን ተግባራዊ እንዲሆኑም ይደረጋል ብለዋል። የዋና ዳይሬከተሩ ጽህፍት ቤት ምክትል ዋና ዳሬክተር አቶ የትምጌታ አስራት ባቀረቡት የቀጣይ የአሰር አመት የመንገድ ዘርፍ ልማት ረቂቅ ሰነድ ሀገራችን አለም ከደረሰበት የመንገድ ዘርፍ ልማት አኳያ በቀጣይ ትደርሰበት የሚገባትን አቅጣጫ በግለጽ አጥንቶ የተዘጋጃ ረቂቅ የአሰር አመት እቀድ መሆኑን አንስተዋል። የመንገድ ዘርፍ ልማቱ ይብልጥ ለግብርና ለመአድን ለኢንዱሰትሪና ለቱሪዝም ያለውን አበርክቶት አሟጦ ለመጠቅም በሚያስችል ሳይንሳዊ ግኝቶች ላይ ተመሰርቶ የተዘጋጀ መሆኑንም ባቀረቡት ሰነድ አብራርተዋል። ረቂቅ ሰነዱ በቀጣይ በየደረጃው ሰፊ ምክክር ተደረጎበት ተጨማሪ ግብአቶች ታክለውበት እንደሚጸደቅ ይጠበቃል።

Call For Books Donation
Call For Books Donation

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን “እንደርሳለን- እኔም እጠነቀቃለሁ ” በሚል መሪ ቃል የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ አካሄደ፡፡ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄው የተካሄደው ከአዲስ አበባ መውጫ ባሉ በሶስት መ
+1
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን “እንደርሳለን- እኔም እጠነቀቃለሁ ” በሚል መሪ ቃል የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ አካሄደ፡፡ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄው የተካሄደው ከአዲስ አበባ መውጫ ባሉ በሶስት መስመሮች ሲሆን እነሱም ዓለምገና ፣ ደብርብረሃን እና ቢሸፍቱ ናቸው፡፡ በንቅናቄው መርሃ- ግብር ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱ በሚያስገነባቸው እና በሚያስጠግናቸው የመንገድ ግንባታ ፕጀክቶች ውስጥ ከዲዛይን አንስቶ የፍጥነት መቀነሻ ህዳጎች ፣ የትራፊክ ምልክቶች እና የመንገድ ላይ ቀለሞች ለትራፊክ አደጋ መባባስ ምክንያት እንዳይሆኑ አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ ጥቅም ላይ ማዋል እንዲቻል ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲጠቀሙባቸው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር አለማየው አየለ አሳስበዋል ፡፡ በቀጣይም ከመንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ሊያጋጥሙ በሚችሉ ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ ህብረተሰቡ ለጉዳት እንዳይዳረግ ባለስልጣኑ መሰል ንቅናቄዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘው ገልጸዋል፡፡ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ የባለስልጣኑ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና መላዉ የተቋሙ ሠራተኞች ተገኝተው ለአሽከርካሪዎች እና ለመንገድ ተጠቃሚዎች ግንዛቤ ሰጪ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም “ እንደርሳለን !-እኔም እጠነቀቃለሁ” የሚል መሪ ቃል ያለበት ከ10 ሺ በላይ እስቲከሮችም ተሸከርካሪዎች ላይ እንዲለጠፉም ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ በመንገድ መሠረተ ልማት በኩል የሚያስፈልጉ ማሻሻያዎችን በተጠና የምሕንድስና መፍትሔ በመስጠት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ # በኢሳያስ መብራቱ

EOI Invitation for Consultancy Services

EOI for Consultancy Services of Road Projects

ከ6.1 ቢሊዮንብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂ
+1
ከ6.1 ቢሊዮንብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ፣የፓርላማ አባላት፣ ከአራቱም የመንገድ የፕሮጀክት የመጡ የህዝብ ተወካዮች በተገኙበት 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ከ6.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከአሽናፊ የስራ ተቋራጮች ጋር በኢመባ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተፈርሟል። የተፈረሙት አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሃሙሲት -እስቴ ፣ጩለሴ-ሶያማ (የሎት፦2) ፣የአደሌ- ግራዋ እና የጎዴ - ቀላፎ ( ሎት፦1) ናቸው። መንገዶቹ ከዚህ ቀደም በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበሩ ሲሆን ፣ ካላቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር ታይቶ በአሁኑ ወቅት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነቡ ታቅዶ የውል ስምምነቱ ተፈርሟል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በመረሀ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ከፍተኛ ህዝባዊ ጥያቄ ይጎላባቸው የነበሩትን መንገዶች ወደ ግንባታ ለመሸጋገር በመብቃታቸው ለአገራችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ከፍ ያለ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ!!! የሚል መልዕክትን አስተላልፈዋል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶቹ በታቀደላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል ። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3699459863428310

6.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ዛሬ ከሰዓት ይፈረማል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የ
6.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ዛሬ ከሰዓት ይፈረማል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የተቀመጠውን የመንገድ ዘርፍ ልማት ግቦች በስኬት ለማጠናቀቅ እንዲቻል 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች 6.1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከአሽናፊ የስራ ተቋራጮች ጋር በኢመባ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ ከሰዓት የውል ስምምነት እንደሚፈረም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል። በዛሬው ዕለት የሚፈረሙት አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሃሙሲት - እስቴ፣ጩለሴ-ሶያማ (የሎት፦2)፣የአደሌ- ግራዋ እና ጎዴ - ቀላፎ (ሎት፦1) ናቸው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ በመንገድ መሰረተ ልማት በኩል የሚያስፈልጉ ማሻሻያዎችን በተጠና የምህንድስና መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል መርሃ ግብር ያዘጋጀ ሲሆን ይህንን በሚመለከት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉ። # merry

tender Notice for mid & mini bus T-07-2012

notice for pave. & Brige data collection equiq.T-08-2012

የመንገድና ጥገና ዲስትሪክቶችንና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ተመለሱ። የመንገድና ጥገና ዲስትሪክቶችንና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዳግም እንዲመለሱ መንግስት ወሰነ
+3
የመንገድና ጥገና ዲስትሪክቶችንና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ተመለሱ። የመንገድና ጥገና ዲስትሪክቶችንና ሴክሽኖች ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዳግም እንዲመለሱ መንግስት ወሰነ ። በዚህም መሰረት አስሩ የመንገድና ጥገና ዲስትሪክቶች እና ሴክሽኖች በአደረጃጀትም ሆነ በተግበር፤ የሚገለገሉባቸውን የተለያዩ ሀብቶች የሰው ሀብት ቢሮዎች ፋይናስ ተሽከርካሪዎችና መሳሪያዎች ፣ ሰነዶች፣ የተለያዩ መረጃዎች፣ በሙሉ ባሉበት ሁኔታ ወደ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን እንዲመለሱ ነው የተወሰነው። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ መደበኛ የመንገድ ጥገና እንክብካቤ ሥራ በባህሪው ሰፊ የሰው ሃይል፣ የተለያዩ መሳሪያዎችን እና ከምንም በላይ ለመንገዱ ቅርብ ሆኖ መገኘትን የሚጠይቅ በመሆኑ በተወሰነ የግንባታ ጣልቃ ገብነት የመንገድ ሀብትን ከብልሽት አስቀደሞ ፈጥኖ ለመከላከል ያላቀ አበርክቶት አለው ብለዋል። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3695106053863691

Notice of Invitation for legal advisory Services

AMENDMENT NOTICE OF INVITATION FOR BIDS