ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 313 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 759 في فئة النقل والمرتبة 2 546 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 313 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 90، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 40.85‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.40‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 439 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 050 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 319
المشتركون
+824 ساعات
+217 أيام
+9030 أيام
أرشيف المشاركات
የደምበጫ - ሰቀላ እና ቢቡኝ አገናኝ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ)፦ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኘውን 69.8 ኪሎ ሜትር ደምበጫ-ፈረስ ቤት-አዴት ኮንትራት1፡ ደምበጫ-ሰቀላ (59 ኪሎ ሜትር) እና ቢቡኝ አገናኝ መንገድ (10.8 ኪሎ ሜትር) የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን እየተሰራ ነው፡፡ 59 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የደምበጫ-ሰቀላ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ደምበጫ ከተማን መነሻ በማድረግ ፈረስ ቤት ከተማን አቋርጦ ሰቀላ ቀበሌን የሚያገናኝ ሲሆን በተጨማሪም ከፕሮጀክቱ 37 ኪሎ ሜትር ላይ በመገንጠል ከቢቡኝ ወረዳ ጋር የሚያገናኝ 10.8 ኪሎ ሜትር መንገድ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ የአፈር ጠረጋ ፤ የቆረጣ እና የቁፋሮ ፤ የሰብ ቤዝ ፤ የስትራክቸር ፤ የማፋሰሻና ሌሎች ስራዎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ እንዲሁም በአሁኑ ጊዜ የቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ንጣፍ ስራ ተጀምሯል፡፡ ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,790,005,720 (አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ዘጠና ሚሊዮን አምስት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግሰት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የተባለ መንግስታዊ የልማት ድርጅት ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ K & J ፕሮጀክትስ ኃ/የተ/የግ/ማ እና ክሎቨር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማ በጣምራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ። በአካባቢው የተስተዋለው የፀጥታ ችግር ፣ የግንባታ ግብዓት እጥረት ፤ የወሰን ማስከበር ችግሮች ፤ የስራ ተቋራጭ የአቅም ውስንነት እና ያልተጠበቀ የአየር ንብረት በግንባታ ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ ቢያሳድርም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የመንገድ ግንባታ ሂደቱን ለማፋጠን እየተሰራ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ሕብረተሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ ከመሆኑም ባሻገር ከዚህ ቀደም ከደምበጫ እስከ ሰቀላ በተሽከርካሪ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን ከ3 ሰዓት በላይ የጉዞ ጊዜ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከ 1: 30 ባልበለጠ ጊዜ ለመድረስ ያስችላል። ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ ህብረተሰቡ ተሽከርካሪዎችን ተጠቅሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትንም ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚህም ባሻገር አርሶ አደሮች በአካባቢው በስፋት የሚገኙ የግብርና ምርቶች እና የቁም እንስሳትን ትራንስፖርትን ተጠቅሞ በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በመስመሩ ተራርቀው ለነበሩ የአካባቢው ህብረተሰቦች በቅርበት የመገናኘት እድልንም የሚፈጥር ሲሆን በመስመሩ ያሉ ትንንሽ መንደሮች ወደ ከተማ እንዲያድጉ ይበልጥ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም የጤና ፣ የትራንስፖርት እና የሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ተደራሽነትን ያስፋፋል፡፡ በአጠቃላይ የትራንስፖርት ጊዜን በማሳጠር የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ እንደሚያረጋግጥ ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአጋርፋ - አጋርፋ   ኮሌጅ  - አምቤንቱ  አስፋልት ኮንክሪት መንገድ  የግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ተደረገ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- በኦሮሚያ   ክልል  ባሌ   ዞን  የአጋርፋ  ወረዳ  እና   አምቤንቱ  ቀበሌ    የሚያገናኘው   እና 15  ኪሎ  ሜትር  ርዝማኔ  ያለው  የአጋርፋ  - አጋርፋ  ኮሌጅ -አምቤንቱ   የአስፋልት   ኮንክሪት   የመንገድ  ሥራ  ፕሮጀክት  ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ። ለመንገዱ  ግንባታ 1,052,976,513 (አንድ  ቢሊዮን  ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን  ዘጠኝ  መቶ  ሰባ ስድስት  ሺህ  አምስት  መቶ  አስራ  ሶሰት  ብር) በኢትዮጵያ መንግስት ፈሰስ ተደርጎበታል።  ግንባታውን   ያካሄደው   የስራ  ተቋራጭ  ቻይና  ኮሙኒኬሽን  ኮንስትራክሽን  ካምፓኒ  ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር  ስራውን   ደግሞ   ሆንግ   ኣይኬ  ከልደት  አማካሪ  ጋር   በጣምራ  በመሆን  አከናውነውታል። የመንገዱ  መገንባት   አጋርፋ   ከተማን ፣ አጋርፋ  ኮሌጅን  እና  አምቤንቱ  ከተማን  በቅርበት በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ያገናኛል። ከዚህም   ባሻገር   በአካባቢው   የሚገኙ  እንደ በርበሬ   እና  ገብስ  ያሉ  የግብርና  ውጤቶችን ወደ ማዕከላዊ  ገበያ  አንዲቀርቡ በማድረግ አምራችና ሸማቾችን ያገናኛል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ  የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ  በከተማ   21.50  ሜትር ፣በቀበሌ  12  ሜትር  እንዲሁም በገጠር 10  ሜትር  የሚሆን  ስፋት  አለዉ። መንገዱ ከፍተኛ መዋለ-ንዋይ የፈሰሰበት የሀገር ሀብት በመሆኑ ኅብረተሰቡ ተገቢውን ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርግ ኢመአ ያሳስባል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቦኖሻ -አጫሞ ከተማ የመንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ወደ ማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋገረ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- በማዕከላዊ የኢትዮጵያ ክልል የሚገኘው የሃድያ፣ የሀላባ እና የስልጤ ዞንን የሚያገናኘው የቦኖሻ - አጫሞ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 68.6 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደርሷል ። 23.3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጅማሮውን ቦኖሻ ከተማ ላይ ያደርግና እስከ አጫሞ ቀበሌ ድረስ የሚዘልቅ ይሆናል። የአፈር ቆረጣና ሙሌት ስራ 96.51% ፣ የ 15.16 ኪ.ሜ የፍካ ስራ (የግንብ ዲች) እና 48 የፓይፕ ካልቨርት ስራ በአጠቃላይ 81.32% የዉሃ ማፍሰሻ ፍካ ስራ፣ 6 ቦክ ካልሰርት እና 1 ድልድይ ፣ የ16 ኪ.ሜ የሚሸፍን የሰብ ቤዝ ስራ፣3 ኪ.ሜ የሚሆን የቤዝ ኮርስ እና የ2.0 ከ.ሜ የአስፍልት ንጣፍ ፣19% የእግረኛ መንገድ ፤ 34% የዲች ኪዳን ማስቀመጥ እና 12 ኪ.ሜ ካርሸ ስቶን ስራ እና በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 682,155,064.23 (ስድስት መቶ ሚሊየን አንድ መቶ ሃምሳ አምስት ሺህ ስልሳ አራት ብር ከሃያሶስት ሳንቲም) ብር የሚሸፍነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ብርሃን የኮንስትራክሽን እና ዲዛይን አማካሪ ድርጅት እያከናወነው ይገኛል። ከተማዋ በፈጣን ዕድገት ላይ የምትገኝ በመሆኗ የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው ። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከሆሳና ወደ ሀላባ እንዲሁም ሃዋሳ ኣና አካባቢው ወዳሉ ሌሎች ከተሞች የሚደረገውን ጉዞ ያቀላጥፋል፡፡ በአካባቢው ድንች ፣ ቦቆሎ ፣ በርበሬ ፣ ቦሎቄ እና ሌሎች የግብርና ምርቶች በሰፊው የሚመረቱ በመሆኑ የመንገድ ግንባታው መጠናቀቅ እነዚህን የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ አርሶ አደሩ ከምርቱ እንዲጠቀም ያስችለዋል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ሻሼጎ ወረዳ (ቦኖሻ ከተማ እና ዶሻ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት)፣አና ሌሞ ወረዳ (አጫሞ ቀበሌ)፣ዉልባረግ ወረዳን በአስፋልት ኮንክሪት የሚያገናኝ ይሆናል። ከዚህ ቀደም በተሽከርካሪ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የሁለት ሰዓት የጉዞ ጊዜ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወደ ሰላሳ ደቂቃ ያሳጥረዋል ይህም የአንድ ሰዓት ከሰላሳ ጊዜን ይቀንሳል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በወረዳ በከተማ 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ዒድ ሙባረክ!!
ዒድ ሙባረክ!!

ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት ተካሄድ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- ለ20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ስነ-ስርዓት በትላንትናው ምሽት በኢንተር-ሌግዤሪ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ ሀገራችን በቅርቡ ያካሄደችው 20ኛው የአለም ሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ በእውቀት፣ በጉልበትና በገንዘብ ድጋፍ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ሽልማቱ ለአጋሮች፣ ለስፖንሰሮች፣ ለብሔራዊ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት፣ ለሚዲያ ሙያተኞችና ተቋማት እንዲሁም ለጽሑፍ አቅራቢዎች የተበረከተ ሲሆን በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፤ ጉባኤው ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን ግዙፍ የልማት ሥራዎችን አፍሪካዊያንና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲመለከት እድል የሰጠ መሆኑን አሳውቀው፣ ለኮንፈረንሱ ስኬት በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጉልበታቸው ድጋፍ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታና የብሔራዊ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ የትምጌታ አሥራት ከዝግጅቱ ጀማሮ አንስቶ እስከ ፍጻሜው ድረስ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋና አቅርበው፣ መድረኩ ከተባበርንና ከተጋገዝን የማይቻል እንደሌለ ያየንበት ክስተት ነበር ብለዋል፡፡ አያይዘውም ያለንን አቅም ለሀገራዊ ልማትና ብልጽግና በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን መርህ መሰረት ተደምረን አስተዋጽኦ ማበርከታችንን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን፤ ጉባኤው ለመሰረት ልማት ዘርፉ አስፈላጊ የምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው መሆኑም አስታውሰው፣ የተገኙ ተሞክሮዎችና ልምምድ ልውውጦች ለሀገራችን መንገድ ልማት እጅግ ጠቃሚ መሆናቸው ገልጸዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads