ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 542 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 329 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 179 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 542 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 31، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.36‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.21‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 097 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 520 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 542
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+3130 أيام
أرشيف المشاركات
አዳማ 2ኛ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ……///……. የአዳማ 2ኛ ባለ 230/132/15 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፕሮጀክቱ የኤሌክትሪካል መሐንዲስ አስታወቁ፡፡ መሐንዲሱ አቶ አንዱአለም መላኩ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በታህሳስ 2012 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ 99 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ የማጠናቀቂያ ስራ ፣ ከጣቢያው መግቢያ ወደ ወጭ አገናኝ መንገድ ስራ እና ማከፋፈያ ጣቢያውን ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል (LDC) ጋር ለማገናኘት የሚያስችል ስራ ብቻ መቅረቱን መሐንዲሱ ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ 350 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ሲሆን ሁለት ባለ 125 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች ተገጥመውለታል፡፡ ለወጪና ገቢ መስመር የሚያገለግሉ (LILO) አንድ ባለ 230 እና አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር እንዲሁም እያንዳንዳቸው 10 ሜጋ ቮልት አምፔር ድረስ የመሸከም አቅም ያላቸው ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች (feeders) እንዳሉት አቶ አንዱአለም ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ እንደተጠናቀቀ ሁሉም ወጪ መስመሮች ኃይል መስጠት እንዲጀምሩ ለማድረግ በአገልግሎቱ በኩል የሚከናወኑ የማሰራጫ መስመሮች ዝግጁ እንዲደረጉ ለአዳማ ዲስትሪክት እና ለሪጅኑ የማሳወቅ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በታህሳስ 2014 ዓ.ም በ132 ኪሎ ቮልት መስመር ኃይል ማግኘቱን ያስታወሱት አቶ አንዱአለም በአሁኑ ጊዜም ከአስሩ ወጪ መስመሮች በአንዱ ብቻ ለህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በቀጣይ ለሚከናወን የማስፋፊያ ስራ የሚሆን 2 ባለ 132 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመር፣ ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚያገለግል 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን መዘርጋት የሚያስችል ሥራ በጣቢያው ላይ ዝግጁ መደረጉን አንስተዋል፡፡ ይሁን እንጅ ከአንዱ መስመር ውጭ ሌሎች ወጪ የማሰራጫ መስመሮች ዝግጁ ባለማድረጋቸው አገልግሎት መስጠት አለመጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጂነሪንግ ቢሮ የፕሮጀክቱ የሳይት አስተባባሪ ልዕልት አምባዬ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ የግንባታ ስራ ላይ አጋጥመው የነበሩ በውይይትና በምክክር መፍታት መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በስራ ተቋራጩ በኩል ስራዎችን በአፋጣኝ ያለማከናወንና ትዕዛዞችን ተቀብሎ ያለመተግበር ችግር ይስተዋል እንደነበር የጠቆሙት የሳይት አስተባባሪዋ ፕሮጀክቱን በወቅቱ ለማጠናቀቅ ማሻሻል ያለበት ጉዳይ እየተነገረውና ስራው በምን መልኩ መካሄድ እንዳለበት አቅጣጫ እየተሰጠ ሲከናወን ነበር፡፡ የሳይቱ የካሳ ክፍያ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ አበበ አለሙ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሚከናወንበት አካባቢ ላሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የካሳ ክፍያዎችን በመፈጸም በወቅቱ ወደ ግንባታ ስራ ለመግባት በከተማ አስተዳደሩ በኩል ወጥ የሆነ አሰራር አለመኖሩና መከናወን ያለባቸው ስራዎች በወቅቱ ባለመፈጸማቸው በተቋሙ ስራ ላይ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ በዲዛይኑ መሰረት ስራውን ለማከናወን ወደ ስራ ሲገባ ተቋሙ ለግንባታ ከሚፈልገው የመሬት ልኬት በላይ የካሳ ክፍያ እንዲከፍልበት ጫና የማድረግ ሁኔታ መስተዋሉ እንዲታረምም አቶ አበበ አሳስበዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ የግንባታ ስራ 127 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እና 13 ነጥብ 8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ በጀት እንደተያዘለት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ የተገነባ ሲሆን በምዕራፍ አንድ በአዳማ ከተማ አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና በነባሩ የአዳማ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የካፓሲተር ባንክ ማስፋፊያ የዲዛይን፣ የአቅርቦት፣ የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎችን ተከናውነዋል፡፡ በምዕራፍ ሁለት ደግሞ 1 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከነባሩ የቆቃ-ሁርሶ ወደ አዳማ ሁለት እና 3 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከነባሩ የአዳማ-መተሃራ ወደ አዳማ ሁለት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር መዘርጋትን ያጠቃልላል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በዕቅዱ መሰረት ኃይል እያመነጨ ነው ……////….. የቆቃ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በዓመቱ የሚጠበቅበትን ኃይል በዕቅዱ መሰረት እያመነጨ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ተወካይ ሥራ አስኪያጅ እና የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሰሎሞን አጅጉ እንደተናገሩት ኃይል ማመንጫው ያለምንም የቴክኒክ ችግር በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የያዘውን 128 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማሳካት እየሰራ ይገኛል፡፡ የዛሬ 62 ዓመት 110 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማመንጨት ወደ ሥራ የገባው የቆቃ ኃይል ማመንጫ በተደረገለት የቴክኒክ ድጋፍ በአሁኑ ወቅት በዓመት ከ128 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በላይ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ላይ መድረሱን ተወካዩ ጠቁመዋል፡፡ ጣቢያው በ2014 በጀት ዓመት ኃይል ለማመንጨት ከያዘው ዕቅድ ውስጥ እስከ አሁን 118 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ማምረቱን ያስታወቁት አቶ ሰለሞን የቀረውን 10 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በቀጣዩ አንድ ወር ለማምረት የሚያስችለው የውሃ መጠን በግድቡ ውስጥ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ ግድቡ ዓመቱን ሙሉ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችለውን ውሃ ከሰኔ እስከ መስከረም ባሉት የዝናብ ወራቶች ይይዛል፡፡ ከግድቡ ለመጠጥ፤ ለመስኖና እና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚለቀቀውን የዉሃ መጠን የሚቆጣጠረው የታችኛው አዋሽ ተፋሰስ ባለስልጠን ሲሆን በአሁኑ ወቅት ባለስልጣን መ/ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ውሃው ኃይል እያመነጨ ከግድቡ እየወጣ ስለመሆኑ አቶ ሰሎሞን አረጋግጠዋል፡፡ ይሁንና ሰሞኑን የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የማምረት አቅም ከ10 MW ያልበለጠ ነው በሚል በተለያዩ ሚዲያዎች የተዘገበው ዜና ስህተት የሆነና የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽን አሰራሮችን ካለመረዳት የመነጨ በመሆኑ እንዲታረም አቶ ሰሎሞን አሳስበዋል፡፡ ከቆቃ ግድብ በሚለቀቀው ውሃ በታችኛው የአዋሽ ተፋሰስ ከ60 -70 ሄክታር መሬት በመስኖ የሚለማ ሲሆን ግድቡ ከሐምሌ እስከ መስከረም መጨረሻ ያጠራቀመውን ውሃ ዓመቱን ሙሉ ይጠቀማል፡፡ ይሁንና ግንቦት ወር ቆቃ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛዎቹ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የሚይዙት ውሃ እንደሚቀንስ ከግድቦች በየዓመቱ የሚሰበሰቡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+1

የሐረርና የጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸውን ችግር እንዲፈቱ የተተከሉት ፓወር ትራንስፎርመሮች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ ……..////……… በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ሲከናወን የቆየው የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ እና የፍተሻ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለሙከራ ዝግጁ መሆኑን በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የምስራቅ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት በሐረር እና አካባቢው ያለውን የኃይል እጥረት ሙሉ በሙሉ ይቀርፋል የተባለለት የአቅም ማሻሻል ሥራ በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ የተጀመረው በጥር ወር መጨረሻ ላይ ነበር፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራ እና ፍተሻው በመጠናቀቁ ኃይል መስጠት የሚችልበት የሙከራ ሥራ የሚሰራበት ደረጃ ላይ መድረሱን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ አዲሱ የፓወር ትራንስፎርመር መሉ በሙሉ ወደ ስራ ሲገባ በሐረር፣ በአወዳይ፡ በኮምቦልቻ ከተሞችና የገጠር መንደሮች በማከፋፈያ ጣቢያው በሚስተዋለው ከአቅም በላይ ጭነት ምክንያት ያጋጥም የነበረውን የኃይል እጥረት ሙሉ በሙሉ ይቀርፋል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እስከ ሐሮማያ ከተማ እንደ አስፈላጊነቱ መመገብ የሚችል አቅም የተፈጠረለት ሲሆን አዲሱ ትራንስፎርመር ከነባሩ ትራንስፎርመር አቅም ጋር ሲነጻጸር በ5 እጥፍ የሚበልጥ አቅም እንዳለው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በሐረር ከተማ ውስጥ በ66 ኪሎ ቮልት አቅም እያገለገሉ የሚገኙትን የሐረር ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለማሳረፍ እንዲሁም የጥገናና ማሻሻያ ሥራ በሚከናወንበት ጊዜ በተጠባባቂነት ሊያገለግል እንደሚችልም ጠቁመዋል፡፡ የማሻሻያ ሥራው በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙ መሀንዲሶችና ቴክኒሻኖች የተከናወነ ሲሆን የትራንስፎርመሩን ግዢ ሳይጨምር እስከ ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊየን ብር በሚያወጣ የገንዘብ ወጪ መከናወኑን አቶ ጋሻው ተናግረዋል። ለስራው አስፈላጊ የሆኑትን ማሽነሪና ክሬን በማቅረብ የሐረሪ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ ትብብር በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊው አቶ ቴዎድሮስ ታመነ እንደገለጹት ሁሉም ባለሙያዎች ሥራው ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በበዓል ቀናት ጭምር በስራው ላይ ቀን ከሌሊት በቃላት ሊገለጽ በማይችል የሥራ ፍቅር ሲረባረቡ ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ በጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያም ተመሳሳይ የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን የሥራው አፈፃፀምም ከሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር ተቀራራቢ በሆነ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የሪጅኑ የሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከድር አብደላ ገልጸዋል። እንደ አቶ ከድር ገለፃ ሪጅኑ ከሑርሶ እስከ ሐረር ድረስ ባለው የ132 ኪ.ቮ. የማስተላለፊያ መስመር ላይ አስራ ሁለት የ132ኪ.ቮ. 400/800/1 አምፐር ከረንት ትራንስፎርመሮችን በመትከል የምስራቅ ኢትዮጵያን የግሪድ ሲስተም የሚያስተካክል ሥራ ሰርቷል፡፡ በሐረርና ጅግጅጋ የተተከሉትን ፓወር ትራንስፎርመሮች በተመሳሳይ ጊዜ ሞክሮ በቅርቡ ስራ ለማስጀመር ታቅዷል፡፡ በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ በተከናወነው የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራ ብቻ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

ሶስተኛው የህብረት ስምምነት ተፈረመ ..........////......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በተቋሙ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር መካከል ሶስተኛው የህብረት ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈርሟል፡፡ በህብረት ስምምነቱ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሰራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ከፍሌ ናቸው፡፡ በፊርማ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የተቋሙንና የሠራተኛውን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ሥራዎች እንዲሰሩ ለማድረግ የህብረት ስምምነቱ ትልቅ ሚና ይጫወታል። በተጠናቀቀው የህብረት ስምምነት ላይ የታዩ ክፍተቶችን በማረም የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ ጊዜ ተወስዶ ሰነዱ መዘጋጀቱን አቶ አሸብር ጠቁመዋል። በቀጣይም የሚሻሻሉ ነገሮች ካሉ በድርድር ኮሚቴው ታይተው መፍትሄ እየተሰጣቸው እንደሚሄድ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ከፍሌ በበኩላቸው የህብረት ስምምነቱ የተቋሙን እና የሠራተኛውን መብት እና ጥቅም ያስጠበቀ እንዲሆን በተለየ ትኩረት መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚያገለግለውን የህብረት ስምምነት የድርድር ኮሚቴው በቅን ልቦና እና ለሌሎች ተቋማት ሞዴል ሊሆን በሚችል መልኩ ማዘጋጀቱንም ሊቀመንበሩ ጠቁመዋል። የተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ከተቋሙ ሜኔጅመንት እና ከመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ተውጣጥቶ የተቋቋመው የድርድር ኮሚቴ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ግብአቶችን በማሰባሰብ ሰነዱን ማዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ሰነዱ ለማኔጅመንት ቀርቦ አስተያየት ከተሰጠበት በኋላ ለፊርማ መዘጋጀቱን አቶ አታላይ ጠቁመዋል፡፡ በፊርማ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ. ም በአዲስ ዘመን ላይ የወጣ የሥራ ማስታወቂያ ነው፣ መስፈርቱን ካሟሉ ይሳተፉበት፣ ለወዳጅ ዘመድዎም ያጋሩት። መልካም ዕድል!

photo content
+1

የስራ ዘመናቸውን ላጠናቀቁ የቦርድ አመራሮች ሽኝት ተካሄደ። .........//////........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ህብረት ስራ ማህበርን ለ6 ዓመታት የመሩት የሥራ አመራር ቦርድ አባላት በክብር ተሸኙ። ሜክሲኮ በሚገኘው የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፓርት ክበብ አዳራሽ በተካሄደው የሽኝት መርሐ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የቦርድ ሰብሳቢው አቶ መልካሙ አበበ እንደተናገሩት የኢትዮ ኤሌክትሪክ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ህብረት ስራ ማህበር በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ዘርፍ የብዙ ሠራተኞችን ህይወት የቀየረ አንጋፋ ተቋም ነው። ማህበሩ ላለፉት 40 ዓመታት ለአባላቶቹ ያልተቋረጠ አገልግሎት የሰጠና በሀገሪቱ ከሚገኙ ጠንካራ የገንዘብ ህብረት ስራ ማህበራት መካከል አንዱ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪቢዩሽን ሲስተም ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብዙወርቅ ደምሴ ለተሸኙ የቦርድ አባላት የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ለማህበሩ ሁለንተናዊ ስኬት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተሰናባች የቦርድ አባላትን ያመሰገኑት አቶ ብዙ ወርቅ አዲስ የተመረጡ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል። በ1974 ዓ.ም የተቋቋመው ይህ ማህበር ከ12 ሺህ በላይ አባላት አቅፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የማህበሩ ቦርድ የቀድሞ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዮሐንስ ለገሰ ለተደረገላቸው አሸኛኘት አመስግነው አዲሶቹ የቦርድ አመራሮች ጠንካራውን በማስቀጠል ክፍተቶችን ደግሞ በማረም አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አደራ ብለዋል። ከሽኝት መርሃ ግብሩ በተጓዳኝ ማህበሩን ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት እንዲመሩ ለተመረጡ አዲስ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የመልካም ምኞት መርሀ ግብር ተከናውኗል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አመራሮች በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 07 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+6

የባቡር ኃይል አቅርቦት ቴክኒካዊ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ ........//////...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮ- ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር በባቡር ኃይል አቅርቦት ዙሪያ የሚታዩ ቴክኒካዊ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮ- ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አብዲ ዘነበ(ዶ/ር) ናቸው። ስምምነቱ ለሁለቱ ተቋማት የጋራ ጥቅም ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውና በሌሎች የትብብር እና የድጋፍ መስኮች በጋራ ለመስራት መሰረት እንደሚጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚዎቹ ተናግረዋል። በስምምነቱ መሰረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከኃይል አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ ችግሮችን በጋራ ለመቅረፍ የቴክኒክ ኮሚቴ ይዋቀራል። ያልተቀናጀና በባቡር የኃይል አቅርቦት ጣቢያ ወይም ትራክሽን ጣቢያዎች የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ለማስቀረት የሚያስችሉ ሥራዎች እንዲሰሩና የተቋማቱን የግንኙነት መስመር የተሳለጠ ለማድረግ በምድር ባቡር በኩል ባሉት ጣቢያዎች 24 ሰዓት የሚሰራ ባለሙያ ለመመደብ ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ ደግሞ በባለሙያዎች ተጠንቶ የሚቀርበውን መፍትሔ በጋራ ገምግመው ተግባራዊ ለማድረግ እንዲሁም የኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲከናወን ተግባብተዋል። የሁለቱ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎችና የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የለቡ የባቡር ጣቢያን፣ የመቆጣጠሪያ እና የኃይል አቅርቦት ክፍል የጎበኙ ሲሆን በባለሙያዎች ገለፃ ተደርጎላቸዋል። የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር ነዳጅም ሆነ ሌሎች ከባቢ አየር የሚበክሉ የኃይል ምንጮችን የማይጠቀም ሲሆን የወጪና ገቢ ምርቶችን በማጓጓዝ የሀገርን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚደግፍ ይታመናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 06 ቀን 2014 ዓ.ም.

photo content
+5

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች Florida University Southeast ለአንድ ወር የሚቆይ የፕሮጀክት ማኔጅመንት የኦንላይን ስልጠና አዘጋጅቷል። ስለሆነ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥልጠናውን መሳተፍ የሚፈልግ ሁሉም ሠራተኛ በዚህ ሊንክ እንዲመዘገብ እየጠቆምን ዕድሉ የመጣው ለአንድ ጊዜ ብቻ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ እናሳስባለን። https://myfuse.education/webinars/fuse-sptasfa-edsi-foundations-of-project-management-online-training-registration-page/?wspage=register

ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረሙ ........../////......... ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችላት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመች። የመግባቢያ ሥምምነቱን በኢትዮጵያ በኩል የፈረሙት የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ዴኤታ ሲሆኑ በደቡብ ሱዳን በኩል የሀገሪቱ የውሃና ግድብ ሚኒስትር ዴኤታ ናቸው። በሥምምነቱ መሰረት የጥናት ሥራዎች በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲጠናቀቁ የታሰበ ሲሆን ግንባታውንም ከጥናቱ በኋላ ባሉት በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት በማጠናቀቅ የኃይል ሽያጭ ስምምነቱ ተግባራዊ ይሆናል። ሀገራቱ የተፈራረሙት የኃይል ሽያጭ ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ 357 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ከጋምቤላ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ደቡብ ሱዳን ማላካል ግዛት መስመር መዘርጋትን ያካትታል። በረጅም ጊዜ ደግሞ እስከ 700 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለ 400 ወይም 500 ኪሎ ቮልት መስመር ከቴፒ ወደ ቦር ጁባ መዘትጋትን ታሳቢ አድርጓል። ሀገራቱ በቀጣይ ለሚሰሯቸው ሥራዎች ጥምር ቴክኒካል ኮሚቴ አዋቅረው ወደስራ እንደሚገቡ በስምምነቱ ላይ ተጠቅሷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 27 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

የደቡብ ሱዳን የልዑካን ቡድን ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከልን ጎበኘ .........////........ ትናንት ምሽት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ የገባው የደቡብ ሱዳን የልዑካን ቡድን ዛሬ ረፋድ ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከልን እና የኮተቤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝቷል። በደቡብ ሱዳን የኢነርጂና ግድብ ሚኒስትር ፒተር ማርሴሎ የተመራው የልዑካን ቡድን የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከሉን ከጎበኘ በኋላ ሚኒስትሩ እንደገለፁት ኤሌክትሪክ የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት በመሆኑ የልዑካን ቡድኑ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ኃይል በምትገዛበት ሁኔታ ላይ ከስምምነት ላይ ለመድረስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል። ስምምነቱ ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እምነት አለኝ ያሉት ሚኒስትሩ ሀገራቸው ለኃይል ሽያጭ ስምምነቱና ለመሰረተ ልማት ዝርጋታው ተገቢ ዝግጅት አድርጋለች ብለዋል። ሁለቱ ሀገራቱ ጠንካራ ትስስር እንዳላቸው የጠቀሱት በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል መሃዲ በበኩላቸው የሀገራቱን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማስፋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ሀገራቱን በኢነርጂ በማስተሳሰር የህዝቦቻቸውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። እንደአምባሳደሩ ገለፃ ሀገራቱ በጋራ ለመስራት የሚኖራቸው ዕድል ሰፊ በመሆኑ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በቁርጠኛነት ክትትል እያደረጉ ነው። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱአለም ሲዓ እንዳስታወቁት ደቡብ ሱዳን በአንድ መቶ ሜጋ ዋት ጀምሮ በየደረጃው እስከ አራት መቶ ሜጋ ዋት የሚደርስ የኃይል ፍላጎት አላት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 27 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

የደቡብ ሱዳን የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ .........////........ በደቡብ ሱዳን የኢነርጂና ግድብ ሚኒስትር ፒተር ማርሴሎ ናስር የተመራ የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል። ሰባት አባላትን ያካተተው የልዑካን ቡድኑ አዲስ አበባ ሲገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል መሃዲ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል። ልዑኩ በኢትዮጵያ ከሚያዝያ 27 - 30 ቀን 2014 ዓ/ም በሚቆይባቸው አራት ቀናትም በሁለቱ ሀገራት በተጠናው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ረቂቅ ስምምነት ላይ በመምከር የመግባቢያ ስምምነት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል። ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ የታዳሽ ኃይል ምርት በማልማት በጋራ ለመጠቀም እየሰራች ሲሆን ልዑኩ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደትን እንደሚጎበኝ ከወጣው መርሃግብር ለማወቅ ተችሏል። ኢትዮጵያ ለሱዳንና ጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል እየሸጠች ሲሆን በቅርቡ ወደ ኬንያ ኤሌክትሪክ ለመሸጥ የሚያስችሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። በኬንያ በኩል ደግሞ እየተገባደደ ይገኛል። በቀጣይም ለታንዛንያ፣ለሩንዳና ብሩንዲ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየሰራች ሲሆን የኢትዮ-ደቡብ ሱዳን ጉብኝትም የዚህ አንድ አካል ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 26 ቀን 2014 ዓ/ም