ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 542 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 329 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 179 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 542 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 31، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.36‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.21‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 097 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 520 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 542
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+3130 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+3

የኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎች የቴክኒክ የሰው ኃይል ፍላጎታቸውን በመከለስ ላይ ናቸው …….////…….. የኃይል ማመንጫ፣ ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎች ያሉባቸውን የቴክኒክ ባለሙያዎች ክፍተት በዕቅድ ለማሟላት የሰው ኃይል ፍላጎታቸውን በመከለስ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም የኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎችን የሰው ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተሰራው ሥራ የሥራ ክፍሎቹን የሥራ ባህርይና ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነበር፡፡ ጉድለቱን ለማስተካከልና የሥራ ክፍሎቹን ዝርዝር ሥራ በባለሙያ በማስተንተን የኦፕሬሽን ክንውናቸውን ያገናዘበ የሰው ኃይል ፍላጎት እየተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ በተቋሙ ያለውን የቴክኒክ ባለሙያዎችን ክፍተት በቀጣይ በዕቅድ ማሟላት መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑ ክለሳውን ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦፕሬሽን ዘርፎች በኩል የተሻለ የስራ አፈፃፀም እየታየ ቢሆንም በቀጣይ የተቋሙን የኦፕሬሽንና ጥገና ስራ በራስ አቅምና ውጤታማ በሆነ አግባብ ለማከናወን በዘርፉ ልምድ ያለውና የቴክኒክ ባለሙያ ምጣኔን አሁን ካለበት የተሻለ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ አዳዲስ የተመረቁ ጀማሪ መሀንዲሶችን በቅጥር ወደ ተቋሙ እንዲገቡና በስራ ላይ ስልጠና እየወሰዱ ልምዳቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ የኦፕሬሽን ዘርፎች አሁን ያለውን የሰው ኃይል ፍላጎት መፈተሽና የባለሙያ ክፍተቶቻቸውን መለየት ቅድሚያ ሊሰጡት የሚገባ ሥራ ነው ያሉት አቶ አታላይ የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣያቢያዎች እንዲሁም የሪጅን ጽ/ቤቶች ያላቸውን የሥራ ባህሪይ፣ አካባቢያዊ ሁኔታና የሥራ ጫናን ግምት ውስጥ በማስገባት የሰው ኃይል ፍላጎታቸውን እንዲከልሱ አቅጣጫ ተቀምጧል ብለዋል፡፡ በተያያዘ ዜና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚታየውን የሰው ኃይል ፍልሰት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታትና አማራጭ መፍትሔዎችን ለማስቀመጥ የሚረዱ ጥናቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ በዘርፉ ልምድና ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች ከገበያ ለማግኘት አስቸጋሪ ቢሆንም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በውስጥ ዕድገትና ዝውውር የሚፈጠረውን የሰው ኃይል ክፍተት ለመቅረፍ ጊዜያዊ መፍትሔዎች እየተሰጡ መሆናቸውን ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ ከ2013 በጀት ዓመት ጀምሮ በተቋሙ ከ350 በላይ አዲስ ጀማሪ መሀንዲሶች ቅጥር መፈፀሙን የጠቀሱት ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም የጀማሪ መሀንዲስ ቅጥር ለመፈፀም ሰነድ የማጣራትና የምልመላ ሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ የቴክኒክ ባለሙያ በቅጥር ከማሟላት ባሻገር በየጣቢያው በስራ ላይ ያሉ ሠራተኞችንና የስራ መሪዎችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 25 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 443ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: ኢድ ሙባረክ!

የተቋሙ አመራሮች ለተቋም ግንባታና ለሠራተኞች ጥያቄዎች ትኩረት እንዲሰጡ ተጠየቀ ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ አመራር ለተቋሙ ግንባታ እና ሠራተኞች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ትኩረት እንዲሰጡ የተቋሙ ሠራተኞች ጠየቁ፡፡ በተቋሙ ስር የሚገኙት የአዲስ አበባና ማዕከላዊ ሪጅን፣ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ፣ የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ቢሮ እና የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በተቋማዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ትናንት ውይይት አካሂደዋል፡፡ ሠራተኞቹ ባካሔዱት ውይይት ከደመወዝና ጥቅማ ጥቅም፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከአመራር ምደባ፣ ከግንባታ ዕቃዎችና ማሽነሪዎች አቅርቦት፣ ከተቋም መዋቅራዊ አደረጃጀት፣ ከኑሮ ውድነት፣ ከህግ የበላይነት ማረጋገጥ፣ ከካሳ ክፍያና ከኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ ሠራተኞቹ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት የተቋሙ አመራሮች ለተቋም ግንባታና ሠራተኞች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ትኩረት እንዲሰጡና የሠራተኛውን ችግር ወደ ታች ወርደው በመመልከት እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡ በተቋሙ ያለው የአመራር ምደባ በቅርብ አለቃ በሚሰጥ አስተያየት ወይም በሪኮመንዴሽን ከሚሆን ይልቅ የሥራ ልምድና ችሎታን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊፈጸም ይገባል ብለዋል፡፡ ተቋሙ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየገነባቸው ባሉ ፕሮጀክቶች እና አገልግሎት እየሰጡ ባሉ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት እና የሚጠየቀው የካሳ ክፍያ የተቋሙን አቅም እየፈተነ በመሆኑ ችግሩን በየደረጃው ከሚገኙ የክልልና የከተማ መስተዳደር አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት መፍታት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቶች በካሳ ክፍያ እና በግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት ችግር ምክንያት በተያዘላቸው መርሀግብር እየተጠናቀቁ ስላልሆነ ዘላቂ መፍትሔ እንዲቀመጥላቸው አሳስበዋል፡፡ ሠራተኛው እየደረሰበት ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም ተቋሙ ከሸማች ማህበራት ጋር ተነጋግሮ ሠራተኛው የድጎማ ዕቃዎችን የሚያገኝበት ሁኔታ እንዲያመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ውይይቱ ተቋሙ የተሰጡትን ኃላፊነቶች ለመወጣት እየተሰራ ባለው ስራ ላይ እየተነሱ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና የአመራር ብቃትን ለማሳደግ ያግዛል፡፡ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት ካልተጠናቀቁ የተቋሙ ፋይናንስ ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድሩ ያነሱት አቶ ደመረ የተቋሙን ወጭ ለመቀነስ ፕሮጀክቶችን በወቅቱ ማጠናቀቅ ይገባል ብለዋል፡፡ ከደመወዝና ጥቅማ ጥቅሞች ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና መሰረት በማድረግ በሂደት መፍትሔ ሊሰጠው እንደሚችል አቶ ደመረ ጠቁመዋል፡፡ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ በበኩላቸው ውይይቱ ግልጽነትን ለማስፈን፣ ከሰራተኞች ጋር ለመተዋወቅና በአመራሩና በሰራተኛው መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ አቶ አክብሮም አክለውም በውይይቱ የተነሱ ሃሳቦችን በዕቅድ በማካተት በአፈጻጸም ላይ ክትትል የሚደረግበትን አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያግዝና ውይይቱ በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት እና የካሳ ክፍያ የተፈጸመባቸውን ቦታዎች የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች መኖራቸውን ያነሱት አቶ ክብሮም በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ የተቋሙ የሰው ኃይል ስራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ከትርፍ ሰዓት አከፋፈል እና ከአመራር ምደባ ጋር እየተነሳ ያለውን ጥያቄ መፍትሔ ለመስጠት የአሰራር ስርዓት ማኑዋል እየተዘጋጀ በመሆኑ ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ከሠራተኞች የተነሱ ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን በግብዓትነት በመያዝና በዕቅድ በማካተት ተቋሙን ለመለወጥና ለችግሮች መፍትሔ ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ የሥራ ኃላፊዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህ በፊት ከተቋሙ የዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ጋር መሰል ውይይት መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይ በሌሎች የተቋሙ የሥራ አካባቢዎች ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ውይይቱ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 19 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+8

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳዔ በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል፡፡

በትንሳዔና በረመዳን በዓላት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ………/////……. በትንሳኤና በኢድ-አልፈጥር- ረመዳን በዓላት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስፈላጊው ዝግጅት አድርጓል፡፡ የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል እንዳስታወቀው በረመዳን ጾም የአፍጥር ዝግጅት፣ በትንሳኤ በዓልና በኢድ-አልፈጥር - ረመዳን በዓል የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም የኃይል ማመንጫዎች፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ያለፉትን ሦስት ዓመታት የበዓላት የኃይል ፍላጎት እና አቅርቦት መነሻ በማድረግ ካለፈው ዓመት በ2 ነጥብ 7 በመቶ ብልጫ ያለው ኃይል ለማቅረብ የማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጅት ማጠናቀቃቸውንም ማዕከሉ አስታውቋል፡፡ የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ለማድረግ ወደሱዳንና ጅቡቲ ኤክስፖርት ሲደረግ የነበረው ኃይል በግማሽ እንዲቀንስ ተደርጓል ብሏል፡፡ የኃይል ተጠቃሚው ፍላጎትን ተከትሎ በሥርጭት መስመሮች ላይ ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር ለመፍታት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ውይይት ተደርጎ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ማዕከሉ ገልጿል፡፡ የግሪድ ሲስተሙን በማረጋጋት ከፍተኛ ሚና በሚጫወቱት በጊቤ 3 እና በበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በልዩ ትኩረት ዝግጅት መደረጉም ታውቋል፡፡ በኃይል ማመንጫዎች፣ በማስተላለፊያ መስመሮችና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተደረገው ዝግጅት በተጨማሪ ማንኛውም ዓይነት የቴክኒክ ችግር ቢያጋጥም ችግሩን ሊፈታ የሚችል የአስቸኳይ ጥገና የቴክኒክ ቡድን ተዋቅሯል፡፡ ህብረተሰቡም የኃይል አቅርቦቱን ሊያስተጓጉሉ የሚችል የመሰረተልማት ስርቆት በሚመለከትበት ጊዜ በአቅራቢያው ለሚገኝ የህግ አካል እንዲጠቁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪውን ያቀርባል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 13 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ

photo content

የአዋሽ 7 ኪሎ - አሰበ ተፈሪ የማስተላለፊያ መስመር ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ስራ ተጠናቀቀ ……///……. ከሐምሌ 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ሲከናወን የቆየው የአዋሽ 7 ኪሎ - አሰበ ተፈሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኢንሱሌተሮችን የመቀየር ስራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የጥገና ሥራው አስተባባሪ አቶ ተካልኝ ጉተማ እንዳስታወቁት ኢንሱሌተሮቹን መቀየር ያስፈለገው የማስተላለፊያ መስመሩ በ1955 ዓ.ም. ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ጋር ተገንብቶ ረጅም ዓመት በማገልገሉ ነው፡፡ በእርጅና የተነሳ ኢንሱሌተሮቹ መሰባበር በመጀመራቸው የኢሌክትሪክ ኃይል እንዲቆራረጥና በሀገሪቱ ኃይል ስርጭት ላይም መስተጓጎል እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውሰዋል። ለወራት ሲከናወን በቆየው የኢንሱሌተሮች ቅየራ ሥራ በ262 ምሰሶዎች ላይ 786 ኢንሱሌተሮችን በአዲስ የፕላስቲክ ኢንሱሌተሮች ሙሉ በሙሉ መቀየራቸውን አስታውቀዋል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ በበኩላቸው እንደገለፁት ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ የጭሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ከባቡር መስመር ላይ ሲጠቀም ቆይቷል፡፡ የዚህ ስራ ውጤትም የሀገሪቱን ግሪድ ከማስተካከል ባለፈ በምዕራብ ሐረርጌ የሚኖረውን የከፍተኛ መስመር ኤሌክትሪክ መቆራረጥ የሚቀንስ መሆኑን ገልፀዋል። ይሁንና የጥገናና የኢንሱሌተር ቅየራ ሥራው የተከናወነው በ132 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ እሰከ አሰበ ተፈሪ(ጭሮ) ማከፋፈያ ጣቢያ በመሆኑ ከማከፋፈያ ጣቢያው በኋላ በ66 ኪሎ ቮልት እየተገለገሉ ያሉት የበዴሳና ገለምሶ አካባቢዎችን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለመቀነስ ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወሰድ አቶ ጋሻው አሳስበዋል። እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ ሥራውን ጥር 2014 ዓ.ም. ለማጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የጥገና ቡድኑ በጦርነት የተጎዱትን የኮምቦልቻ - ሰመራ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመር መልሶ የመጠገን ስራ ላይ በመሳተፉ ተጨማሪ ወራት ወስዷል፡፡ ለሥራው አስፈላጊ የሆኑትን ኢንሱሌተሮችን በማቅረብና የተለያየ ድጋፍ በማድረግ ከጎናቸው ለነበረው የመካከለኛ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ እና ለብሔራዊ ኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ማዕከል ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሥራው በተቋሙ የጥገና ባለሙያዎች 3 መቶ ሺህ ብር በሚደርስ ወጪ መከናወኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 12 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋፊያ ፕሮጀክት በአንደኛው ጉድጓድ የምርት ሙከራ በይፋ ጀመረ ……….////……. የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ከተጠናቀቀባቸው አራት ጉድጓዶች መካከል አንደኛው የምርት ሙከራ በይፋ መጀመሩን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ መሳይ ፍቃዱ እንደገለፁት የአምስተኛው ጉድጓድ ቁፋሮ ሰባት መቶ ሜትር ላይ ደርሷል፡፡ ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋፊያ ፕሮጀክት ስድስተኛውን የእንፋሎት ፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ ለማስጀመር የመቆፈሪያ ማሽን (ሪግ) ወደሚቆፈረው ቦታ በማንቀሳቀስ የመትከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አንድ ጉድጓድ ለመቆፈር በአማካይ እስከ 75 ቀናት ይፈጃል ያሉት አቶ መሳይ ቁፋሯቸው ከተጠናቀቁት አራት ጉድጓዶች መካከል የሁለተኛውን ጉድጓድ የምርት ሙከራ ሥራ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ይጀመራል ብለዋል፡፡ የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮው ወደ ከርሰ ምድር እስከ 3 ሺህ ሜትር ጥልቀት የሚኖረው ሲሆን ፕሮጀክቱ እስከ 70 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ታስቦ እየተሰራ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 11 ቀን 2014 ዓ/ም

+1

የሥራ ክፍሎች በመመሪያዎች መሠረት እየሰሩ ስለመሆናቸው ክትትል እየተደረገ ነው …….///…….. የተቋሙ የሥራ ክፍሎች መመሪያዎችን መሠረት አድርገው ሥራቸውን እየፈፀሙ ስለመሆናቸው ክትትል እያደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገ/እግዚአብሔር መዝገበ እንደገለፁት የሥራ ዘርፎቹ ባቀዷቸው ዕቅዶችና በተዘጋጁት መመሪያዎች መሰረት ሥራዎቻቸውን እያከናኑ መሆናቸውን መምሪያው ክትትል እያደረገ ነው፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን ያቀዳቸውን ተግባራት ከግብ ለማድረስ መምሪያው የክትትል ሥርዓቱን አጠናክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ ያለውን የመልካም አስተዳደር ሁኔታና አተገባበሩን በመፈተሽ ለሚስተዋሉ ክፍተቶች የማሻሻያ ሀሳብ በኦዲት ምርመራ አማካኝነት እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ መምሪያው የአመራሩንና የሠራተኞችን አፈፃፀም ከተቋሙ ፖሊሲ፣ ደረጃ፣ የአፈፃፀም ሥርዓት፣ ተፈፃሚነት ሊኖራቸው ከሚገቡ ህጎች፣ ፕሮግራሞች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን መመርመርና በሚታዩ ክፍተቶች ላይ የማሻሻያ ሃሳቦችን በማቅረብ እየሠራ ነው፡፡ መምሪያው ለሁሉም የሥራ ዘርፎች መስፈርቶችን እንደሚያዘጋጅ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ምንጮቹም ከፖሊሲዎች፣ መመሪያዎች፣ ከመልካም ተሞክሮዎች እና ሃገሪቱ እየተጠቀመችባቸው ከሚገኙ ህጎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የኦዲት ሥራዎች በሚከናወኑበት ወቅት በአንዳንድ የሥራ ዘርፎች ውስጥ መመሪያዎች እና ፖሊሲዎች በአግባቡ ተሰንደው አለመገኘታቸው በሥራው ላይ እንቅፋት እንደሆነ በመጥቀስ ተገቢው ውይይት ያልተደረገባቸውና ያልፀደቁ መመሪያዎችና ፖሊሲዎችን አስፀድቀው ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡ የኦዲት ምርመራው ለተቋሙ ተልዕኮ መሳካት መሆኑን ተገንዝቦ ሁሉም የሥራ ክፍል ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ማንኛውንም የሰነድና የሰው ኃይል መረጃዎችን በወቅቱ በማዘጋጀትና በማቅረብ ትብብር እንዲያደርጉ አቶ ገ/እግዚአብሔር ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 11 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content

የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር የማዕቀፍ ግዢ ሥምምነት ተፈረመ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ቴቢያን ኤሌክትሪክ አፓራተስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ (TBEA Co.,Ltd) ጋር የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር የማዕቀፍ ግዢ ሥምምነት ተፈራረመ፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የቴቢያን ኤሌክትሪክ አፓራተስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ተወካይ ሚስተር ዴቪድ ሃኦ ተፈራርመዋል፡፡ ሥምምነቱ ለሶስት ዓመታት የሚቆይ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊርስ (GIS Switchgears) የማዕቀፍ ግዥ (Framework Agreement) እንደሆነ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡ በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙትን ጨምሮ ተደጋጋሚ ብልሽት ሲያጋጥማቸው የቆዩትን የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያዎች በአዲስ የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ለመቀየር ያለመ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ የመጀመሪያው ዙር ግዢ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የሚፈፀም ሲሆን በዚህም 18 ባለ 15 ኪሎ ቮልት እና 26 ባለ 33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ስዊች ጊር በአዲስ ጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ለመተካት ይተካል ተብሏል፡፡ የማዕቀፍ ሥምምነቱ በሚቆይበት የሶስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ከ65 በላይ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያዎች ስዊች ጊር በአዲስ ጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ለመቀየር ታስቧል፡፡ የግዥ ሥምምነቱ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት የተያዘለት ሲሆን ፋይናንሱም ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚሸፈን ታውቋል፡፡ ሥምምነቱ በተደጋጋሚ ለሚነሱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል የተባለ ሲሆን ለተቋሙም ከፍተኛ የሆነ የጥገና ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 10 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

EEP Communication - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @eepcommuication