ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 554 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 399 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 163 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 554 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 12، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.73‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 14.92‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 157 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 320 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 554
المشتركون
+724 ساعات
+77 أيام
+1230 أيام
أرشيف المشاركات
ዘርፉ የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎች ይበልጥ መጠናከር አለባቸው ……///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን በኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ ሥር የሚ
+9
ዘርፉ የተጀመሩ የቅንጅት ሥራዎች ይበልጥ መጠናከር አለባቸው ……///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን በኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ ሥር የሚገኙ መምሪያዎች በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ፡፡ በዘርፉ ሥር የሚገኙት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን፤ የህግ አገልግሎት፤ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ እንዲሁም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያዎች በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወኗቸውን ሥራዎች አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በተቋሙ የሚገኙ ሴት ሠራተኞች መብትና ጥቅም ለማስከበር እና ማህበራዊ ችግሮቻቸውን ለመፍታት መንቀሳቀሱን ሲገልጽ የህግ አገልግሎት መምሪያ በበኩሉ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ የፍትሐብሔር፣ የሥራ ክርክር እና  የካሳ ጉዳዮችን በመከታተል የመርታት አቅሙን ማሳደጉን ገልጿል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ዘርፉ-የተጀመሩ-የቅንጅት-ሥራዎች-ይበልጥ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ዘርፉ የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም እየገመገመ ነው             ‎.....///..... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ ዘርፍ  የ2018 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን መገምገም ጀምሯል። ‎ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ ‎በግምገማው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት እንደ ተቋም የተያዙ ስትራቴጂያዊ ዕቅዶችን ለማሳካት የዘርፉን አበርክቶ መገምገም አስፈላጊ ነው። ስለሆነም በዘርፉ ስር ያሉ ሁሉም መምሪያዎች በስድስት ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ሥራዎችን በዝርዝር በማቅረብ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን ለማረም ግምገማው ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በዘርፉ የተከናወኑ የዕቅድ አፈጻጸሞች በግምገማው የሚቀርቡ ሲሆን የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችና የታዩ ክፍተቶችን በመገምገም እንዲሁም የቀጣይ ሥራዎችን አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ግምገማው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ የመሰረተ ልማት ሥርቆትን ለመከላከል የዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ ነው ..….///….… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈ
+2
ተቋሙ የመሰረተ ልማት ሥርቆትን ለመከላከል የዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ ነው ..….///….… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል የተዘረጋው ስትራቴጂ ውጤት እያመጣ መሆኑን በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ገለፀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት በመሰረተ ልማቶቹ ላይ ይፈፀም የነበረው ስርቆት ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የመቀነስ አዝማሚያ ታይቷል፡፡ በ12 ሪጅኖች የቀድሞ የመከላከያ መኮንኖችን በመመደብ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የመሰረተ-ልማት-ሥርቆትን-ለመከላከ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት ስድስት ወራት ለ139 ጉዳዮች ምላሽ ተሰጥቷል ……///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከውጭ ተገልጋዮች እና ከተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ለቀረቡ 139 አ
+4
ባለፉት ስድስት ወራት ለ139 ጉዳዮች ምላሽ ተሰጥቷል ……///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከውጭ ተገልጋዮች እና ከተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ለቀረቡ 139 አስተዳደራዊ ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠቱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት ለ 152 አስተዳደራዊ ጉዳዮች ምላሽ ይሰጣል በሚል የታቀደ ቢሆንም ለቀረቡት 139 አስተዳደራዊ ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ከዋና ስራ አስፈጻሚ በተሰጠ ውክልና መሠረት የተቋሙ ባለሙያዎች ለሚያከናውኗቸው ሙያዊ ተልዕኮዎች ድጋፍ ከመስጠት አንፃር ለ107 ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የፓስፖርት እድሳትና አዲስ ፓስፖርት እንዲያገኙ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ባለፉት-ስድስት-ወራት-ለ139-ጉዳዮች-ምላሽ-ተሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦት ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ረገድ ሚናው የጎላ ነው ……///……. የኃይል አቅርቦት በኮምቦልቻ ከተማ በተኪና ወደውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት ላይ ለተሰማሩ እንዲሁም ለፌደራል ለመንግ
+6
የኃይል አቅርቦት ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ረገድ ሚናው የጎላ ነው ……///……. የኃይል አቅርቦት በኮምቦልቻ ከተማ በተኪና ወደውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት ላይ ለተሰማሩ እንዲሁም ለፌደራል ለመንግስት ታክስ በመክፈል በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ያሉ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ በኩል ሚናው የጎላ እንደሆነ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ልሳነወርቅ እንዳስታወቁት በኮምቦልቻ ከተማ 127 ከፍተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ይገኛሉ፡፡ ከማህበረሰቡና ከመንግስታዊ ተቋማት በተጨማሪ በከተማዋ የሚገኙት የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት፣ የአምራችና የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከፍተኛ የሆነ የኃይል ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦት-ኢንዱስትሪዎችን-በመደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚያሳድጉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው …….///…… በኮምቦልቻ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በየጊዜው እያደገ የሚመጠውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች
+7
የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚያሳድጉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው …….///…… በኮምቦልቻ ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በየጊዜው እያደገ የሚመጠውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የጣቢያው ኃላፊ አስታውቀዋል፡፡ ኃላፊው አቶ ዝናቡ ገብሩ እንዳስታወቁት የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ የኢንዱስትሪ እና ከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ያለው የኃይል አቅርቦት ፍላጎት በፍጥነት እያደገ ይገኛል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው በ2002 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት ሲጀምር 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር እና አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ብቻ እንደነበሩት ያስታወሱት አቶ ዝናቡ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት መሰረት በማድረግ በተለያዩ ጊዜያት የአቅም ማሳደግ፣ ማስፋፊያና ማዘመን ሥራዎች እንደተከናወኑለት ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦት-አስተማማኝነት-የሚያሳ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦ
+7
ሪጅኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ተሻገር እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የአስቸኳይ ጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለማረጋጋት እና ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የጥገና እና የማሻሻያ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው ይህም የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እና የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት ለማሟላት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-አስተማማኝ-የኃይል-አቅርቦትን-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ .....///...... የሥራ መደብ፡ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒሻን I (Technician I EV Battery Charger) የትምህርት ደረጃ፡ ኮሌጅ ዲፕሎማ
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ .....///...... የሥራ መደብ፡ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒሻን I (Technician I EV Battery Charger) የትምህርት ደረጃ፡ ኮሌጅ ዲፕሎማ/TVET 10+3 ወይም በደረጃ 4 በአውቶሞቲቭ ኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ወይም አውቶሞቲቭ ኤሌክትሮ ሜካኒካል የተመረቀ። ልዩ መስፈርት፡ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ማቅረብ የሚችል። የሥራ ልምድ፡ አይጠይቅም (0 ዓመት)። የምዝገባ ቦታ፡ ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት፣ የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ (በአካል በመገኘት) ለበለጠ መረጃ በድረ ገጻችን https://www.eep.com.et/?amh-announcement=ክፍት-የሥራ-ቦታ-ማስታወቂያ መመልከት ትችላላችሁ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው
+6
የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …..///….. በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ ለሚገነባውና 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ላለው የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የፋይናንስ ሥምምነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከዋና ዋና የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር የከፍተኛ ደረጃ የአበዳሪዎች የቅድመ ኢንቨስትመንት ምርመራ ስብሰባ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በስብሰባው ላይ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የማክሮ ኢኮኖሚ እና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎችን በማድረግ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአይሻ-1-የንፋስ-ኃይል-ማመንጫ-ፕሮጀክትን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

@9:00

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪ
+1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘ .....///…... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቋቋም እና አሠራሩን በማዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፋማነት መሸጋገሩን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ አስታወቀ። የኢንቨስትመንት ሆልዲንጉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) እንደገለፁት ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡ አሁን ላይ የተመዘገበው ትርፍ ተቋሙ ካለበት የብድር ጫና ወጥቶ ራሱን እንዲችል መንገድ የሚከፍት መሆኑ ጠቁመዋል። ተቋሙ የነበረበት ከፍተኛ የብድር ጫና ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መተላለፉ፣ በመንግሥት የተተገበረው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የተደረገው የታሪፍ ማሻሻያ ለትርፉ መመዝገብ ድርሻው የጎላ መሆኑን ዶ/ር ብሩክ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ የኃይል አቅርቦት ቁልፍ ድርሻ ያበረክታል ……...///…….... በባህር ዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲጠናቀቅ
+6
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ የኃይል አቅርቦት ቁልፍ ድርሻ ያበረክታል ……...///…….... በባህር ዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲጠናቀቅ በከተማዋ እና በአካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ተሻገር እንደገለፁት በከተማዋ አንድ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሚገኝ ቢሆንም ጣቢያው የነዋሪውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ጥያቄ በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል አልነበረም፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-ሲጠናቀቅ-ለከተማዋ-የኃይል-አቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

አካዳሚው ዲጂታል የምዘና ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዲጂታል የምዘና ስርዓት መጀመሩን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ። በአካዳሚው የዕውቀት
+1
አካዳሚው ዲጂታል የምዘና ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ ጀመረ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዲጂታል የምዘና ስርዓት መጀመሩን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ አስታወቀ። በአካዳሚው የዕውቀት አስተዳደርና ብቃት ምዘና ተወካይ ስራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ አለማየሁ እንደተናገሩት ተቋሙ ከታህሳስ 2018 ዓ.ም ጀምሮ የዲጂታል ምዘና ስርዓት በይፋ ጀምሯል። የምዘና ሥርዓቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ በ18 የሥራ መደቦች ለ91 የተቋሙ ሠራተኞች የዲጂታል ፈተና ያለምንም ችግር መስጠት መቻሉን ገልፀዋል። በመጀመሪያው ዙር የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር ለሚወዳደሩ የተቋሙ ሠራተኞች በዋና መስሪያ ቤት፣ በደሴ፣ በሠመራ፣ በወላይታ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና በጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የዲጂታል ምዘና በስኬት መከናወኑንም ነው አቶ ፈቃዱ የገለፁት። በቀጣይም ሌሎች የዲጂታል ምዘናዎች ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም ተናግረዋል። የዲጂታል የምዘና ስርዓት ከዚህ ቀደም በሠራተኞች ይቀርብ የነበረውን የፈተና አወጣጥ የተአማኒነት ቅሬታ በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበታል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስድስት የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባዘጋጁት የፋይናንስ ኮንፈረንስ እየተሳተፉ ነው። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
+4
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ስድስት የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት በጋራ ባዘጋጁት የፋይናንስ ኮንፈረንስ እየተሳተፉ ነው። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እና “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል በተሰናዳው ኮንፈረንስ ስድስት የሀገራችን የፋይናንስ እና የገቢ ሥርዓት በመምራት ላይ ያሉ ዐበይት ተቋማት አፈፃፀማቸውን ያቀርባሉ። እነዚሁ ተቋማት ለሚቀጥሉት አምስት አመታት የሚኖራቸውን ስትራቴጂያዊ የቅድሚያ ምልከታ ለታዳሚው የሚያቀርቡ ይሆናል። መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ነው 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት ለማጠናቀቅ ነቅቶ መስራት ይገባል …….///……. አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት እና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ ሁሉም የዘ
+8
ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት ለማጠናቀቅ ነቅቶ መስራት ይገባል …….///……. አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት እና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ ሁሉም የዘርፉ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችኛ በንቃትና በመተባበር መስራት እንደሚጠበቅባቸውት የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አሳሰቡ፡፡ ዘርፉ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሲገመግም እንደተናገሩት ከፕሮጀክቱ የተገኙ ተሞክሮዎችንና ያጋጠሙ ችግሮችን ለቀጣይ ፕሮጀክቶች ግብዓት በሚሆን መልኩ አደራጅቶ ማስቀመጥ ይገባል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቶቹን-በተያዘላቸው-ጊዜ-እና-በጀት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙን መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የተገኙ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን ማጠናከር ያስፈልጋል …….///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በዘላቂነት ለመፍታት የታዩ ተስፋ ሰጪ ጅምሮች
+9
የተቋሙን መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የተገኙ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን ማጠናከር ያስፈልጋል …….///……. በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት በዘላቂነት ለመፍታት የታዩ ተስፋ ሰጪ ጅምሮችና የተገኙ ውጤቶችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ደህንነት መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከሪጅን ኃላፊዎችና ከመሠረተ ልማት ደህንነት የጥበቃ አባላት ኃላፊዎች ጋር በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አስመልክቶ ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ አጠናቋል። በግምገማው ላይ በሁሉም የተቋሙ ሪጅኖች የተመደቡ የመሰረተ ልማት ጥበቃ የሥራ ኃላፊዎች ሥራ ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ ባከናወናቸው ሥራዎች ላይ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ቀርበው ተገምግመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-መሠረተ-ልማቶች-ለመጠበቅ-የተገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል …….///……… የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ
+4
የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል …….///……… የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን የጣቢያው ኃላፊ ተናገሩ፡፡ ኃላፊው አቶ ደምሴ ሣህለማርያም እንደተናገሩት የኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ በ1976 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ነው፡፡ ጣቢያው በወቅቱ ከሸዋሮቢት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በሰባት ባለ 15 እና በአንድ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካው፣ ለኮምቦልቻና ለደሴ ከተሞች ኃይል ሲያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኮምቦልቻ-ቁጥር-1-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ለኢንዱ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫዎችን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ ተገለፀ …….///…….. በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን አቅምን ለማሳደግ እና የሥራ ላይ
+7
የኃይል ማመንጫዎችን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ ተገለፀ …….///…….. በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን አቅምን ለማሳደግ እና የሥራ ላይ ደህንነት መስፈርቶችን ለማስጠበቅ እንደሚሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የባለሙያዎች ቡድን በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው በጣቢያዎቹ ወቅታዊ የኦፕሬሽን አፈፃፀም፣ በማመንጨት ሂደት ላይ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች እና በሌሎች የዘርፉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመወያየት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማመንጫዎችን-የኦፕሬሽን-አቅም-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ዘርፉ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ነው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ሥራዎችን እያከና
+2
ዘርፉ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ነው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የጀኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን ተናገሩ። ዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀሙን እየገመገመ ይገኛል። ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር ኤፍሬም በግምገማው ላይ እንዳሉት ዘርፉ ተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮና የነደፈውን ስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ቀደም ሲል በተናጠል ሲሰሩ የነበሩት የኃይል ማመንጫ ግንባታ እና የኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎችን በአንድ ላይ በማድረግ የተቋቋመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ዘርፉ-እያደገ-የመጣውን-የኃይል-ፍላጎት-ለ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 5 ቀን 2018 ዓ.ም