ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 543 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 332 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 157 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 543 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.06‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.33‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 543
المشتركون
-1624 ساعات
-97 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በርካታ ሥራዎች መሥራት ይገባል ……….///……….. የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ተከትሎ እየመጣ ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በርካታ ሥራዎች እየሰራ ይገኛል፡፡ በዓመት በአማካይ በ6 በመቶ እያደገ የሚሄደውን የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ የኢንዱስትሪ ደንበኞችን ፍላጐት ለማሟላት የኃይል አቅርቦቱ አሁን ካለበት 3 ሺህ 271 ጊጋ ዋት ሰዓት ወደ 5 ሺህ 205 ጊጋ ዋት ሰዓት ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡ በተመሳሳይ በየዓመቱ በአማካይ በ20 በመቶ እንደሚያድግ የተተነበየውን የመካከለኛና ዝቅተኛ ኢንዱስትሪዎች የኃይል አጠቃቀም አሁን ካለበት 739 ጊጋ ዋት ሰዓት ወደ 3 ሺህ 285 ጊጋ ዋት ሰዓት ማድረስ ይገባል፡፡ ከዚህ ባልተናነሰ በአገልግሎቱ ዘርፉ ውስጥ የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና አስተማማኝነት ችግሮችን በማስወገድ፣ የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽና ቆይታና በማስተካከል የደንበኞችን እርካታ ማሻሻል ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ እንደ ሀገር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግንባታ፣ ኦፕሬሽንና ጥገና ወጪን ታሳበ ያደረገ ታሪፍ ቢተገበር አገልግሎቱን ለማሻሻልና ተደራሽነቱን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት ……….///……… ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን statistica የተሰኘ ድረ ገፅ ገልጿል፡፡ ድረ ገፁ ባሰፈረው መረጃ መሰረት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ አንጎላና ሊቢያ ለግለሰብ ተጠቃሚዎች በአንድ ኪሎዋት ሰዓት 0 ነጥብ 01 አንድ የአሜሪካ ሳንቲም ያስከፍላሉ፡፡ በአንፃሩ ጎረቤት ኬንያ በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 0 ነጥብ 22 የአሜሪካ ሳንቲም በማስከፈል ከመጨረሻ አንድ ደረጃ ብቻ ከፍ ብላ ኬፕ ቨርዴን ብቻ ቀድማ ውድ ታሪፍ ያላት ተብላ ተቀምጣለች፡፡ ማሊ፣ ሩዋንዳ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ጋቦን ውድ ታሪፍ ያላቸው ሀገራት ተብለው ሲቀመጡ በአንፃሩ ግብጽ፣ ናይጄሪያና ዛምቢያ በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 0 ነጥብ 02 የአሜሪካ ሳንቲም በማስከፈል ኢትዮጵያ ከተመደበችበት ከቀዳሚው ምድብ ቀጥሎ ዝቅተኛ ታሪፍ ያላቸው ሀገራት ተብለዋል፡፡ በአፍሪካ የአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ዝቅተኛው የኤሌክትሪክ ታሪፍ 0 ነጥብ 01 የአሜሪካ ሳንቲም ሲሆን ከፍተኛውና ውዱ ደግሞ 0 ነጥብ 31 የአሜሪካ ሳንቲም ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

አፍሪካ ኤሌክትሪክን ለማዳረስ የበጀት እጥረት ፈተና እንደሆነባት አንድ ዓለም አቀፍ ሪፖርት አመለከተ ……….///……… የዓለማችን 1/5ኛ ህዝብ የሚኖርባት አፍሪካ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት የበጀት እጥረት ፈተና እንደሆነባት ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጄንሲ አመለከተ፡፡ ኤጀንሲው የ2023 የዓለም ኢነርጂ ምልከታን አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው አፍሪካ በ2030 የኤሌክትሪክን ተደራሽ ለማረጋገጥ፣ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላትና ከኢነርጂ ጋር የተቀመጡትን ግቦች ለማሳካት የመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንቷን ከሁለት እጥፍ በላይ ማሳደግ ይጠበቅባታል፡፡ የአሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥና ለሁሉም አፍሪካውያን ንፁህ ኢነርጂ ተደራሽ ለማድረግ እ.ኤ.አ. ከ2026 ጀምሮ በየዓመቱ በአማካይ ሁለት መቶ ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር እንደሚያስፈልግም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ አንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ከነዳጅ ምርት ኤክስፖርት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ወጪያቸውን ለመተካት አልያም በብድር ለመሸፈን ጥረት እንደሚያደርጉ ቢገመትም በርካታ ሀገራት ግን ወጪያቸውን ለመሸፈን እንደሚቸገሩ ሪፖርቱ ስጋቱን አስቀምጧል፡፡ እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በአፍሪካ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ህዝብ መካከል ግማሽ የሚሆኑት ወይም 600 ሚሊዮን ሰዎች ምንም ዓይነት የኤሌክትሪክ ብርሃን አያገኙም፡፡ በአፍሪካ የኤሌክትሪክ ሽፋን 43 በመቶ ላይ የሚገኝ ሲሆን ናይጄሪያ 86 ሚሊየን የሚሆኑ ዜጎቿ ኤሌክትሪክ ባለማግኘት በቀዳሚነት ተቀምጣለች፤ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ኢትዮጵያ ደግሞ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡ የአፍሪካ ሀገራት ለኃይል ማመንጫነት ሊውሉ የሚችል የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት ቢሆኑምአብዛኛዎቹ ሀገራት ያላቸውን ፀጋ ወደ ኃይል ለመቀየት የበጀት እጥረት ከፍተኛ ፈተና ሆኖባቸዋል ይላል ሪፖርቱ፡፡ ይህን ለመቀየር ሀገራቱ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚገባቸው ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ማህበሩ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ ፈጽሜያለሁ አለ ……..////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ባለፉት አስራ አንድ ወራት በጡረታ ለተሰናበቱ የማህበሩ አባላት ከ2.8 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈፀሙን አስታወቀ፡፡ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በጡረታ ለተሰናበቱ ከ70 በላይ የማህበሩ አባላት በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ክፍያ ተፈፅሟል፡፡ በማህበሩ የነበራቸውን ቆይታ ታሳቢ ያደረገ ከአንድ እስከ ሁለት ወራት የደመወዝ ክፍያ የተፈፀመ መሆኑን የተናገሩት አቶ መኮንን ለአንድ የማህበሩ አባል 112 ሺህ ብር ክፍያ መፈፀሙን ነው ያስታወቁት፡፡ ሠራተኞች ለበርካታ ዓመታት ተቋማቸውን አገልግለው በጡረታ ሲሰናበቱ በክብር እና በምስጋና እንዲሰናበቱ በመደረጉ የጡረታ ተሰናባቾቹ ደስታቸውን ለማህበሩ በተደጋጋሚ እንደሚገልፁ ተናግረዋል፡፡ የማህበሩ አባላትን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ከዳሸን ባንክ የአለ በዱቤ ስምምነት በመፈራረም እና ሶስት ሚሊዮን ብር የዋስትና ገንዘብ ለባንኩ በማስያዝ የማህበሩ አባል ሠራተኞች የተለያዩ የቤት ቁሳቁሶችን በዱቤ እንዲገዙ እያገዘ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ማህበሩ ከዓመታዊ የደመወዝ ጭማሪ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ባሻገር የማህበሩ አባላትን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ለመፈፀም አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አቶ መኮንን ገልፀዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከ242 በላይ የተቋሙ ሠራተኞች ማህበሩን በአባልነት መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል፡፡ በ2007 ዓ.ም እንደ አዲስ የተመሰረተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ከ4 ሺህ በላይ አባላት ያሉት አንጋፋ ማህበር ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 03 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ እየተሰራ ነው ………///…….. የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ለማድረግ የሚያስችል የጥገና ሥራ በራስ አቅም እየተከናወነ መሆናቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደገለፁት ውሃን ለመቆጣጠር በሚያገለግለው ሹል ጫፍ ባለው የብረት አካል ወይም ኖዝል ላይ የገጠመው የመበላት ችግር የዩኒት አራት ተርባይን በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዳያመነጭ አድርጎት ቆይቷል። በተርባይኑ ላይ ያሉት ስድስት የኖዝል ጫፎች (needle tip)፣ ኢንሰርቶች እና ሲሎች በመቦርቦራቸው፣ አንዱ ኖዝል ውሃ ወደ ተርባይን ማስተላለፍ በማቆሙ እና ሌሎች ኖዝሎች ደግሞ ውሃና ዘይት በማስረጋቸው በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩንና የተርባይኑን የማመንጨት አቅም እስከ 45 ሜጋ ዋት ዝቅ ማድረጉን ጠቁመዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ተርባይኑ በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ለማድረግ ጉዳት የደረሰባቸውን የኖዝል አካላት የመጠገን ሥራ እየተከናወነ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ኖዝሎቹን ከተርባይኑ ላይ የማውረድ፣ ፈትቶ የማፅዳት እና በሌላ ለመተካት የማስተካከል ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ አንዱን ኖዝል ተርባይኑ ላይ መልሶ የመግጠም ሥራ ሲናቀቅ ሌላ ተጨማሪ አንድ ኖዝል ደግሞ ለመልሶ ገጠማ ዝግጁ ተደርጓል። የጥገና ሥራው በተርባይኑ 'ቤሪንጎች' ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን እና ሌሎች ተጓዳኝ ችግሮችን ቀድሞ ለመከላከል እንደሚያግዝም ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል። የጥገና ሥራው ከዚህ በፊት አገልግሎት የሰጡ እና ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ዕቃዎችን በጣቢያው ወርክሾፕ ላይ ማሻሻያ (modify) በማድረግ እየተከናወነ መሆኑን አቶ ሹመት ጠቁመዋል። በራስ አቅም እየተከናወነ ያለው የጥገና ሥራ የባለሙያዎችን በራስ የመተማመን አቅም ለማሳደግ እና በተቋሙ ክህሎት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ከማስቻሉም በተጨማሪ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ እና ከውጭ ምንዛሪ እንደሚታደግ አስገንዝበዋል። በተቋሙ ባለሙያዎች እየተሰራ ያለው ሥራ በውጭ ባለሙያዎች ቢሰራ ኖሮ ተቋሙን ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስወጣ ነበር ብለዋል። በኖዝሎች ላይ እየተከናወነ ካለው የጥገና ሥራ በተጨማሪ በቀጣይ በዩኒት አራት ዋና የውሃ መክፈቻና መዝጊያ ቫልቭ (Main Inlet Valve) ላይ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አቶ ሹመት ጠቅሰዋል፡፡ በጣቢያው የኤሌክትሪካል መሀንዲስ አቶ ምስጋና ደቻሳ እና መካኒካል መሀንድስ አቶ ፋንታሁን እስከዚያ በበኩላቸው የኖዝል አካላቶቹ ከውሃ ጋር ወደ ተርባይኑ በሚገባ ደለልና ጠጠር እንዲሁም በአገልግሎት ጊዜ ምክንያት ሊቦረቦሩ መቻላቸውን ገልፀዋል። በኖዝሎቹ ላይ የተስተዋለው ችግር የተርባይኑ የቁጥጥር ሥርዓት በማኑዋል እንዲከናወን ማስገደዱን ጠቅሰው ይህም ተርባይኑ ሲወጣ መልሶ ለማስገባት ተጨማሪ የሠው ኃይል እና ጊዜ እንዲጠይቅ አድርጎታል እንደነበር አንስተዋል፡፡ ኖዝሎቹ ተጠግነው ወደ ሥራ ሲገቡ የዩኒቱን የማመንጨት አቅም ለማሳደግ፣ ወደ ተርባይኑ የሚገባውን ውሃ ለማመጣጠን፣ በውሃ አጠቃቀምና በቁጥጥር ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፉ እና የቆመውን ተርባይን መልሶ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚወስደውን ጊዜ ለማሳጠር ያግዛል። ከግንቦት 12 ጀምሮ እየተከናወነ ባለው የጥገና ሥራ ላይ የጣቢያው ባለሙያዎችን ጨምሮ ከተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የተውጣጡ ባለሙያዎች እየተሳተፉበት የሚገኙ ሲሆን ሥራውንም እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ባሉት ጊዜያት ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው። በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጉልህ ሚና የነበራቸው ስመ ጥሩ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት በ2002 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ እያንዳንዳቸው 105 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ተርባይኖች አሉት። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የደጀን የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በቀጣዮቹ ወራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………..///………….. የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በመስክ ምልከታው ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰበሳቢ፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ፣ የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ የክልሉ እና የምስራቅ ጎጃም ዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ድረስ ሳህሉ የደጀን የማከፋፊያ ጣቢያን ጨምሮ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ልዩ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰበሳቢ የተከበሩ አቶ አስቻለ አላምሬ በበኩላቸው የደጀን ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢውን ሕዝብ የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት የሚፈታ እና ኢንቨስትመንትን የሚያነቃቃ መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደጀን የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተቆጣጣሪ እና አማካሪ አቶ ግርማ ብርሃኑ እንደገለጹት የማከፋፊያ ጣቢያው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመደበው 285 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ግንባታው እየተከናወነ ይገኛል። ግንባታው በግብዓት ችግር ምክንያት ከተቀመጠለት ጊዜ በላይ ቢወስድም የገጠሙት ችግሮች ተቀርፈው ሥራው በፍጥነት እየተከናወነ በመሆኑ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ወራት ግንባታውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የደጀን ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥንድ ገቢ መስመር፣ አምስት ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

በሠራተኞች የሰርቪስ አጠቃቀም ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶች በፍጥነት እንዲታረሙ ተጠየቀ ………..////………… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሠራተኞች የትራንስፖርት አጠቃቀም ላይ የሚስተዋሉ የሥነ ምግባር ጉድለቶች በአስቸኳይ እንዲታረሙ የተቋሙ ሥራ አመራር አሳሰበ። የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን አባላትና ሠራተኞች በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና አጠቃቀም ላይ በሚስተዋሉ ችግሮች እና የሥነ ምግባር ጉድለቶችን በማረም የሠራተኛውን ምቾት የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚቻልበት ዙሪያ ተወያይተዋል። የኢ.ኤ.ኃ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት በአንዳንድ የትራንስፖርት መስመሮች ላይ የተቋሙ ሠራተኞች ያልሆኑ ሰዎች አገልግሎቱን ከመጠቀም ባለፈ የሠራተኛውን ክብርና ምቾት የሚነሱ ተግባራት እየተፈፀሙ እንደሚገኙ ለሥራ አመራሩ መረጃ ደርሶበታል። ተቋሙ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያመቻቸው የሠራተኛውን ምቾትና ክብር ጠብቆ በሠዓቱ ወደ ሥራ ቦታው እና ወደ ቤቱ ለማጓጓዝ ብቻ ቢሆንም አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በትውውቅ፣ በዘመድ አዝማድና በቸልተኝነት ያላግባብ አገልግሎቱን ሌሎች ግለሰቦች እንዲጠቀሙበት በማድረግ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም እየተጋፉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በመሆኑም የትራንስፖርት አገልግሎት ማግኘት ካለባቸው የተቋሙ ሠራተኛ ውጪ ሌሎች ግለሰቦች እንዲጠቀሙ የሚያደርጉ ግለሰቦችን ለይቶ ተቋሙ ተጠያቂ እንደሚያደርግ ኃላፊው አንስተዋል፡፡ ለዚህም የተቋሙ ሠራተኞች ከሥነ -ምግባር ያፈነገጡ የአጠቃቀም ጉድለቶችን በንቃት መከታተልና ጥቆማ ማድረግ እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡ በውይይቱ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡ ሠራተኞች እንደገለፁት የተቋሙ ሠራተኛ ሳይሆኑ በየመንገዱ የሚሳፈሩና የሚወርዱ ግለሰቦች መበራከት ሠራተኛው አገልግሎቱን እንዳያገኝ ስለማድረጉ ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ አካሄዶች በሠራተኛው ደህንነት ላይ ሥጋት የሚደቅኑ በመሆናቸው ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚ ሠራተኞች በጋራ ክትትል በማድረግ የአጠቃቀም ሥርዓቱን የሚጥሱ ሠራተኞችን እንደሚያጋልጡ ተናግረዋል፡፡ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው በበኩላቸው የተነሱ ችግሮችን በማረም የተቀላጠፈና ጥራት ያለው የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ዘርፋቸው ቁርጠኛ መሆኑን አንስተዋል። ለሰርቪስ አገልግሎት የሚመደቡ ተሽከርካሪዎች የጥራት ደረጃቸውን ያሟሉ፣ በቂና ምቹ እንዲሆኑ ዘርፉ በትኩረት እየሰራ ነው ያሉት ወ/ሮ ስመኝ አገልግሎቱ የበለጠ አስተማማኝ እንዲሆን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ሳይሆኑ አገልግሎቱን የሚጠቀሙ ግለሠቦችን በቀላሉ ለይቶ ለማወቅ የሚያስችልና የሚሄዱበትን መስመር የሚገልፅ መታወቂያ መሰጠቱንም ነው ሥራ አስፈፃሚዋ የገለፁት፡፡ የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ሁሉም ሠራተኛ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ያቀረቡት ደግሞ የተቋሙ የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ ናቸው፡፡ ተቋሙ በየዓመቱ በጀት መድቦ በሚሰጠው የትራንስፖርት አገልግሎት አንድም ሠራተኛ ተቸግሮ ወደ ሥራና ወደ ቤቱ እንዲጓጓዝ አንፈልግም ያሉት ሥራ አስፈፃሚው ሠራተኛውም አገልግሎቱን ከራሱ ውጪ ለሌላ አካል መፍቀድ የለበትም ብለዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ባለፉት አስር ወራት ከ2 ሺ 700 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ……….///……… በሁለት ተርባይኖች ኃይል እያመነጨ የሚገኘው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ2016 በጀት ዓመት አስር ወራት ከዕቅዱ የ26 በመቶ ብልጫ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨቱን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ፡፡ በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሺፈራው እንደገለጹት ግድቡ በበጀት ዓመቱ አስር ወራት 2 ሺ 152 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 2 ሺ 711 ጊጋ ዋት ሰዓት ማአመንጭቷል። ይህም ከዕቅዱ የ26 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል። ግድቡ የተሻለ ውሃ መያዙና ሁለቱ ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ መደረጉ ለዕቅድ አፈፃፀሙ ከፍ ማለት ምክንያት እንደሆነ ሥራ አስኪያጇ አስታውቀዋል። እንደ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገለፃ ባለፋት አስር ወራት በአጠቃላይ ከመነጨው የ16 ሺ 900 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የ16 በመቶ ድርሻ አለው። ኃይል በማመንጨት ላይ የሚገኙት የግድቡ ሁለቱ ተርባይኖች እያንዳንዳቸው 375 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን በግድቡ ላይ የሚተከሉት ቀሪ 11 ዩኒቶች ኃይል ማምረት ሲጀምሩ አሁን በሀገሪቱ ያለውን የማመንጨት አቅም በ83 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ ይጠበቃል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 5,150 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም የሚኖረው ሲሆን ዓመታዊ የኃይል ምርቱም 15 ሺ 760 ጊጋ ዋት ሰዓት ይሆናል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የአካባቢ ጥበቃ ሥራ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን በቂ ኃይል እንዲያመነጩ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ………/////……… ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ “የተጎዳ መሬት እንዲያገግም የእንክብካቤ ሥራ እንስራ፤ በረሃማነትና ድርቅን ለመቋቋም የመሬት ማገገምን ማረጋገጥ!” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል፡፡ የበዓሉ መከበር በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች አስቀድሞ ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች የሚገመገሙበትና ቀጣይ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም የአካባቢ ጥበቃን ለማጎልበት ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የሚቀዳ የታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ሰጥታ በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም ሀገሪቱ ለተለያዩ ዓላማዎች የምታውለውን የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች መጎልበት የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል በመከላከል፣ የአየር ንብረት እንዳይዛባ እና ተፈጥሯዊ የዝናብ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ስለሆነም እያንዳንዳችን አካባቢያችንን በመጠበቅ የበኩላችንን ሚና እንወጣ መልዕክታችን ነው! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ “የተጎዳ መሬት እንድያገግም የእንክብካቤ ሥራ እንስራ፤ በረሃማነትና ድርቅን
ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ50ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ “የተጎዳ መሬት እንድያገግም የእንክብካቤ ሥራ እንስራ፤ በረሃማነትና ድርቅን ለመቋቋም የመሬት ማገገምን ማረጋገጥ!” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል፡፡ የበዓሉ መከበር በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚያጋጥሙትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች አስቀድሞ ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች የሚገመገሙበትና ቀጣይ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም የአካባቢ ጥበቃን ለማጎልበት ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የሚቀዳ የታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ትኩረት ሰጥታ በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም ሀገሪቱ ለተለያዩ ዓላማዎች የምታውለውን የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች መጎልበት የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል በመከላከል፣ የአየር ንብረት እንዳይዛባ እና ተፈጥሯዊ የዝናብ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ስለሆነም እያንዳንዳችን አካባቢያችንን በመጠበቅ የበኩላችንን ሚና እንወጣ መልዕክታችን ነው! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል!