ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 543 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 332 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 157 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 543 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 10، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -16، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.06‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.33‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 895 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 539 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 543
المشتركون
-1624 ساعات
-97 أيام
+1030 أيام
أرشيف المشاركات
የጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተለያዩ አገልግሎት ሊውሉ የሚችሉ ንብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ እንደሚከተለው በሎት በመከፋፈል አቅርበናል፡- ሎት-1- 20(ሀያ) ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፤ቦታ ኮተቤ አካባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የተቋማችን ዋና መ/ቤት ግቢ ውስጥ፤ ሎት-2- ከባድ ጥቁር እና ቀላል ናፍጣ መጠኑ ከፍተኛ ፤ ቦታ በድሬድዋ ከተማ አስተዳደር የኢንዱስትሪ መንደር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዲዝል ኃይል ማመንጫ ግቢ ውስጥ፤ ሎት-3- የጠጠር ማምረቻ (መፍጫ) ክሬቸር ማሽን፤ ቦታ መልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ግቢ ውስጥ፤ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡- በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ሠነድ ለመግዛት ሲመጡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወይም የታደሠ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፤ 1. የጨረታው ሂደት የሚከናወንበት ቦታ አዲስ አበባ ኮተቤ አከባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት፤ 2. የመወዳደሪያ ሰነድ መግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች የፋይናንስ አሰተዳደር ቢሮ የማይመለስ ብር 1,000.00(አንድ ሺ) በመክፈል የከፈሉበትን ደረሰኝ በመያዝ የንብረት አስተዳደር ቢሮ በመቅረብ የጨረታ ሁኔታን የሚገልጽ ዝርዝር መረጃ የያዘ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ መሙያ ቅጽ መውሰድ ይሮርባችኋል፤ 3. ተጫራቾች ሠነድ ገዝተው ማስታወቂያ ከወጣበት ከሰባተኛው ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታዎች በመገኘት መመልከት ይችላሉ፤ 4. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን ተቋሙ ባዘጋጀው ኦርጅናል ማህተም ባረፈበት ቅጽ ላይ ብቻ በመጠይቁ መሠረት በመሙላት በታሸገ ፖስታ ማዘጋጀት ግዴታ ሲሆን እንዲሞላ ከተዘጋጀው ስፍራ ውጭ የሚሞላ ጽሁፍ ከውድድሩ ሊያሰርዝ ይችላል፤ 5. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የምታሰሩት ሲ.ፒ.ኦ ህጋዊነቱን ለማረጋገጥ አመቺ እንዲሆን በአዲስ አበባበ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከሚገኙ ማንኛውም የባንክ ቅርንጫፎች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ብቻ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ የጨረታ ሳጥኑ ውስጥ ማስገባት ግዴታ ሲሆን ከመመመሪያው ውጪ የተሰራ ሲ.ፒ.ኦ. ተቀባይነት የለውም፤ 6.ተወዳዳሪዎች በሎት ሁለት ላይ ለመሳተፍ በፋብሪካ ምርት ስራ ላይ የተሰማራቹ ሆኖ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፋብሪካው በአከባቢው ላይ ጉዳት እንደማያደርስ የሚያረጋግጥ ሰነድ እንዲሁም የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆኑን የሚገልጽ ሰነድ አባሪ አድርጎ ማቅረብ ግዴታ ሲሆን ማቅረብ ያልቻለ ተወዳዳሪ ውጤቱ ውድቅ ይሆናል፡፡ 7. ጨረታው ከ23/09/16 እስከ 07/10/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ የሚቆይ ሲሆን ሰኔ 07 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጠዋት 4፡00 ድረስ የመወዳደሪያ ሰነድ ወደ ሳጥኑ ውስጥ ማስገባት ይኖርባችኋል፤ ሳጥኑ በዚሁ ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ በ4፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በተቋማችን አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል፤ ሆኖም ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ የቀረ ተጫራች ጨረታውን ከመከፈት ሊያስተጓጉል አይችልም፤ 8. በጨረታው አሸናፊ ለምትሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታችሁ በሚገለፅላችሁ ቀን ጀምሮ የሚቆጠር አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የአሸነፉችሁበትን ዋጋ ሙሉውን ክፍያ ለወደፊት በምናሳውቃችሁ ደብዳቤ ላይ በሚገለፀው የተቋማችን ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ የሽያጭ ውል ስምምነት መፈጸም ግዴታ ይኖርባችኋል፤ ሆኖም ግዴታቸውን የማይወጡ ተጫራቾች ያሲያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ. ለተቋማችን ገቢ ይደረጋል፤ 9. ከላይ የተጠቀሰውን እና በዋጋ መሙያ ሠነድ ላይ የተቀመጡ መመሪያዎችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታ ውድድር ውድቅ/ሊሰረዝ ይችላል፤ 10. ተቋሙ ጨረታውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የሚችል ሲሆን በማንኛውም ጊዜ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 11. ለተጨማሪ መረጃ ግንቦት 23/2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣውን የጨረታ ማስታወቂያ እና ግንቦት 24/2016 ዓ.ም የተሰጠውን የእርምት ማስተካከያ መመልከት እና በስልክ ቁጥር 011-558-14-24 ወይም 011-558-06-49 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና መስጠት ተጀመረ፤ .........///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሁሉም ሪጅኖች ያሉትን የጥገና ሥራዎች ለማዘመን የሚያስችለውንና በሁለተኛው የሳፕ ምዕራፍ ተግባራዊ የሚደረገውን የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና የመጀመሪያ ዙር መስጠት ተጀመረ፡፡ በኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የቴክኒክ ድጋፍ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱ ይማም እንደገለፁት በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበረው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ያለውን የጥገና ሥራ ለማዘመን ያስችላል፡፡ በጥገና አሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት፣ አስተዳደር እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገው የመጀመሪያው ዙር ስልጠና በተግባርና በንድፈ በመታገዝ ለቀጣዮቹ 15 ቀናት እንደሚሰጥ አቶ አብዱ ተናግረዋል፡፡ በሥልጠናው ላይ ከሰባት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የተውጣጡ የጥገና ኃላፊዎች እና የኤሌክትሪካልና ሜካኒካል መሀንዲሶች እየተሳተፉ ሲሆን በቀጣይ ለሌሎች የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ተመሳሳይ ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል፡፡ ሥልጠናው የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የቴክኒክ ድጋፍ ቢሮ ከሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የማከፋፊያ ጣቢያዎችን ከእሳት አደጋ ለመከላከል እየተሰራ ነው ……//…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፊያ ጣቢያዎች ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ የእሳት አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ነፃነት መላኩ እንዳስታወቁት በተቋሙ የማከፋፊያ ጣቢያዎች በተለያዩ ምክንያቶች የእሳት አደጋዎች እየተከሰቱ ይገኛል፡፡ ችግሩን አስቀድሞ ለመከላከል ለአደጋ ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮችን ተከታትሎ በማሰወገድ፣ በየጣቢያው ያሉትን ሠራተኞችን የእሳት አደጋ መከላከያ ስልጠና በመስጠት እና የእሳት አደጋ መከላከያ ስልክ ቁጥሮች በማስቀመጥ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በጣቢያዎቹ እሳት በሚነሳበት ጊዜ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት 16 የእሳት አደጋ መከላከያ መኪኖች መገዛታቸውን ተናግረዋል፡፡ መኪኖቹም የጣቢያዎቹን ተጋላጭነትና ሪጅኖቹ ያላቸውን የማከፋፊያ ጣቢያ ብዛት ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሚሰራጩ እና ሥራውንም በተቋሙ በሰለጠኑ ባለሙያዎች ለማከናወን መታቀዱን አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም በማሰራጫ መስመሮች ብልሽት ምክንያት የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን ለመከላከል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በዕቃዎች እርጅና ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ለመቅረፍም በአዲስ የመተካት እና ከፍተኛ የጥገና ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የጣቢያዎችን ዙሪያ አጥር የማጠናከር፣ አካባቢውን የማፅዳትና በመንገድ የማካለል ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው የተለያዩ መመሪያዎች በማዘጋጀት አሰራሩን ወጥና ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ለህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የተዘጋጀው itsmydam መተግበሪያ ተሻሽሎ ዳግም ሥራ ጀመረ ………..////…….. ላለፉት ሁለት ዓመታት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ለማሰባሰብ በሥራ ላይ የቆየው itsmydam መተግበሪያ ተሻሽሎ ሥራ ጀመረ፡፡ የተሻሻለው መተግበሪያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተዘጋጀ መርሀ ግብር ትናንት በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በመርሀ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት መተግበሪያው ከዚህ በፊት ሥራ ላይ ውሎ ከ250 ሺ ዶላር በላይ ልገሳ ተሰብስቦበታል፡፡ ለአጠቃቀም እንዲመች የተሻሻለው መተግበሪያ ለጋሾች ለሚያደርጉት ልገሳ በኢሜል አድራሻቸው የምስክር ወረቀት ማግኘት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አቤ ገለፃ ለጋሾች የቪዛ እና ማስተር ካርዳቸውን በመጠቀም ባሉበት ሆነው በስልካቸው አማካኝነት ከ5 እስከ 1000 ዶላር መለገስ ይችላሉ፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን መተግበሪያውን በመጠቀም በመገባደድ ላይ በሚገኘው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ አቶ አቤ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው 4 በመቶ ሥራ ብቻ የሚቀረውን የግድቡን ግንባታ በቀጣዩ ዓመት ለማጠናቀቅ 40 ቢሊዮን ብር ወይም 850 ሚሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡ ቀሪ ክፍያዎች በአብዛኛው በውጭ ምንዛሪ የሚከፈሉ ከመሆኑ አንፃር በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አስተዋጽኦ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የታለቁ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሔ በበኩላቸው ጽህፈት ቤቱ ‘በሕብረት ችለናል’ በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻ እያካሄደ መሆኑን በመግለጽ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሚችሉት ሁሉ ለግድቡ ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዳያስፖራ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይነህ አቅናው የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ዳያስፖራው የገንዘብ እና የዓይነት አስተዋጽኦ ቢያበረክትም በመላው ዓለም ከሚገኘው የዳያስፖራ ብዛት እና አቅም አንፃር ሲታይ የሚጠበቀውን ያህል እንዳልሆነ ገልፀዋል፡፡ ዲጂታል የድጋፍ ማሰባሰቢያ አማራጮች አለመኖር፣ የመረጃ ተደራሽነት እጥረት፣ በሀገር ውስጥ የተቋማት አለመቀናጀት እና ሌሎችንም ከዳያስፖራው ለተገኘው ድጋፍ ማነስ ተግዳሮት እንደነበሩ አቶ በላይነህ አንስተዋል፡፡ በድረ ገጽ እና በመተግበሪያ በሁለት አማራጮች የሚሰራውን Itsmydam የተሰኘው የድጋፍ ማሰባሰቢያ በማበልፀግ ሂደት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪ ኃይል፣ የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት እንዲሁም ኤግል ላዮን ሲስተም ቴክኖሎጂ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋሙ ቦታቸውን ለልማት ለለቀቁ ተነሺ አርሶ አደሮች የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር የዓይነት ድጋፍ አደረገ ....../////........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለወራቤ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ቦታቸውን ለለቀቁ ተነሺ አርሶ አደሮች የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር የዓይነት ድጋፍ ማድረጉን በተቋሙ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ባለሙያ አቶ ቤዛ አብርሃም እንደገለፁት የቡታጅራ ወራቤ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ባመቻቸው የመልሶ ማቋቋም ሥራ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ሲባል ተገቢው የካሳ ክፍያ ተከፍሏቸው ለተነሱ አርሶ አደሮች ተቋሙ የወተት ላሞችን ገዝቶ ድጋፍ አድርጓል። ማከፋፈያ ጣቢያው ካረፈበት ቦታ ለተነሱ 11 አርሶ አደሮች ለእያንዳንዳቸው አንድ አንድ የሆልስቲን ዝርያ ያላቸው የወተት ላሞች ከአንድ ወር መኖ ጋር በ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ገዝቶ መስጠቱን የገለፁት ባለሙያው ለቀሪ አምስት አርሶ አደሮችም በቅርቡ ርክክብ ይደረጋል ብለዋል፡፡ የመልሶ ማቋቋም ድጋፉ በአርሶ አደሮቹ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ወደ ፊት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን ውጤት ተቋሙ ከአርሶ አደሮቹ እንደሚጠብቅ አስገንዝበዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ በዙሪያቸው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን እንደራሳቸው ንብረት እንዲጠብቁ ባለሙያው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የወራቤ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅና ም/ከንቲባ አቶ ሻፊ ሙዜ በበኩላቸው በልማት የተነሱ አርሶአደሮችን መልሶ ለማቋቋም ተቋሙ ትኩረት በመስጠቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያደረገው ድጋፍ አርሶ አደሮች ራሳቸውን እንዲችሉ ከማድረግ ባሻገር በከተማዋ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የወተት እጥረት ለማቃለል እንደሚግዝ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ሻፊ ከተማ አስተዳደሩ ነዋሪዎችን በማሳተፍ የተገነቡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በባለቤትነት እንደሚጠብቅ አረጋግጠዋል፡፡ የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ነጃ ሺፋ በበኩላቸው ተቋሙ ለአርሶ አደሮች የገዛቸው የሆልሰቲን ዝርያ ያላቸው ላሞች በቀን በአማካይ ከ20 እስከ 30 ሊትር ወተት ስለሚሰጡ አርሶ አደሮቹ በአጭር ጊዜ ትልቅ ለውጥ ያመጣሉ ብለው እንደሚያምኑ ገልፀዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ በርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የተደረገላቸው ድጋፍ ለዕድገታቸው ትልቅ መነሻ በመሆኑ ተቋሙን መቼም እንደማይረሱት እና በተደረገላቸው ድጋፍ ትልቅ ለውጥ በማምጣት የተቋሙን ስም እንደሚያስጠሩም አረጋግጠዋል። ለማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ይዞታቸው ሲወሰድ ተቋሙ በቂ ካሳ እንደከፈላቸው እና የከተማ አስተዳደሩም 500 ካሬ ምትክ ቦታ እንደሠጣቸው የጠቀሱት አርሶ አደሮቹ ያሁኑ የመልሶ ማቋቋሚያ ድጋፍ ተጨማሪ በመሆኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሚገነባቸው የኃይል መሠረተ ልማቶች በተጨማሪ ለአካባቢው ማህበረሰብ የተለያዩ የማህበራዊ አገልግሎት ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+4

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል በአርክቴክት 1ኛ እና በአርክቴክት 2ኛ የሥራ መደብ ለመቅጠር መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም በወጣው ማስታወቂያ መሰረት መስፈርቱን አሟልታችሁ የተገኛችሁ ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾች በሙሉ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጠው ለአርክቴክት 1ኛ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን ለአርክቴክት 2ኛ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ከጠዋቱ 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት አዳራሽ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

ክለቡ ለዋና አሰልጣኙ የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አበረከተ ...///... የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዳግም እንዲመለስ ላደረጉት ዋና አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አበርክቷል። ክለቡ ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዳግም መመለሱን ተከትሎ ትላንት ምሽት በሒልተን ሆቴል የዕውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብር ተካሂዷል። በመርሐ-ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አለማየሁ መንግስቴ እንደገለፁት የስፖርት ክለቡ ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን ወክለው በመወዳደር የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ያደረጉ ዕውቅ ስፖርተኞችን ያፈራ ነው። እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ ክለቡ ከአራት ዓመታት የከፍተኛ ሊግ ቆይታ በኋላ በ2014 ዓ.ም ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ቢመለስም ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ዳግም ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዷል። በ2016 ዓ.ም ክለቡ አምስት ጨዋታ እየቀረው ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ድጋሚ መመለሱ እንዳስደሰታቸውም ነው አቶ አለማየሁ የገለፁት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚና የክለቡ ጠቅላላ ጉባዔ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንደገለፁት ክለቡ ዳግም ወደ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በመመለሱ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኢነርጂ ዘርፍ እያበረከቱት ያለውን አስተዋጽኦ በስፖርቱ ዘርፍም እየደገሙት መሆኑንም ነው የገለፁት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚና የክለቡ ጠቅላላ ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ክለቡ በ2017 ዓ.ም የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ተፎካካሪ ቡድን እንደሚሆን እምነት እንዳላቸው ገልፀዋል። የሁለቱ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች፣ የስፖርት ማህበሩ አባላት እንዲሁም መላው የስፖርት ቤተሰብ ለክለቡ ስኬታማነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናቸውንም አቅርበዋል። በመርሃ-ግብሩ ቡድኑ አምስት ጨዋታ እየቀረው ፕሪሚየር ሊጉን በመቀላቀሉ እንደ ተሳትፏቸው ደረጃ ከ20 ሺህ እስከ 355 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት ለተጫዋቾች፣ ለምክትል አሰልጣኞችና ለቡድን መሪዎች እንዲሁም ለድጋፍ ሰጪ አባላት ተበርክቷል። የስፖርት ክለቡ ውጤት እንዲያመጣ የክትትልና ድጋፍ  አስተዋፅኦ ላደረጉት የሁለቱ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎችም ሽልማት ተሰጥቷል። በዕውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብሩ ላይ የሁለቱ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ የከፍተኛ ሥራ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+9

ተቋሙ ተሽከርካሪዎችን በራሱ አቅም በመጠገን ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድኗል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተሽከርካሪዎቹን እና ማሽነሪዎቹን በራሱ አቅም በመጠገን ባለፉት አስር ወራት 25 ነጥብ 33 ሚሊዮን ብር ወጭ ማዳኑን የተሸከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ ገለፀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ አህመድ እንደገለፁት ተቋሙ በጋራዡ በተለያዩ ምክንያቶች የሚያጋጥሙ ድንገተኛ የተሽከርካሪ ብልሽቶች፣ የቅድመ መከላከል እና መደበኛ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ጋራዡ የተቋሙን ተሽከርካሪዎች የቦዲ፣የቀለም ቅብ፣ የ'ኢንጀክሽን ፓምፕ'፣ የሞተርና ሌሎች ከባድ፣ መካከለኛና ቀላል ጥገናዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል። እየተከናወኑ ያሉ የጥገና ሥራዎች ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ እየታደጉት እንደሆነ ያነሱት አቶ ሰይድ ባለፉት 10 ወራትም 1 ሺህ 293 ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ላይ የቀላል፣ መካከለኛና ከባድ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን 25 ነጥብ 33 ሚሊዮን ብር ማዳን ተችሏል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የሥራ ክፍሉ አዲስ ለሚገዙ ተሽከርካሪዎች ዝርዝር የቴክኒክ መስፈርቶችን የማዘጋጀትና በመስፈርቱ መሰረት መቅረባቸውን የማረጋገጥ እንዲሁም በተለያዩ ጋራዦች የሚጠገኑ ተሽከርካሪዎች በአግባቡ መጠገናቸውን የመከታተልና የመፈተሽ ሥራዎችን ያከናውናል። ቢሮው በኢንሹራንስ የሚሰሩ የተሽከርካሪ ጥገናዎችን እንደሚከታተል እና ባለፉት አስር ወራትም 67 የተቋሙ ተሽከርካሪዎች በኢንሹራንስ የጥገና አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል። በጋራዡ ለጥገና ሥራ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዘመናዊ መሳሪያዎችንና የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማሟላት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ሰይድ በአሁኑ ወቅትም 70 በመቶ የሚሆነው የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦት ችግር መቀረፉን አንስተዋል። ምንም እንኳን በጋራዡ ላይ የዘመናዊ መሳሪያዎች እጥረት ቢኖርም ሠራተኞቹ ያላቸውን ልምድና ክህሎት ተጠቅመው ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሆነ ነው አቶ ሰይድ የተናገሩት። በየዓመቱ ጥገና ከሚደረግላቸው ተሽከርካሪዎች ውስጥ 70 በመቶ የሚሆነው በራስ አቅም እየተከናወነ ሲሆን በቀጣይ የራስ ኃይል አቅምን ለማሳደግ ተቋሙ ለሥራ የሚያስፈልጉ የተለያዩ መሳሪያዎችንና መለዋወጫ ዕቃዎችን በአግባቡ ማሟላት እና ደረጃውን የጠበቀ ጋራዥ መገንባት እንደሚጠበቅበት ሥራ አስኪያጁ አፅንዖት ሰጥተዋል። የተሽከርካሪ ጥገና ባለሙያዎችን ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ ለማድረግና አቅማቸውን ለማሳደግ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጉን አስታውሰው ተጨማሪ ስልጠናዎችን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም ጠቁመዋል። አቶ ሰይድ አክለውም ከስልጠና ጎን ለጎን አዲስ ሠራተኞች ከነባሮቹ ጋር እንዲሰሩ በማድረግ የእውቀት ሽግግርና የሥራ ላይ ልምድ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙን በኃይል ልማት ዘርፍ ዓለም-አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለፀ ...///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ በተቋሙ የስብሰባ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ውይይቱ ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሪፎርም እና በሌሎች ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ያቀረቡት በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት በዓለም-አቀፍ ደረጃ ብቁ የሆኑ ሠራተኞችን ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው። በዚህም በፕሮጀክት ሥራዎች ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ የሥራ መሪዎች የፕሮጀክት አስተዳደር ሥልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ዓለም-አቀፍ የፕሮጀክት ሥራ አመራር ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ15 ሺህ ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የዕቅዱን 94 በመቶ ማሳካት መቻሉን የጠቆሙት አቶ አንዱዓለም ይህም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ14 በመቶ ብልጫ እንዳለው አመላክተዋል። የኃይል ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥራዎችን አስተማማኝ ለማድረግ የጥገና ሥራዎች በትኩረት ቢሰሩም በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ የፀጥታ ችግሮች ምክንያት ዕቅዱን ማሳካት እንዳልተቻለ ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለሀገር ውስጥ ከቀረበ የኃይል ሽያጭ ከ14 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ እንዲሁም ለውጭ ሀገራት ከቀረበው ኃይል ከ78 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል። አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችበማስወገድና ከውዝፍ የንብረት ኢንሹራንስ ካሳ ከ113 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የገለፁት ሥራ አስፈፃሚው ከአላስፈላጊ የመድን ሽፋን ክፍያ፣ ነዳጅ፣ ተሽከርካሪና ማሽነሪ ጥገናዎች ከ112 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉንም ጨምረው ገልፀዋል። በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማዳረስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ጋር በጋራ እየተሰራ ነው። የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማሟላት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የፕሮጀክት ማማከርና ግንባታ አቅምን በማሳደግ በዓለም-አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ለመፍጠር ይሰራል። በተቋሙ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንዲሁም ገፅታውን ለመገንባት በሚሰሩ ሥራዎች ላይ እያንዳንዱ ሠራተኛ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በውይይቱ ላይ ከፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓት፣ በራስ ኃይል የግንባታ ሥራዎችን ከማጠናከር፣  ምቹ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር፣ የሠራተኞችን ደህንነት ከማረጋገጥ፣ ከካሳ ክፍያና ስርቆት፣ ከታሪፍ ማሻሻያ፣ ከተሽከርካሪ የመለዋመጫ ዕቃዎች አቅርቦት እንዲሁም ከደመወዝና ጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ ከተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየቶች ቀርበው በዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3