ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 551 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 406 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 161 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 551 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -3، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.69‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.00‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 150 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 332 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 551
المشتركون
-524 ساعات
+97 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 9
+6
ማመንጫ ጣቢያው የ9 ወራት ዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ አሳካ ...///… የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 99 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ:: ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንዳስታወቁት ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ32 ተርባይኖች 258 ነጥብ 28 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዶ 256 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ችሏል። አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱንም ገልፀዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የጣቢያው ዝግጁነት ወይም የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ (Plant Availability) እና ኃይል ከሚያመነጨው አቅም አንፃር ጥቅም ላይ የዋለው (Utilization Index – UI) አፈፃፀም ከዕቅዱ በላይ መሆኑን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማመንጫ-ጣቢያው-የ9-ወራት-ዕቅዱን-99-ነጥብ-1-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተ
+5
የአጋሮ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለው ተገለፀ የአጋሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ ሁኔታ በማሟላት ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሞሲሳ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በ1980ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የነበረው የኃይል መጠን 132 ኪሎ ቮልት ብቻ ነበር። በወቅቱም በአንድ ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር እና በሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት ለአጋሮ ከተማና ለአካባቢው ውስን ማህበረሰብ ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርብ እንደነበር አስታውሰዋል።  ይሁን እንጂ በአካባቢው በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ተከትሎ በ2008 ዓ.ም ሰፊ የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራዎች ተከናውነውለታል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአጋሮ-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ተጨማሪ-ደንበኞች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በ
ያልተነካውን የፀሐይ ኃይል አቅማችንን ማልማት! ኢትዮጵያ ዐሥራ ሦስት ወራት ሙሉ የምታገኘውን የፀሐይ ብርሃን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግዙፍ የሶላር ፕሮጀክቶችን በዕቅድ እየመራ ይገኛል። እነዚህ የአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ ፕሮጀክቶች በኮፕ 32 መድረክ ላይ ለዓለም አቀፍ አጋሮች የሚቀርቡ ዋና ዋና ማሳያዎቻችን ናቸው። ታዳሽ ኃይልን ማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምንጠቀምበት ዋናው ስትራቴጂያችን ነው። የተፈጥሮ ብርሃን ለሀገር ብልጽግና! #SolarPower #RenewableEnergy #CleanFuture #COP32Sustainable #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለ
ከሜጋ ዋት በስተጀርባ ያሉት የብርሃን ታሪኮች! እኛ የምናመነጨው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ደረቅ ቁጥር ሳይሆን በኢንዱስትሪዎቻችን ውስጥ ለሚሰሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል፣ በጤና ተቋማት ውስጥ ለሚታደጉ ሕይወቶች ዋስትና፣ ለነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ ለሚሰንቁ ሕፃናት የብርሃን ምንጭ ነው! ኮፕ 32 በኢትዮጵያ መካሄዱ ሀገራችን የምታመነጨው አረንጓዴ ኃይል ማኅበራዊ ፍትሕንና የአየር ንብረት ጥበቃን እንዴት እያረጋገጠ እንደሚገኝ ለዓለም የምናስመሰክርበት ወሳኝ መድረክ ነው። ⚡️የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል - ሕይወትን በታዳሽ ኢነርጂ ማብራት! #HumanStory #Sustainability #CleanPower #COP32Ethiopia #EEPBrand #EmpoweringLives 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተር
የአየር ንብረት ለውጥን የማይበግረው የምድር ውስጥ እንፋሎት ኃይል! የአየር ንብረት ለውጥ የውሃ መጠንን በሚቀንስበት ጊዜ እንኳ ያለምንም መቆራረጥ 24/7 አስተማማኝ ኃይል መስጠት የሚችለው የጂኦተርማል (የምድር ውስጥ እንፋሎት) ኃይል የሀገራችን ሌላኛው ትልቅ አቅም ነው። ኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ያላትን ሰፊ የጂኦተርማል ኃይል አቅም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አማካኝነት ወደ ልማት እያቀረበችው ትገኛለች። ኮፕ 32 ሀገራችን በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ (Climate-Resilient) የኃይል አማራጮችን በማስፋፋት ረገድ ያላትን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ የምታጋራበት መድረክ ነው! ⚡️ የማይበገር አረንጓዴ ኃይል ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ! #GeothermalEnergy #ClimateResilient #CleanEnergy #COP32Ethiopia #EEP

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረ
1፡ ታሪካዊ ስኬት ለሀገራችን! ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) ለማስተናገድ መመረጧ፣ በታዳሽ ኃይል ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ ያሳያል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ፣ ከንፋስ፣ ከፀሐይና ከእንፋሎት (Geothermal) 100% ንፁህና ለአየር ንብረት የማይበክሉ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በስፋት በመገንባት የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በግንባር ቀደምትነት እየመራ ይገኛል። ኮፕ 32 ተቋማችን የሚያመነጨውን ዘላቂ ኃይል ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶችና ለአጋር ድርጅቶች ለማስተዋወቅ ትልቅ ድልድይ ነው! ኃይል ለኢትዮጵያ ብልጽግና፣ ንፁህ ኢነርጂ ለዓለም ደህንነት! #EthiopiaCOP32 #GreenEnergy #RenewablePower #EEP #CleanEnergy #ClimateAction 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ .......///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀንደርና ሶሻል አፌይርስ ኦፊሰር - 5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም የቀረበውን መስፈርት አሟልታችሁ የጽሁፍ ፈተና ከወሰዳችሁ መካከል ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች፤ ዕሮብ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ለሚሰጠው የቃል ፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም

የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰ
የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የተቋማችን አመራሮችና ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የአረፋ በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የጽናት፣ የሰዋዊ መተሳሰብና ለላቀ ዓላማ የመገዛት ታላቅ ተምሳሌት ነው። ተቋማችን በሀገሪቱን እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨትና በማስተላለፍ ረገድ ሀገራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት እየተወጣ ይገኛል። ይህን ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ይበልጥ ወደ ላቀ ስኬት ለማሸጋገርእንደ በዓሉ እሴቶች ሁሉ የሁላችንም የጸና ቁርጠኝነት፣ የጋራ ትብብርና ሙያዊ መስዋዕትነት እጅግ አስፈላጊ ነው። ሀገራችንን የብርሐን ማማ ላይ ለማድረስ ቀን ከሌሊት ለምትተጉ መላው የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ለምታበረክቱት ተቋማዊና ሀገራዊ ውለታ ተቋሙ ታላቅ ክብርና እውቅና ይሰጣል። የዘንድሮው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ለሀገራችን ሰላምና አንድነትን ለተቋማችን አዳዲስ ስኬቶችን ለሁላችንም ደግሞ የስራ ተነሳሽነታችንን የሚያድስ እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ። ዒድ ሙባረክ! ኢ/ር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማሳወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30
የውጤት ማሳወቂያ  ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት/Child Caregivers /የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/169/18 የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ አውጥቶ ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የፅሁፍ የተግባር ፈተና መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡   ስሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከተራ.ቁ1 እስከ 5 የተገለጸው አመልካቾች ከግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5/አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ  የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን
+4
የኃይል ማመንጫ ግድቦች በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ ይገኛሉ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በአስተማማኝ እና በጥሩ የደህንነት ቁመና ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ጀኔሬሽን ቢዝነስ የግድብ ደህንነት ክትትል እና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤሊያስ ደላሽ እንዳስታወቁት የግድቦችን ደህንነት ለማረጋገጥና ሊከሰቱ ለሚችሉ ችግሮች አስቀድሞ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ በግድቦችና ተያዥ አካላት ላይ በየጊዜው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ ይከናወናል፡፡   በዚህም ባለፉት አስር ወራት በመበልካ ዋከና፣ በግልገል ጊቤ አንድና ሁለት፣ ጊቤ ሶስት፣ ጢስ አባይ፣ ጣና በለስ፣ ቆቃ፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ገናሌ ዳዋ፣ ተከዜ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት ግድብ እና ተያያዥ ህዳጎች ላይ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማመንጫ-ግድቦች-በጥሩ-የደህንነት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ አፈፃፀም ከ96 በመቶ በላይ ደርሷል ...///.... ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አጠቃላይ ግንባታ 96 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት 1 ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ያለበትን የግንባታ ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። የመስክ ግምገማው ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የመጨረሻ ምዕራፍ የግንባታ አፈፃፀም እና በግንባታ ሂደቱ ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ የዕቃ አቅርቦት ተግዳሮቶች ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ነው። በዚሁ የመስክ ጉብኝት ወቅት ለከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድኑ ገለፃ ያደረጉት በኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት 1 ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ተሾመ እንደተናገሩት በማከፋፈያ ጣቢያው ውስጥ እየተከናወኑ የሚገኙ የፍተሻና የማስተካከያ ሥራዎች የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከሚኖሩት አራት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች መካከል 50 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ያለው አንዱ ትራንስፎርመር በተንቀሳቃሽ ስዊችጊር አማካኝነት አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ውጫዊ ክፍል የተተከሉ መሣሪያዎችን የመፈተሽ ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በመጥቀስ ሁለተኛውን የፍተሻ ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። አንዳንድ የመቆጣጠሪያ ኬብሎች እና የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎች በዕቃ አቅራቢ ኩባንያው በኩል ባለመቅረባቸው የተነሳ የሥራ መዘግየቶች እያጋጠሙ መሆኑንም ነው ያብራሩት። በአሁኑ ወቅትም የመቆጣጠሪያ ኬብሎችን እጥረት ለመቅረፍ ከሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በውሰት የማምጣት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስረድተዋል። የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ ደመላሽ ሙሉ እንደገለፁት በኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ የሚገኙ ፋብሪካዎች በፍጥነት ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ ይገባል። በማከፋፈያ ጣቢያው ያለውን ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከውሃ ምንጩ እስከ ጣቢያው ድረስ የ3 ኪሎ ሜትር የውሃ ቧንቧ መስመር ለመዘርጋት ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል። ዕቃ አቅራቢ ኩባንያው የቀሩትን ዕቃዎች በአስቸኳይ እንዲያቀርብና የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር የተቋሙ የሥራ አመራር ቡድን ጥብቅ መመሪያም አስተላልፏል። የኃይል ማከፋፈያው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ባለስልጣን ለሚፈልገው አገልግሎት ኃይል የሚያቀርቡ 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ እየተገነባ የሚገኝ ጣቢያ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ እና የማማከር ሥራ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ለግንባታ ሥራው የሚያስፈልገው ወጪም በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን እየተሸፈነ ይገኛል፡፡ ‎ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ‎…....///....... ‎ የገንደ አርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ጥረት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ‎በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘውን የገንዳርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ያለበትን የግንባታ ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። የመስክ ግምገማው ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የግንባታ አፈፃፀም እና በግንባታ ሂደቱ ላይ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ተወያይቶ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ነው። ‎በመስክ ግምገማው ወቅት በተቋሙ የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደገለፁት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና ወጪ የማይጠናቀቁት በወቅቱ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች በትኩረት ስለማይሰሩ ነው። ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት ኢንጂነር ውድነህ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች አቅርቦት ችግሮች በመፈታታቸው ዕቃዎቹ በአሁኑ ወቅት ወደ ጣቢያው እየገቡ መሆኑን አብራርተዋል። ከዚህ በኋላ ተከታታይ የሆነ የዕቃዎች አቅርቦት የሚኖር ከሆነ ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ እንደሚቻል አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት ላይ ማነቆ ሆኖ እየተስተዋለ ያለውን የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ከአካባቢው መስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት በመተባበር መፍትሔ ለመስጠት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው የጊዜ ገደብና ወጪ ለማጠናቀቅ ከተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጀምሮ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች በሪፖርት ብቻ ሳይወሰኑ በመስክ ተገኝተው መገምገማቸው ለሥራው መፋጠን ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። ‎እንደ ኢንጂነር ውድነህ ገለፃ በየጊዜው በሥራ መሪዎች የሚደረጉ የመስክ ምልከታዎች በፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ ለሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ይረዳል። ‎ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ደርሶበት የነበረው መስመር ተጠግኖ ኃይል መስጠት ጀምሯል ....…///….... ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የመልካ ዋከና - ራይቱ - ጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር በጊዜያዊነት ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ።   የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለጹት ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ "ኦዳ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ ከባድ ንፋስ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ በመስመሩ ላይ  ስድስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን እንዲወድቁ አድርጎ ነበር።   በዚህ የተነሳ ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የጎዴ እና የቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከጣቢያዎቹ ኃይል ሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱን አስታውሰዋል።   የወደቁትን ስድስት ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ሙሉ በሙሉ ጠግኖ ወደ መደበኛ አገልግሎት ለማስገባት ረጅም ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም የኅብረተሰቡን እንግልት ለመቀነስ እና ለአካባቢው አስቸኳይ ኃይል ለመስጠት ጊዜያዊ የአማራጭ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውንም ገልጸዋል፡፡    በዚህም አምስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት እና አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በመጠቀም ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በጊዜያዊነት መልሰው ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡   የወደቁትን ታወሮችን በዘላቂነት ለመጠገን የሚደረገው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።   በአካባቢው የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ወደነበረበት እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞች እና ለሥራው እገዛ ላደረጉ አካላት ዳይሬክተሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡። 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+6

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ለስልጤ ዞን ሁለንተናዊ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ...///... የወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መገንባት ለስልጤ ዞን ሁለንተናዊ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ። ዋና አስተዳዳሪው አቶ ዘይኔ ቢልካ በጣቢያው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የኃይል መሠረተ ልማቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ለአካባቢው የኢኮኖሚ፣ የኢንዱስትሪና የማህበራዊ ልማት መፋጠን የጎላ ድርሻ ይኖረዋል። ዞኑ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚካሄድበት ከ1 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ያረፈ የኢንዱስትሪ መንደር ልማት የተጀመረበትና ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍላጎት ያለበት አካባቢ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ባለፉት ዓመታት ያጋጥም የነበረው የኃይል አቅርቦት እጥረት ችግር የአካባቢውን እምቅ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም ትልቅ ማነቆ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ችግሩን በዘላቂነት ከመፍታቱም በላይ ለተጀመሩት የልማት ሥራዎችና ለአዳዲስ ኢንቨስትመንቶች አስተማማኝ ግብዓት መሆኑን አስገንዝበዋል። የወራቤ ከተማ በርካታ መጋቢ መንገዶችና የንግድ መስመሮች የሚገናኙባት ስልታዊ ቦታ መሆኗን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል መገኘቱ የከተማዋንና የአካባቢውን የንግድ ትስስር ይበልጥ እንደሚያሳድገውም ነው  የገለፁት። እንደ አቶ ዘይኔ ገለፃ በዞኑ ውስጥ ለሚገኙት የጤና፣ የትምህርትና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጣቢያው ያለው ፋይዳ እጅግ የጎላ ነው። ለፕሮጀክቱ መሳካት በቁርጠኝነት ለሠሩት ለክብርት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮች፣ ለግንባታ ተቋራጩ የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ እና ለአማካሪው እንዲሁም ለዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአካባቢው ማህበረሰብና አመራር ፕሮጀክቱን ከመጀመሪያው ጀምሮ በባለቤትነት ስሜት ሲደግፉና ሲከታተሉ መቆየታቸውን ያነሱት አቶ ዘይኔ በቀጣይም ይህንን ታላቅ ሀገራዊ መሰረተ ልማት በአግባቡ በመንከባከብና በመጠበቅ ረገድ  የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወጣ እምነታቸውን ገልፀዋል። 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፅ https://www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም