EEP Communication
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication
تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 695 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 016 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 154 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 695 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 145، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 31.28%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.96% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 909 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 661 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“EEP Communication”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.
15 695
المشتركون
+224 ساعات
+187 أيام
+14530 أيام
أرشيف المشاركات
15 695
የሀገርን ማዕዘናት በንጹህ ኃይል የማብራት ጉዞ
ሀገራችን ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን በጥቅም ላይ በማዋል የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን አበክራ እየሰራች ትገኛለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለፁት "የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችንን በስፋት በማሳደግ፣ የሀገራችንን እያንዳንዱን ማዕዘን እያበራን እንገኛለን" የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኤኮኖሚና በኃይል ዘርፍ የያዘችውን ሀገራዊ ራዕይና በተግባር ያሳካቻቸውን ስኬቶች ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።
ሀገርን በታዳሽ ኃይል ለማብራት ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡-
1. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 5,150 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ግዙፍ የውሃ ኃይል ማመንጫ ሲሆን የሀገሪቱን ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ አሳድጓል። ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ለዜጎች አስተማማኝ ኃይል ከማቅረቡ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ይገኛል።
2. የታዳሽ ኃይል ምንጮች አሰባጥሮ መጠቀም
ኢትዮጵያ እንደሀገር ከውሃ ኃይል ማመንጫዎች በተጨማሪ እንደ አሸጎዳ፣ አዳማ 1 እና 2፣ አይሻ 2 እና አሰላ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ሥራ መጀመር ከንፋስ የማመንጨት አቅምን 504 ሜጋ ዋት ያደረሱ ናቸው፡፡ ማሳደግ እንዲሁም የአይሻ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክትን የመሳሰሉ አዳዲስ ግንባታዎችን በማጠናቀቅ የኃይል አማራጩን ማሰፋፋት ተችሏል። በአሉቶ ላንጋኖ እና በቱሉ ሞዬ እየተካሄዱ ያሉ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች የወደፊት የኃይል ዋስትና ስብጥርን ከሚያረጋግጡ የታዳሽ ኃይል አማራጮች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዋናው ግሪድ ርቀው ለሚገኙ የገጠር አካባቢዎች የፀሐይ ኃይል አነስተኛ ግሪዶችን (Mini-grids) እና የቤት ውስጥ ሶላር ሲስተሞችን መስፋፋት የኃይል ተደራሽነትን lማሳደግ ተዐማሪ አቅም ፈጥሯል፡፡
3. የኃይል ተደራሽነትን ማፋጠን
በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በሺዎች የሚቆጠሩ መንደሮችና አነስተኛ ከተሞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ጣቢያዎችና የግብርና ምርት ማቀናበሪያዎች ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ጥራት ማሻሻል ተችሏል።
4. ቀጣናዊ የኃይል ትስስር
ኢትዮጵያ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች የሚመነጭ ንፁህ ኢነርጂ ወደ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ በመላክ የኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡
5. የግል አልሚዎች ወደ ዘርፉ መግባት
ዘርፉን ለማዘመን በተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የሀገር ውስጥና የውጭ የግል አልሚዎች (Private Developers) በኃይል ማመንጨት ሥራ ላይ በር የሚከፍት የፖሊሲ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል።
በአጠቃላይ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ማስፋፋት የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ከማሻሻሉም በላይ ሀገራችንን ወደ ተሻለ የኢንዱስትሪ እና የኢኮኖሚ እድገት የሚያሸጋግር የታሪካዊ ጉዞ አወንታዊ ማሳያ ነው።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥራትን ማሻሻል
….///….
በአንድ ሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚጫወተው ሚና ወደር የለውም። የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች መንቀሳቀስ፣ ለንግድ ተቋማት መስፋፋት፣ ለጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች መዘመን እንዲሁም ለዜጎች የዕለት ተዕለት ህይወት መሻሻል ዋነኛ መሰረት ነው።
ይሁንና ዘላቂና ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ማስፋፋት እና የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡
የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማለት አገልግሎቱ ያልደረሳቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን ከዋናው ግሪድ የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ማለት ነው። ይህን ማድረግ ከተቻለ አገልግሎቱን ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሐዊነት በማድረስ ማህበራዊ ፍትህን ለማረጋገጥ ያስችላል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-አቅርቦት-ጥራትን-ማሻሻል&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+9
"ተቋሙ የሚያካሂዳቸው ግዥዎች ከህግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ መሆን አለባቸው” ኢንጂነር አሸብር ባልቻ
….///….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዥ ሂደቶች ከሕግ ጥሰትና ከሙስና የጸዱ፣ በረጅም ጊዜ ዕቅድ ላይ የተመሠረቱ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ሊሆኑ እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ።
ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ በሚያከናውናቸው የግዥ ሂደቶችና የአሠራር ማሻሻያዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሂዷል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ እንደገለጹት ሕግና መመሪያን የተከተለ የግዥ አሠራር ሂደት ለተቋማዊ ዕድገትና ለመልካም አስተዳደር ወሳኝ ነው።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የሚያካሂዳቸው-ግዥዎች-ከህግ-ጥሰት&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+3
የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ የብድር አቅርቦት ስምምነት ተፈረመ
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሥራ መሪዎቹና ሠራተኞቹ የረጅም ጊዜ የብድር አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ሥምምነት ከኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ጋር ተፈራርሟል፡፡
ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደርቤ አስፋው ተፈራርመዋል፡፡
የተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ስለስምምነቱ እንደተናገሩት ተቋሙ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር የሚፈጥረው አጋርነት የሠራተኞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ከመፍታት ባሻገር ለወደፊት የፕሮጀክት ሥራዎች ማስፈፀሚያ የሚሆን የፋይናንስ ምንጭ ለማመቻቸት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የሥራ-መሪዎችና-ሠራተኞች-ተጠቃ&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን ተፋሰስ ሀገራት ከጎርፍ አደጋ እየጠበቃቸው ነው
….///….
በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት በየዓመቱ ከሚደርስባቸው የጎርፍ አደጋ እና መፈናቀል እየጠበቃቸው መሆኑን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሃይድሮሎጂ እና ውኃ ሀብት ተባባሪ ፕሮፌሰር ደመላሽ ወንድምአገኘሁ (ዶ/ር) ገለፁ።
ደመላሽ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት ለረጅም ጊዜ የታችኞቹ የናይል ተፋሰስ ሀገራት በተለይም የሱዳን እና የግብፅ ሕዝቦች በክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ፣ ለንብረት ውድመት እና መፈናቀል ይዳረጉ ነበር።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መገንባት አፈር በከፍተኛ ጎርፍ ተጠርጎ እንዳይወስድ በማድረግ የታችኞቹ ሀገራት ውሃውን እና አፈሩን በተሻለ እና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙበት እያገዛቸው መሆኑን አብራርተዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-የታችኞቹን&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው?
....///.....
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበለጠ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ዘመናዊ ማድረግ ነው። ይህ ሂደት ተለምዷዊውን የኤሌክትሪክ ግሪድ ከኢንተርኔት፣ ሴንሰሮች፣ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ ዳታ ትንተናና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማዋሃድ እንደ “ስማርት አውታር” (Smart Grid) እንዲኖር የማድረግ ሂደት ነው።
ይህ አሰራር የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የተጠቃሚዎችን ቆጣሪዎች በአንድ ዲጂታል ኔትወርክ በማገናኘት አጠቃላይ ስርዓቱ እርስ በእርሱ እንዲናበብና በራስ-ሰር (Automatically) እንዲቆጣጠር ያስችለዋል። በሌላ አገላለጽ፣ ዲጂታላይዜሽን የኤሌክትሪክ ግሪዱን “ባለ አእምሮ” ሥርዓት ያደርገዋል — ሥርዓቱ በራሱ መረጃ መሰብሰብ፣ መተንተንና በመተንተን ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት ይችላል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ግሪድ-ዲጂታላይዜሽን-ምንድ&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ምንድነው?
....///.....
የኤሌክትሪክ ግሪድ ዲጂታላይዜሽን ማለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍና ማከፋፈል ሥርዓትን ዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የበለጠ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ዘመናዊ ማድረግ ነው። ይህ ሂደት ተለምዷዊውን የኤሌክትሪክ ግሪድ ከኢንተርኔት፣ ሴንሰሮች፣ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ ዳታ ትንተናና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማዋሃድ እንደ “ስማርት አውታር” (Smart Grid) እንዲኖር የማድረግ ሂደት ነው።
ይህ አሰራር የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የተጠቃሚዎችን ቆጣሪዎች በአንድ ዲጂታል ኔትወርክ በማገናኘት አጠቃላይ ስርዓቱ እርስ በእርሱ እንዲናበብና በራስ-ሰር (Automatically) እንዲቆጣጠር ያስችለዋል። በሌላ አገላለጽ፣ ዲጂታላይዜሽን የኤሌክትሪክ ግሪዱን “ባለ አእምሮ” ሥርዓት ያደርገዋል — ሥርዓቱ በራሱ መረጃ መሰብሰብ፣ መተንተንና በመተንተን ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት ይችላል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-ግሪድ-ዲጂታላይዜሽን-ምንድ&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+6
ተቋሙ በጥናቱ ላይ ተመስርቶ አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ይሰራል
....///.....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጠውን አገልግሎት በጥናት ላይ ተመስርቶ ለማዘመንና የተጣለበት ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የምርምርና ልማት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢትወደድ ገብረአሊፍ ገለጹ፡፡
በደንበኞች እርካታ፣ በድርጅታዊ ባህል፣ በሠራተኞች የሥራ እርካታ እና ተሳትፎ ዙሪያ በኢትዮ ፓወር አካዳሚ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምርምርና የልማት ቡድን በጋራ የተከናወኑ ጥናቶች ለተቋሙ አመራሮች ቀርቧል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ የጥናቶቹ ዓላማ፣ ስልትና ሞዴል፣ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች፣ የናሙና አወሳሰድ፣ ንጽጽር፣ ግኝትና ምክረ ሀሳቦች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን ቀርበዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በጥናቱ-ላይ-ተመስርቶ-አገልግሎት-አ&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት እና አስተማማኝነት - ለእድገት
......///.......
የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነት (accessibility) እና አስተማማኝነት (dependability) የማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን ቁልፍ ሞተሮች እና የዘመናዊ እድገት መለኪያ ጠቋሚዎች ናቸው። ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ፣ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና ቀጣይነት ያለው ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሠረቶች ናቸው።
በልማት ኤኮኖሚክስ እና በኃይል ፖሊሲ ዘርፍ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አስተማማኝ እና ፍትሐዊ የኃይል አቅርቦት የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የሰው ኃይል አቅምን ለማጎልበት እና የተቀናጀ ሀገራዊ ዘላቂ የልማት ለማሳካት አስፈላጊ ግብዓት ነው።
1. የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት (Accessibility)
የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማለት አገልግሎቱን በከተማም ሆነ በገጠር ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሐዊነት፣ በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማድረስን የሚያመለክት ....
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-አገልግሎት-ተደራሽነት-እና&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+9
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
......///.......
ለበለጠ መረጃ .... 👇
https://www.eep.com.et/?amh-announcement=የፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ-5&lang=am
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+6
ጥናቱ ለተቋሙ አመራሮች እየቀረበ ነው
….….///….….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓወር አካዳሚ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምርምርና የልማት ቡድን በጋራ የተከናወነው ጥናት ለተቋሙ አመራሮች እየቀረበ ነው፡፡
የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንዶሰን ካሳ ጥናቱ በደንበኞች እርካታ፣ በድርጅታዊ ባህል፣ በሠራተኞች የሥራ እርካታ እና በተሳትፎ ደረጃ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
ጥናቱ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ ድርጅታዊ ባህልን ለማጠናከር እና የበለጠ ቁርጠኝና ደስተኛ ሠራተኛን ለመገንባት የሚያግዝ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
መድረኩ ከተቋሙ አመራር በጥናቱ ላይ ግብረ መልስ ለማሰባሰብና እና በቀጣይ በጥናቱ ግኝት አፈጻጸም ላይ የባለቤትነት ስሜት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
......///.......
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ሚና
.....///.....
ብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ በሀገሪቱ ውስጥ የሚመረት ማናቸውንም የኃይል አቅርቦት በደህንነት፣ በጥራት እና በብቃት ለአገልግሎት ለማዋል የሚያስችል ሀገራዊ የኃይል ኔትወርክ ነው። ይህ ኔትወርክ በልዩ ልዩ አካባቢዎች የሚገኙ የውሃ፣ የነፋስ፣ የፀሐይ እና የጂኦተርማል ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ወደ አንድ ማዕከላዊ ሥርዓት ያገናኛል።
ዋነኛ ተግባራት፦
ኃይል ማጓጓዝ፦ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ከፍተኛ ቮልቴጅ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች አማካይነት ኤሌክትሪክን ከተመረተበት ቦታ ወደ ሩቅ ከተሞችና የኢንዱስትሪ ማዕከላት ያጓጉዛል።
ፍላጎትና አቅርቦትን ማመጣጠን፦ በየቀኑ እና በየሰዓቱ የሚቀያየረውን የኤሌክትሪክ ፍላጎት (Demand) እና ማመንጫዎች የሚያቀርቡትን ኃይል (Supply) በማመጣጠን የኃይል መቋረጥን ይከላከላል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የብሔራዊ-ኤሌክትሪክ-ግሪድ-ሚና&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
አረንጓዴ አሻራ - ለዘላቂ የኃይል ዋስትና
.....///.....
በኢትዮጵያ በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የአካባቢ ጥበቃ እና የደን ሽፋን ማሳደጊያ ስልት ብቻ አይደለም። ከዚህ ባሻገር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ለሆኑት የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ህልውና እና ዘላቂነት እጅግ ወሳኝ የሆነ ግብዓት ነው።
ከ90% በላይ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃ የምታመነጨው ኢትዮጵያ የግድቦቿን ህልውና ለማስጠበቅ እና አቅማቸውን ለማጎልበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከግድቦች ደህንነት እና ጥበቃ ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ከአባባቢ ጥበቃ በዘለለ በርካታ ጠቀሜታዎች ይኖሩታል፡፡
1. የደለል ክምችትን የመከላከል ሚና
የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በአግባቡ ኃይል እንዳያመነጩ ከሚያደርጓቸው ችግሮች መካከል አንዱ የደለል ክምችት ነው። የደን ጭፍጨፋ እና የአፈር መሸርሸር በሚኖርበት ጊዜ ከባድ የክረምት ዝናብ ለም አፈርን እያጠበ ወደ ወንዞች እና በቀጥታ ወደ ግድቦች እንዲገባ ያደርጋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=አረንጓዴ-አሻራ-ለዘላቂ-የኃይል-ዋስትና&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
የኤልኒኖ (El Nino) ክስተት እና የኃይል አቅርቦት
ብዙ ጊዜ የኤልኒኖ ክስተት ሲነሳ አእምሯችን ወደ ድርቅ፣ የምግብ እጥረት እና የግብርና መስተጓጎል ያደላል። ነገር ግን ኤልኒኖ ከአየር ጠባይ መዛባት ባሻገር በቀጥታ ከምንጠቀመው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ደህንነት ጋር እጅግ ጥብቅ የሆነ ትስስር አለው።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አብዛኛው የኤሌክትሪክ ኃይላቸውን ከውሃ (Hydropower) በሚያመነጩ ሀገራት ላይ የኤልኒኖ መከሰት በኃይል አቅርቦት ስርዓቱ ላይ ግዙፍ ፈተና ይደቅናል።
1. የኤልኒኖ ክስተት ምንድን ነው?
ኤልኒኖ በፓሲፊክ ውቅያኖስ አካባቢ የሚከሰት የአየር ጠባይ መዛባት ሲሆን የውቅያኖሱ ወለል የሙቀት መጠን ከተለመደው በላይ ሲጨምር የሚከሰት ነው። ይህ የሙቀት መጨመር፡-
· የዓለም አቀፍ የንፋስና የዝናብ ስርጭትን ያዛባል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ የክረምት ዝናብ ስርጭትን በመቀነስ ለከፍተኛ ድርቅ እና የውሃ እጥረት ይዳርጋል።
በሌሎች የዓለም ክፍሎችም ያልተለመደ ከባድ ጎርፍ ያስከትላል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤልኒኖ-el-nino-ክስተት-እና-የኃይል-አቅርቦት&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
ከማብሪያና ማጥፊያ የሚዘለው የብርሃን ጉዞ
……///……..
ብዙዎቻችን ቤታችን ስንገባ እንደምናገኘው የማብሪያና ማጥፊያ ቁልፍ ኃይልን የምናገኝበት እና ሲቋረጥም ወደነበረበት የምንመልስበት ሂደት ቀላልና አፍታ የማይወስድ ተግባር ይመስለናል። ነገር ግን ማብሪያና ማጥፊያውን በተጫንንበት ቅጽበት በቤታችን ወይም በሥራ ቦታችን የሚበራው የኤሌክትሪክ ኃይል እኛ ዘንድ ለመድረስ የሚያልፍበት መንገድ እጅግ ውስብስብ፣ አደገኛ እና በሺዎች የሚቆጠሩ የዘርፉ ባለሙያዎችን የሌሊትና ቀን የማይቋረጥ አድካሚ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑን ምን ያህል እንረዳለን፡፡
በሸለቆዎችና በበረሃዎች የሚጀመር የኃይል ማመንጨት ሂደት
የኃይል አቅርቦት ጉዞው የሚጀምረው ከኃይል ማመንጫዎች ነው። በኢትዮጵያ አብዛኞቹ የውሃ ኃይል ማመንጫዎች የሚገኙት ከመኖሪያ በራቁ አካባቢዎች፣ ከፍተኛ ንፋስና ሙቀት ባለባቸው በረሃዎች እና ሸለቆዎች ውስጥ ነው። በእነዚህ አስቸጋሪ አየር ጠባይና መልክዐ ምድር ውስጥ የሚሰሩ መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች ግዙፍ የውሃ እና የንፋስ ተርባይኖችንና ጄነሬተሮችን በከፍተኛ ጥንቃቄ...
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ከማብሪያና-ማጥፊያ-የሚዘለው-የብርሃን-ጉ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+3
የወደቀው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት እስኪጀምር የኃይል ፍሰት የማመጣጠን ሥራ ይሰራል
………///……..
በለገጣፎ - ቃሊቲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በደረሰ ጉዳት ምክንያት የወደቁ 5 የብረት ምሰሶዎችን በመጠገን ዳግም አገልግሎት መስጠት እስኪጀምሩ ድረስ የኃይል ፍሰት የማመጣጠን ሥራዎች እንደሚሰሩ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡
በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዘለቀ እንደገለፁት የብረት ምሰሶዎቹ የወደቁት በከባድ አውሎ ንፋስ ምክንያት ቢሆንም ቀደም ሲል በምሰሶዎቹ አካላት ላይ ይፈፀም የነበረው ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀል ለጉዳቱ መከሰት አሉታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
በወደቁት የብረት ምሰሶዎች ላይ በተደረገው የቴክኒክ ፍተሻ መሰረት የተሰረቁ የምሰሶ አካላትን መልሶ ለመተካት በማሻሻያ (Modification) መልክ ይገጠሙ የነበሩት ብረቶች የምሰሶዎቹን መደበኛ ጥንካሬና የመሸከም አቅም ማምጣት አለመቻላቸው መረጋገጡን ተናግረዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የወደቀው-የኃይል-ማስተላለፊያ-መስመር-ተ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
ጥብቅ የውሃ አስተዳደር ሥርዓት የመዘርጋት አስፈላጊነት!
.....///.....
ውሃ ለኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ልማት ዋነኛውና ዋናው የኃይል ምንጭ ነው። በተለይም በውሃ ኃይል ማመንጫዎች የሚመረተው እያንዳንዱ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የሚጀምረው ከአንዲት የውሃ ነጠብጣብ በመጠራቀም በመሆኑ የውሃ አጠቃቀምና አስተዳደር ሥርዓት በኃይል ማመንጨት ሂደት ቁልፍ ሚና አለው!
ጥብቅ የውሃ አስተዳደር ለኃይል ዘርፉ ያለው ወሳኝ ፋይዳ
የኃይል ብክነትን መቀነስ
በወቅታዊ የአየር ንብረት መለዋወጥና ያላግባብ በሚባክን የውሃ ሀብት ምክንያት የሚፈጠርን የኤሌክትሪክ ማመንጨት አቅም መቀነስ ይከላከላል።
ዘላቂ የኃይል አቅርቦት
ግድቦች ሙሉ የማመንጨት አቅማቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እና ሥርዓት ባለው ሁኔታ እንዲጠቀሙ ያስችላል።
ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ
እያንዳንዷ የምትባክን የውሃ ነጠብጣብ በኃይል ማመንጨት ሂደት ላይ የምታሳድረው ተጽዕኖ በቀጥታ በመኖሪያ ቤቶች፣ በፋብሪካዎች፣ በንግድና በማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ተጽዕኖ ስለሚያሳድር ውጤታማ ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ጥብቅ-የውሃ-አስተዳደር-ሥርዓት-የመዘርጋ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም
15 695
+3
በሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነት ዙሪያ ሥልጠና እየተሰጠ ነው
……///…….
በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ሪጅኖች ለተመደቡ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና አስተባባሪ መሐንዲሶች በሥራ ላይ ደህንነት ላይ ያተኮረ ሥልጠና መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ኮርሳ ተሬሳ እንደገለፁት ሥልጠናው መሐንዲሶቹ በተመደቡባቸው የሥራ ቦታዎች ላይ በሚኖራቸው የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤንነት ክትትልና ቁጥጥር ላይ ያላቸውን የማስፈፀም አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው።
ሥልጠናው ባለሙያዎቹ በሥራ ላይ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ስጋቶችን በመለየት መከላከል በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱን ነው የገለፁት።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=በሥራ-ላይ-ደህንነት-እና-ጤንነት-ዙሪያ-ሥ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም
