የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 400
المشتركون
-22624 ساعات
-2 2007 أيام
-2 65830 أيام
أرشيف المشاركات
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ማስተባበሪያ ማአእከል ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ተከታዩን መልእክት አጋርተዋል።
ሁላችንም እንደምንገዘበው ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ወደ 1700 ኪ.ሜ የሚጠጋ በድንበር የሚዋሰኑ እና ተመሳሳይ ባህል፣ ቋንቋ እና ኃይማኖት የሚጋሩ ሕዝቦች ያሏቸው ሀገራት ናቸው፡፡
ይህ በታሪክም ሆነ በዘመናት መሀከል በሚፈጠሩ ትርክቶች ሊቀየር የማይችል እውነት እንደሆነ የምታምነው ሀገራችን፤ ለእድገቷ እና ለብልጽግና ጉዞዋ የሶማሊያ ሰላም እና መረጋጋት እጅጉን ጠቃሚ እንደሆነ በመረዳት በአብሮ ማደግ እሳቤ ሀገረ ሶማሊያ ተጠናክራ እንድትቆም በርካታ ጥረቶችን ስታደርግ ኖራለች፡፡
እ.ኤ.አ 1991 ዓ.ም ከሶማሊያ መንግስት መፍረስ በኋላ ሶማሊያ ዳግም ወደ ሰላም እንድትመጣ ለማድረግ እና የሀገረ መንግስት ህልውናዋ ተረጋግጦ በሁለት እግሯ መቆም እንድትችል በወንድማዊ አጋርነት ኢትዮጵያ በርካታ ጥረቶችን ስታደርግ ኖራለች፡፡
በተለይም በሶማሊያ ከተፈጠረው የእርስ በርስ ጦርነቱ ማግስት የተሰደዱ ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ እና መጠለያ እንዲያገኙ በማድረግ፣ የሶማሊያን መንግስታዊ ህልውና መልሶ ለማጠናከር የሚደረጉ ውይይቶችን በማመቻቸት፣ በማስተባበርና በመደገፍ ያላሰለሰ ጥረቶችን ስታደርግ እንደኖረች ዘመን የማይሽረው ሀቅ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከፖለቲካዊ ጥረቶች በዘለለ ሀገራችን ኢትዮጵያ የሶማሊያ ሰላም እና አንድነት ለማረጋገጥ የውድ ልጆቿን ደም ጭምር በመገበር ገደብ የለሽ አጋርነቷን አሳይታለች፡፡
ሌላው ሊታወቅ የሚገባው እውነት የሶማሊ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሕዝብ ሀገራችን በምትከተለው ህብረብሔራዊ ፌደራል ስርዓት ከሌሎች ወንድም ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጋር ፍትሓዊ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶቹና ጥቅሞቹ ተከብሮ ለሁሉም ኢትጵያዊያን የምትምች ዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ብልፅግና የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በኀብር ሀገሩን እየገነባ የሚገኝ መሆኑ ነው።
እውነታው ይሄ ሆኖ ሳለ በቅርብ ጊዜያት በሀገረ ሶማሊያ ፕሬዚዳንት እየተሰጡ ያሉ መግለጫዎች እና ንግግሮች እጅግ ከእውነታው የራቁ፣ የሁለቱን ሕዝቦች የትስስር ታሪክ የማይመጥኑ፣ መሬት ላይ ያለውን ሀቅ የሚክዱ፣ የሁለቱን ሀገራት ሕዝቦች መልካም ጉርብትና የጋራ ጥቅም ጋር የሚፃረሩ እንደሆነ ለመታዘብ ችለናል፡፡
ሁሌም ቢሆን ኃላፊነት ከሚሰማቸው ፖለቲከኞች የሚነገሩ ንግግሮች ለቀጣናው ሀገራት ሕዝቦች ፍትሓዊና ዘላቂ ጥቅም የሚመጥኑ፣ የወንድማማችነት እና እህትማማችነት ትስስር የሚያጠናክሩ እና የሶማሌ ህዝብ ዋነኛ ተዋናይ የሆነበት የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት የሚጠቅሙ መሆን አለባቸው፡፡
የሶማሊያ ልሂቃን እና መላው ሕዝብም ቀጣይ እጣ ፈንታቸው በከፍተኛ ደረጃ የተቆራኘውን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የሚያሻክሩ እንዲሁም የቀጣናውን ሕዝቦች ዘላቂ ጥቅሞች የሚፃረሩ አካሄዶች እና ንግግሮች እንዲቆሙ የድርሻችሁን እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
የኢትዮጵያ መንግስትም እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለጋራ ተጠቃሚነት፣ ለመልካም ጉርብትናና ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት አዎንታዊ ሚናውን አጠናክሮ ለመቀጠልና ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት ሁሌም ዝግጁ መሆኑን ላረጋግጥ እወዳለሁ፡፡
Good Morning #Ethiopiaዬ : አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታደርግ ከግብጽ ጉቦ የተቀበሉት ሴናተር ቦብ ሜነንዴዝ መጨረሻ ምን ሆነ?
በዋሸንግተን ፖለቲካ ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑት ሜነንዴዝ ከግብጽ እና ኳታር ጉቦ መቀበላቸው ተረጋግጧል እኝህ ጉምቱ ፖለቲከኛ የፊታችን ጥቅምት ወር ላይ የእድሜ ልክ እስር እንደሚተላለፍባቸው ይጠበቃል
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታደርግ ከግብጽ ጉቦ የተቀበሉት ሴናተር ቦብ ሜነንዴዝ መጨረሻ ምን ሆነ?
ቦብ ሜነንዴዝ ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ የነበሩ ሲሆን አሁን ላይ የሀገሪቱ ህግ አውጪ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው፡፡
የዘር ሀረጋቸው ከኩባ የሚመዘዘው ሜነንዴዝ ዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤትን ከመቀላቀላቸው በፊት የኒው ጀርሲዋ ዩኒየን ሲቲን በከንቲባነት መርተዋል፡፡
እኝህ ጉምቱ ፖለቲከኛ በፈረንጆቹ 2020 ላይ የወቅቱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አድርገዋል ተብሏል፡፡
እንደ አሜሪካ ድምጽ ዘገባ ከሆነ ፖለቲከኛው ይህን ያደረጉት ከግብጽ ባለስልጣናት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ጉቦ ከተቀበሉ በኋላ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መሪዎች በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሶስትዮሽ ውይይት በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን የወቅቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ውይይት ወደ ዋሸንግተን እንዲመጣ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡ በዋሸንግተን በተደረጉት ተከታታይ የሶስትዮሽ ድርድር ላይ ኢትዮጵያ በጫና ወደ ስምምነት እንድትመጣ ግፊት ሲደረግ እንደነበር እና ኢትዮጵያ ስምምነቱን አልፈርምም በሚል አቋሟ መጽናቷን በወቅቱ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ አውጥቶም ነበር፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ፖለቲከኛው ከግብጽ እና ኳታር ኩባንያዎች ጋር ጥቅም ትስስር በመፍጠር ያልተገባ ገንዘብ ተከፍሏቸዋል የተባለ ሲሆን የሀገሪቱ ፍትህ ተቋማት ባደረጉት ምርመራ ሜነንዴዝ በጉቦ መቀበል፣ በፍትህ ማዛባት እና ሌሎችም ወንጀሎች ጥፋተኛ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡
ይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ፍርድ ቤት በፖለቲከኛው ላይ የእስር እና ሌሎች ቅጣት ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅምት ቀጠሮ ይዟል፡፡
ሴናተር ቦብ ሜነንዴዝ ጥፋተኛ መሆናቸውን ተከትሎ የስልጣን ጊዜው እየተጠናቀቀ ካለው የምክር ቤት አባልነታቸው በነገው ዕለት በይፋ እንደሚነሱ ኒዮርክ ታየምስ ዘግቧል፡፡
እንደ ዘገባው ከሆነ ሴናተሩ የኒው ጀርሲ ህዝብን ወክለው የአሜሪካ ምክር ቤት አባልነታቸው በይፋ የሚያበቃ ሲሆን በምትካቸውም ፊል መርፊ እስከ ቀጣዩ ጥር ወር ድረስ እንደሚተኳቸው ተገልጿል፡፡
በቀጣይ ሕዳር ከሚደረገው ምርጫ ዝርዝር ውስጥም ፓርቲያቸው ዲሞክራት ፓርቲ በቦብ ሜኔንዴዝ ምትክ ሌላ እጩ እንደሚያዘጋጅም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡
ሴናተር ቦብ በቀጣይ ጥቅምት ወር ላይ ፍርድ ቤት ቀርበው በፈጸሟቸው ወንጀሎች ላይ የሚተላለፍባቸውን ፍርድ ይቀበላሉ የተባለ ሲሆን የእድሜ ልክ እስራት ሊተላለፍባቸው እንደሚችል ይጠበቃል፡፡
+5
የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ወደ ጎን ትቶ በአፈና እና ዘረፋ ላይ የተሰማራው ፅንፈኛ ቡድን ተደመሰሰ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 12 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮማንዶ ክፍለ ጦር በሰሜን ሸዋ ዞን ለሰላም አልገዛም ያለውን ፅንፈኛ ሀይል መደምሰሱን የክፍለ ጦሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ሞሲሳ ቶለሳ አስታውቀዋል፡፡
አበሞጃና ወይራ ወረዳ ጣርማ በር ቀበሌ እንዲሁም በሞረትና ጅሩ ወረዳ እየተሹለከለከ ህዝብን ሰለም በመንሳት ሲዘርፍና ሲያፍን በነበረው ፅንፈኛ ሀይል ላይ ክፍለ ጦሩ በወሰደው እርምጃ በርካቶች ሲደመሰሱ ቀሪው ሀይል መማረኩን አዛዡ ተናግረዋል፡፡
በዚህ ዘመቻ
• የተገደለ ጠላት 111
• የቆሰለ ጠላት 37
• የተማረከ ጠላት 20
• የተማረከ መሳሪያ ለውንቸር 01
• ብሬን 03
• ክላሽ 34
• ኋላ ቀር መሳሪያ 18
• መገናኛ ራዲዮ 01
• የዲሽቃ ጥይት 60 በቁጥጥር ስር ውሏል።
ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ፀንታ ትቀጥላለች ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ሞሲሳ ቶለሳ በሁለቱም ወረዳዎች ፅንፈኛው ሀይል አከርካሪው ተሰብሮ ከሞትና መቁሰል ያመለጠው ጥቂት ሀይል በየአቅጣጫው እግሬ አውጭኝ ብሎ የተበታተነ መሆኑን ገልፀው ይህም የሰላም ዋጋ እስኪገባው ድረስ ተከታትለን የሚገባውን ቅጣት እንሰጠዋለን ብለዋል፡፡
ዘጋቢ አብዱራህማን ሀሰን
ፎቶግራፍ አብዱራህማን ሀሰን
ትላንት የተደረጉ ጨዋታዎች
🏴 በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
ኢፕስዊች 0-2 ሊቨርፑል
አርሰናል 2-0 ወልቭስ
ኤቨርተን 0-3 ብራይተን
ኒውካስትል 1-0 ሳውዛሃፕተን
ኖቲንግሃም 1-1 ከ በርንማውዝ
ዌስትሃም 1-2 አስቶን ቪላ
🇪🇸 በስፔን ላሊጋ
ኦሳሱና 1-1 ሌጋኔስ
ቫሌንሲያ 1-2 ባርሴሎና
🇫🇷 በፈረንሳይ ሊግ ኧ
ብሬስት 1-5 ማርሴ
ሬምስ 0-2 ሊል
ሞናኮ 1-0 ኢቴይን
🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ
ጀኖዋ 2-2 ኢንተር
ፓርማ 1-1 ፊዮረንትና
ኤሲ ሚላን 2-2 ቶሪኖ
ኢምፖሊ 0-0 ሞንዛ
🇸🇦በሳውዲ ሱፐር ካፕ ፍፃሜ
አል ናስር 1-4 አል ሂላል
+9
ይህ በሰላ ድንጋይ በኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ በቀይ ለባሾቹ በሁለት ሻምበል ብቻ የተሰራ ጀብዱ ነው። አዳሜ ቀረርቶና ፉከራው በሚዲያ ሌላ ነው የተግባር ሜዳው ግን ይህንን ይመስላል። ቀይ ለባሾቹ በሰሜን ሸዋና በደቡብ ወሎ ድንበር በዝንጀሮ ገደልና አንቱቴ የነበረውን የፅንፈኛውን ካምፕ ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ የቀረው እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል። እኔ ምለው ግን ይህ ፋኖ የሚባለው ጡሩንባ ዩኒት የቀረርቶና የምላስ ጉራ ሚሳኤል ነው እንዴ የታጠቀው ይገርማል እኮ ቂቂቂቂቂቂቂቂቂቂ🙏🇪🇹🙏
ለሶማሊያ ህዝብ ሰላም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ትልቅ መስዋዕትነትን ከፍሏል።
ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
ለጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ህዝብ ሰላም ሲባል የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ትልቅ መስዋዕትነት መክፈሉን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለፁ።
ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ በአፍሪካ ህብረት ተልእኮ ሶማሊያ በአትሚስ ጥላ ስር ግዳጁን በስኬት ለተወጣው አንድ ሻለቃ ጦርና ከ368 ኪሎ ሜትር በላይ በእግር በመጓዝ ንብረትና ትጥቆችን በቅልፈት እጀባ በማጓጓዝ ግዳጅ ለፈፀሙ የሰራዊት ክፍሎች አቀባበል አድርገዋል።
በሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞን ፈርፈር ወረዳ በተደረገው የአቀባበል ሥነሥርዓት ላይ የተገኙት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመከላከያ ሰራዊታችን የሶማሊያን ሰላም ለማረጋጋት ለበርካታ ዓመታት ዋጋ መክፈሉን አውስተው አሁንም በአፍሪካ ህብረት ተልእኮ በአትሚስ ጥላ ስር ግዳጁን በሚገባ እየተወጣ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከአፍሪካ ህብረት ውሳኔ በፊትና በኋላ ለረዥም ዓመታት ሠራዊቱን ወደ ሶማሊያ በመላክ የሶማሊያን ማህበረሰብ የፀጥታ ችግር በመጋራት ከፍተኛ የሕይወት የደም የላብና የሃብት ዋጋ ከፍሎ የሶማሊያ መንግሥት እንዲረጋጋ ሠርቷል ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሶማሊያ ሕዝብ ከአልሸባብ ጥቃት እንዲጠበቅ ለዓመታት ትግል መደረጉንና ኢትዮጵያ በዚህ ተልዕኮ በገንዘብ የማይተመን ዋጋ መክፈሏንም ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ ይኸን ሁሉ ዓመት ስትታገል የት እንደነበሩ የማይታወቁ ወገኖች ዛሬ ብቅ ብለው ሞታችንን ከሶማሊያ ጋር ያድርገው እያሉን ነው ፤ ከተሳካላቸው አብረን እናያለን፤ ነገር ግን ቀጠናው ላይ ሌላ ችግር ይዘው እንዳይመጡ እኛ የቀጠናው ባለቤቶች ከማንም በላይ የሚያገባን ስለሆነ ዝም ብለን የምንመለከተው ጉዳይ አይኖርምም ብለዋል።
በኛ ጥበቃ ሥር ሆኖ ወደ ሥልጣን የመጣውና ጥበቃ እየተደረገለት የኖረ ሰው ዛሬ ኢትዮጵያን በመካድ ሩጫ ላይ ተጠምዷል ነገር ግን ኢትዮጵያ የከፈለችው ዋጋ ሁሉ ድሮም ለሶማሊያ ሕዝብና ለቀጠናው መረጋጋት እንጂ ለግለሰቦች አይደለምና ለከፈልነው ዋጋ አንፀፀትም ብለዋል።
መሀስ በሚባል ስፍራ የግዳጅ ቆይታ የነበረው
ሻለቃው ከሶማሊያ ህዝብ ጋር መልካም ግንኙነት የፈጠረና የተመሰገነ መሆኑ ያወሱት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አባላቱ በጀግንነት ለፈፀሙት ግዳጅም ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መሠረተ-ልማት በሌላቸውና በፈታኝ የአየር ፀባይ የሚሰጠውን ማንኛውንም ተልዕኮ የሚያሳካ መሆኑንም ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ተናግረዋል።
ሻለቃው ሲገለገልባቸው የነበሩ ትጥቆችንና ንብረቶችን ወደሀገር ቤት በማጓጓዙ ረገድ በዋነኝነት ግዳጅ የተሰጣቸው የምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር አባላት በርካታ ተሽከርካሪዎችን በቅልፈት በማጀብ ከ368 ኪሎ ሜትር በላይ በእግር በመጓዝ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ላከናወኑት ተግባርም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ምስጋና አቅርበዋል።
ትጥቅና ንብረትን ይዞ ለመውጣት ሲታሰብ በጠላት በኩል ዛቻዎች እንደነበሩ ያወሱት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ሰራዊታችን ያለውን ልምድ ተጠቅሞ በጀግንነት ያለአንዳች ችግር የኢትዮጵያን ንብረት ይዞ መመለሱን ተናግረዋል።
በዚህ ስኬታማ እንቅስቃሴ ላይ ለተካፈሉት ለኢፌዴሪ አየር ኃይል ፣ ለሎጀስቲክስና መሐንዲስ ዋና መምሪያዎች ፣ ለተለያዩ የሰራዊት ክፍሎች ፣ ለሶማሌ ክልል የፀጥታና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ለሀገር ሽማግሌዎችና ለማህበረሰቡ ምስጋና አቅርበዋል።
በመርሀግብሩ ላይ ጄነራል መኮንኖች የምስራቅ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ተሰማ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ኮምሽነር አብዲ ዓሊና የፈርፈር ወረዳ መስተዳድር አካላትና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ አብዮት ዋሚ
ፎቶግራፍ ምስጋናው ከበደ
‹‹ግብፅ ወታደሮቿን በሶማሊያ ለማሰማራት ያላት ፍላጎት ኢትዮጵያን አያሸብርም›› - ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባይ ነብዩ ተድላ ‹‹ግብፅ ወታደሮቿን ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ በሶማሊያ ለማሰለፍ ያለት ፍላጎት ኢትጵያን እንደአዲስ የሚያሸብር ጉዳይ አይደለም›› ሲሉ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል፡፡
‹‹ሶማሊያ እንደማንኛውም ሉዓላዊ መንግስት የወታደራዊም ሆነ ሎሎች ዓይነት ስምምነቶች ከፈለገችው አገር ጋር የማድረግ መብት አላት ›› ያሉት ቃል አቀባዩ ‹‹ ከዚህ ቀደምም ኢትዮጵያን እና ግብጽን ጨምሮ ከሱዳን፣ ከኡጋንዳ ፤ ከኤምሬትስ፣ ከሳውዲ እና ሌሎች አገራት ጋር ተመሳሳይ ግንኙነቶች ›› የነበሯት መሆኑን በማስታወስ ሰሞንኛው ጉዳይ እንዳ አዲስ መንግስታቸውን የሚያሸብር አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡
በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ የሽግግር ተልዕኮ አትሚስ በተያዘው የ2024 እ.አ.አ. በወርሃ ታህሳስ ተልዕኮውን አጠናቅቆ ለሶማሊያ ብሔራዊ መንግስትና ተቋማት አስረክቦ እንዲወጣ እቅድ እንደነበረ ያስታወሱት ቃል አቀባዩ ‹‹ ነገር ግን ከአልሸባብ መጠናከር ጋር ተያይዞ እቅዱን መከለስ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷልም ›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
ነብዩ አያይዘውም ‹‹ ኢትዮጵያ ወታደር እንዳዋጣ አገር፣ የጸጥታ እና የደህንነት ስጋት እንዳለባት አገር፤ ከ2000 ኪ.ሜ በላይ ድንበር ከሶማሊያ ጋር እንደምትጋራ አገር፣ እንደጎረቤት አገር፣ ድርሻ እንዳለው አገር ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለችው ትገኛለች ›› ብለዋል፡፡
አክለውም ‹‹ በሶማሊያ ውስጥ ለኢትዮጵያ የሰላም፣ የጸጥታ፣ የደህንነት ስጋት እስካለ ድረስ ኢትዮጵያ የማንንም ፈቃድ ሳትጠይቅ አስፈላጊውን እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ የሚያግዳት ጉዳይ አይኖርም ›› ሲሉ ፈርጠም አድርገው ተናግረዋል፡፡
ሰበር‼️
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት እና ፕሬዘዳንቱ ላይ ሕጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠየቀ‼️
👉 በቀረበው ሰነድ ዶክተር አሸብርን ጨምሮ የሥራ አስፈጻሚው ቦርድ አባላት የፈጸሟቸውን በደሎች በዝርዝር ተመልክቷል
👉አቤቱታው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ጥሰትና ምዝበራ መካሄዱን ይገልጻል
👉 ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ያለ እሱ ፍቃድና ዕውቅና እየተቃወመ በግድ ምክትል እንዳደረጉት ተጠቅሷል።
👉 ረ/ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ያለ ምርጫ ለቦርዱ አመራርነት እንድታልፍ መደረጉም ተያይዟል።
በኢትዮጵያ ተመዝግበው ያሉ ሕጋዊ የስፖርት ፌዴሬሽኖች በሕጋዊ ወኪል ጠበቆቻቸው አማካኝነት፤ በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት እና ስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት ላይ አስዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ የሚጠይቅ ሰነድ በዛሬው ዕለት ለኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚንስቴር አስገብተዋል።
አቤቱታ አቅራቢ ፌዴሬሽኖቹ በሰነዳቸው ላይ ካቀረቧቸው ምክንያቶች መሐል፦
👉ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ኮሚቴው ከፌዴሬሽኖቹ እውቅና ውጪ በድብቅ ጥሪ ተደርጎ በድብቅ የተፈጸመ ስብሰባ ማካሄዱን ይገልጻል።
👉አቤቱታ አቅራቢ ፌዴሬሽኖች ባልተጠሩበት፤ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ/ም በተደረገ ሕገወጥ የኦሎምፒክ ኮሚቴ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት ምርጫ፤ ኮሚቴ ለሚፈልጋቸው ጥቂት አባላት ብቻ ጥሪ በማድረግ፤ መተዳደሪያ ደንቡ የማይፈቅድላቸውን በድምፅም ሆና ያለ ድምፅ የጠቅላላ ጉባኤው አባል ያልሆኑ ግለሰቦችን የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴ አድርገዋቸዋል።
👉 ከዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ጋር የጥቅም ግንኙነት አላቸው ያሏቸውን የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ጥበቡ ቸኮልን ኮሚቴው አስመራጭ በማድረግ ሕግ ተላልፏል ሲል በአቤቱታው ላይ ያስነብባል።
👉አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ዕውቅና እና ፍቃድ ድርጊቱን እየተቃወመ በሕገ ወጥ ምርጫው ላይ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ተደርርጓል የሚል አቤቱታም ይገኝበታል።
👉የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት በጠቅላላ ጉባኤው ምርጫና አብላጫ ድምፅ እንደሚመረጡ መተዳደሪያ ደንቡ የሚደነግግ ቢሆንም ረ/ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ያለ ምርጫ እንድታልፍ መደረጉን በሰንዱ ተብራርቷል።
👉ለኮሚቴው ከረጂ ተቋማት የተሰበሰበ ከ300,000,000.00 (ከሦስት መቶ ሚልየን ብር) በላይ ምን ላይ እንደዋለ በኦዲት ሪፖርት እንደማያውቁት አቤቱታ አቅራቢዎቹ በሰነዱ ላይ ገልጸው በተጨማሪም ከስፖንሰር አድራጊዎች የተገኙ በውጭ ምንዛሪ ገቢ የተደረጉ ገንዘቦች ምን ላይ እንደዋሉ የሙያሳይ ግልጽ የኦዲት ሪፖርት አለመደረጉን አቤቱታ አቅራቢዎቹ ጨምረው ዘርዝረዋል።
👉ሰነዱ የአትሌት ገዘኸኝ አበራንም ጉዳይም አያይዞታል።
👉 በአትሌቶች አመራረጥ ላይ ተደርጓል ስለተባለው አድሏዊ አሠራርም ተካቷል።
👉ለአገር ክብር ምልክት ከሆኑ አትሌቶች ይልቅ የአመራሮቹ ዘመድ አዝማዶች አገር ወክለው እንዲሄዱ መደረጉም ተነሥቷል።
👉 ሰነዱ የሥራ አስፈጻሚው ቦርድ አባላት የቅርብ ዘመዶች በኮሚቴው ያለ አግባብ ቅጥር እንዲፈጸምላቸው በማድረግ ምንም ዓይነት ሥራ ሳይፈጽሙ ገንዘብ በመመዝበር በርካታ የፋይናንስ ጥሰት መደረጉን ጨምሮ ይገልጻል።
እነዚህን እና ሌሎችንም አቤቱታዎች ያቀረቡት ፌዴሬሽኖች
👉ኮሚቴው አሻሻልኩት ያለው መተዳደሪያ ደንብ እንዲታገድ፤
👉ሰኔ 4 ተደረገ የተባለው ሕገ ወጥ ምርጫ እንዳልተደረገ ተደርጎ ቀሪ እንዲደረግላቸው፤
👉የተፈጸሙት ተግባራት ከባድ የሆነ የዲሲፕሊን ጥፋት ውጤት በመኾናቸው ቦርዱ ከኃላፊነት ታግዶ እንዲቆይ
👉 በገለልተኛ ኦዲተር ምርመራ እንዲደረግ፤ በመጠየቅ
👉ሚንስቴር መሥሪያ ቤቱ አስተዳደራዊ ርምጃ እንዲወሰድላቸው አቤቱታ አቅራቢዎቹ ጠይቀዋል።
ATTENTION ‼️
በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት ናዳ ምክንያት ብዙ ወገኖቻችን ጉዳት ደርስባቿል ሁላችንም ባለን አቅም ወደ 8091 የተቻለውን የገንዘብ መጠን በመላክ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖቻችንን እንደግፍ ።
ሁላችንም የቻልነውን መጠን እናግዝ🙏
ስፖርትና ውትድርና
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም
ውትድርና የአያሌ እውቀትና ቴክኖሎጂዎች መፍለቂያ እንደሆነ ሁሉ ሁለንተናዊ ጠቀሜታቸው እጅግ ከፍተኛ የሆኑ የተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች መገኛም የውትድርናው ሙያ አውድ ነው፡፡ ለአብነት በዓለም የስፖርት አፍቃሪያን በእጅጉ ተወዳጅ የሆኑት የእግር ኳስና የአትሌቲክስ ስፖርቶች መፈጠሪያቸው በዚሁ ወታደራዊ ሙያ ዘርፍ ነው፡፡
ስፖርት ለውትድርና ሙያ ወይም ለሠራዊት አካላዊና ሥነ-አዕምሯዊ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ ያክል የሠራዊቱን ውስጣዊ ግንኙነትና አንድነት በማጠናከር የክፍል ፍቅርና የጋራ ሥነ-ልቦናን የመፍጠር ፋይዳው እጅግ የላቀ ነው፡፡
ስፖርት ጤናማና ብቁ ዜጋን ሲፈጥር የልማት መሣሪያ ይሆናል፤ ሰላምን፣ የሕዝቦች አንድነትና ፍቅርን ሲያሰፍን ደግሞ ለልማት የተመቻቸ ሁኔታን የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡ በሌላ መልኩ ልማትና እድገት ከሌለ ስፖርቱን የትም ማድረስ አይቻልም ማለት ነው፡፡ ቴክኖሎጂ፣ ጥሩ አሠልጣኝ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ ሰፋፊ የስፖርት ማዘዎተሪያዎች፣ የተሟላ ትጥቅ እና የተመጣጠነ በቂ ምግብ ወጣቱ እንዲያገኝ አድርጎ ለማብቃት በቂ ገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም የስፖርት እድገት የዘመናዊ ስፖርት ኢንዱስትሪ የሚጠይቀውን በማሟላት የሚሳካ ነው፡፡ እዚህ ላይ ጠንካራ ማኅበራዊ መሠረት ያላቸው ደጋፊዎች ሚና ዓይተኛ እና አይተኬ ነው፡፡
መቻል የሠራዊታችን ሞራልና ሥነ-ልቦና ግንባታ አንዱ መሣሪያ ከመሆን ባሻገር የክፍል ፍቅርና ውስጣዊ አንድነት በማጠናከር ረገድ ዓይነተኛ ፋይዳ ያለው ክለባችን ነው፡፡ የሠራዊታችን የአሸናፊነት ምልክት የሆነው አንጋፋው የመቻል ስፖርት ክለብ የምሥረታውን 80ኛ ዓመት"መቻል ለኢትዮጵያ!" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች በደማቅ ሁኔታ እያከበረ ይገኛል፡፡
"መቻል ለኢትዮጵያ!" የሚለውን መሪ-ሃሳብ የያዝነው መቻል አንድ ብሔር ወይም አካባቢ የሚወክል ክለብ ካለመሆኑ በተጨማሪ የመላው ኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ ልጆች ያሉበት ለሀገራችን ኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብርና ጥቅም ብሎም ለሕዝብ ደኅንነትና ሉዓላዊነት የቆመውን መከላከያ ሠራዊት በታላቅ ገድሉ የገዘፈ ስብዕናን በመወከል የሚጫወት ክለብ ስለሆነ ጭምር ነው፡፡
ይህን ታሪካዊ ሁነት ተከትሎ መቻል በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ከአፍሪካ ምርጥ አሥር ክለቦች አንዱ ሆኖ ለመገኘት ራዕይ ይዞ ከመትጋት ባሻገር ውትድርና የምርጥ ስፖርተኛ መፍለቂያ እና የሞራል ግንባታ መሠረት እንዲሆን የሚሠራ፤ ለሀገራችን ዘመናዊ ስፖርት ዕድገት አዎንታዊ አስተዋፅኦ የሚያበረክት፤ ለተቋማችን በስፖርቱ መስክ የገፅታ ግንባታን እንዲሠራም ተልዕኮ ተቀብሎ እየተጋ ይገኛል፡፡
የመቻል ስፖርት ክለብ ዋነኛ ዓላማ የሀገሩን፣ የተቋሙንና የራሱንም ታሪክ በሚመጥን ደረጃ በመጪው ጊዜ የስፖርት ክለቡን የዕድገት መሠረት መጣል ሲሆን ይህን እውን ለማድረግ ሲንቀሳቀስ በተለይ በዚህ ሁነት የመቻል የስፖርት ክለብን እውቅና ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር፤ ለክለቡ ዕድገት መሠረት የሚጥል ገቢ ማሰባሰብና ጠንካራ መሠረት ያለው ድጋፊ እንዲኖረው ማድረግ የሚያስችል ተግባር መፈፀምን ግብ አድርጎ ይሠራል፡፡
በከፍተኛ ትኩረት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከልም የጎዳና ላይ ሩጫ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ክለቦችን ያሳተፈ የእግር ኳስ ውድድር፣ የመቻል ስፖርት ክለብን ታሪካዊ ዳራና የወደፊት ራዕይ መላው ሠራዊታችን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚገባ እንዲገነዘበው ማድረግ እንዲሁም ይህን ሀገራዊ ስም ይዞ የተነሳ ታላቅ የስፖርት ክለብ ሕዝባችን ተረድቶትና አውቆት በየእኔነት ስሜት እንዲደግፈው ማድረግ የበዓሉ ቁልፍ የትኩረት ነጥቦች ናቸው፡፡
በእነዚህና በሌሎች ተግባራት በሚገኘው ገቢም የስፖርት ክለቡን ለማዘመን ወይም ለማሳደግ አበክሮ ይሠራበታል፡፡ መቻል ስፖርት ክለብ የስፖርት መሠረተ ልማቶች የተሟሉለት ክለብ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ በዚህም ክለቡ የራሱ የስፖርት ማዘውተሪያና የውድድር ሜዳ እንዲኖረው የሚደረግ ሲሆን የስፖርት ኮሌጅ ወይም አካዳሚ በመገንባት የክለቡንም ሆነ የኢትዮጵያን ዘመናዊ ስፖርት በማሳደግ ደረጃ ከፍተኛ ሚና ያለው ተግባር ይፈፀማል፡፡
ስለሆነም ይህ ታላቅና አንጋፋ ክለብ ስሙንና የወከለውን የታላቅ ሀገር ጀግና ሠራዊት የሚመጥን ደረጃ ላይ እንዲገኝ ራዕዩንና ዓላማውን እውን ማድረግ የሚያስችል ሁለንተናዊ ድጋፍ ለማድረግ ሁላችንም በንቃት መሳተፍ ይጠበቅብናል፡፡
የመቻል ስፖርት ክለብ 80ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓል መቻል ለ ኢትዮጵያ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
የሚኒስትሮች ም/ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 34ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ምክር ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈባቸው ጉዳዮች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ላይ ነው፡፡ የ2017 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት በጀት የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነውን የ2016-2018 የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊስካል ማዕቀፍን ማስፈጸም እንዲቻል በሚያደርግ መልኩ ፤ የ2016 የፌደራል መንግስትን የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፤ የመንግስት የፋይናንስ አቅም እና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልኮና ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በመገምገም እንዲዘጋጅ ተደርጓል፡፡
በዚሁ መሰረት ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣ ለካፒታል ወጪዎች ፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ እና ተጠባባቂ ወጪን ጨምሮ ወደ አንድ ትሪሊየን የሚጠጋ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2017 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የአረንጓዴ አሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያ እና አስተዳደሩን ለመወሰን የወጣ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በአረንጓዴ አሻራ የተጀመሩ ሰፊ ሥራዎች ቀጣይነትን ለማረጋገጥ፣ ሀገራችን ካላት የቆዳ ስፋት ከግማሽ በላይ የሆነው የተጎሳቆለ መሬት እንዲያገግም ለማድረግ፣ የደን ዘርፉ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዲሰጥ ለማስቻል፣ በአሁኑ ወቅት በተበጣጠሰ መልኩ በፌዴራል መንግስትም ሆነ በክልል መንግስታት ፋይናንስ እየተደረገ እየተሰራ የሚገኘውን የአረንጓዴ አሻራ ልማት በተቀናጀና ተገቢውን ሀብት መመደብ በሚያስችል የፋይናንስ አሰራር ስርዓት መደገፍ አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት የአረንጓዴ አሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድን ማቋቋሚያ እና አስተዳደሩን ለመወሰን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ተቋማት ለሚሰጧቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን በቀረቡ ረቂቅ ደንቦች ላይ ነው፡፡ ተቋማቱ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች፣ አሰራሮችና የሰለጠነ የሰው ሀይል በማዘመን የአገልግሎት አሰጣጣቸውን የጥራት ደረጃ ማሻሻል ብሎም የተጠቃሚውን ማህበረሰብ አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት ለመስጠት እንዲችሉ የሚያስችል ስርአት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ ደንቦቹ ተዘጋጅተው ቀርበዋል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውሉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
