የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 400
المشتركون
-22624 ساعات
-2 2007 أيام
-2 65830 أيام
أرشيف المشاركات
#Ethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢንጂነር አይሻ መሀመድ እና ዶ/ር አብርሃም በላይን የስልጣን ቦታ ቀያየሩ።
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ሰጥተዋል።
በዚህም ፦
1. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣
2. ዶ/ር አብረሃም በላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣
3. ዶ/ር መሀመድ እንድሪስ ደግሞ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አድርገው ሾመዋቸዋል።
ኢ/ር አይሻ መሀመድ በ2011 ዓ/ም የመጀመሪያዋ ሴት የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ በኃላ 6 ወር እንዳገለገሉ ከቦታው ተነስተዋል።
ዶ/ር አብርሃም በ2014 ነበር የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት።
ዶ/ር አብርሃም በላይ የአሁኑ ሹመት እስኪሰጥ ድረስ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴርን በሚኒስትርነት እያገለገሉ የነበሩ ሲሆን አሁን በኢ/ር አይሻ መሀመድ ተተክተው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ሆነዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከሎች የተሰጣቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እየተወጡ እንደሚገኙ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 09 ቀን 2016 ዓ.ም
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል አሰልጥኖ ባስመረቃቸው 42ኛ ዙር የኮማንዶ አባላት ምረቃ የዕዙ የማሰልጠኛ ማዕከላት እንቅስቃሴን አብራርተዋል።
የኮማንዶ ፣ የአየር ወለድ ፣ የፀረ-ሽብር ፣ የልዩ ሀይል እና የአመራር ትምህርት ቤቶች ከባቢያዊና አለም አቀፉዊ ሁኔታን ባገናዘበ መልኩ ለሀገራችን ሰላምና ደህንነት እንዲሁም ለተቋማዊ ሪፎርሙ የማይተካ ሚናን እየተጫወቱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
የኮማንዶና የአየር ወለድ ዕዝ በስሩ የሚገኙ የስልጠና ማዕከሎች በቀጣይነት አቅማቸውን ለማሳደግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት አዛዡ ፣ ዕዙ የአሰልጣኞችን አቅም ለማሳደግ ወደ ተለያዩ ወዳጅ ሀገራት ልኮ እያሰለጠነና በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ካላቸው ሀገራትም አሰልጣኞችን በማስመጣት የልምድ ልውውጥ እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ለአየር ወለድና ለፀረ ሽብር ማሰልጠኛ ማዕከሎች በአካልና በአስተሳሰብ ብቁ የሆኑ ወታደሮችን እያፈራ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ የፀጥታ አካላትን የማብቃት ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል አዛዥ ኮሎኔል ቦጃ አጋ በምረቃው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የዘንድሮ ተመራቂዎች ለየት የሚያደርጋቸው ሰራዊታችን ያሳለፋቸው የውጊያ ውሎዎች ልምድና ተሞክሮ ተቀምሮ በተሻሻለ የስልጠና ካሪኩለም መሰልጠናቸው መሆኑን ተናግረው፣ ተመራቂ ኮማንዶዎቹ ለረጅም ወራት በስልጠና መቆየታቸውን ገልፀዋል።
በማዕከሉ የሚሰጡ ስልጠናዎች በአካል ብቃትና በወታደራዊ አቅም የጎለበቱ ወታደሮች ከማፍራቱ በተጨማሪ ሀገር ወዳድና ፕሮፌሽናል ኮማንዶዎችን ለማፍራት በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤት መገኘቱንም ጠቁመዋል።
ተመራቂዎች በማዕከሉ በነበራቸው ቆይታ ባገኙት አቅም ማንኛውንም ግዳጅ ለመወጣት እንደሚያስችላቸው የገለፁት ኮሎኔል ቦጃ አጋ ፣ ሰልጣኞች ስለሀገራቸው በጥልቀት እንዲያውቁና አንድነታቸው እንዲጠናከር በአስተሳሰብና በባህሪ ቀረፃ ላይ በትኩረት መሰራቱን ገልፀዋል።
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ኢትዮጵያ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና ከመከላከያ ሠራዊቱ ፣ ከባህር ሀይልና ከፌዴራል ፖሊስ የተውጣጡና ለረጅም ወራት የሰለጠኑ የኮማንዶ አባላትን የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙና ከፍተኛ የሠራዊቱ አመራሮች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት አስመርቋል።
ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ
+5
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ለ42ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ኮማንዶዎችን እያስመረቀ ነው
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ለ42ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ኮማንዶዎች በብላቴ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ማስልጠኛ ማዕከል እያስመረቀ ይገኛል፡፡
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል ከፍተኛ የሠራዊቱ አመራሮች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂዎቹ “ኢትዮጵያ” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው እና ከመከላከያ ሠራዊቱ ፣ ከባህር ኃይል እና ከፌዴራል ፖሊስ ተውጣጥተው ለረጅም ወራት የሰለጠኑ የኮማንዶ አባላት መሆናቸው ታውቋል።
በዝግጅቱ ላይ ተመራቂዎች የተለያዩ ወታደራዊ ትዕይንት የሚያሳዩ ሲሆን፣ በእለቱ የክብር እንግዳ እና በኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ንግግር እንደሚደረግ ከመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
👇👇👇👇👇👇👇 subscrib አድርጉን ❤🙏🇪🇹❤🙏
https://www.youtube.com/@Commando_1998
"ስለ ኢትዮጵያ እስከሆነ ከጸሃይ በታች አንዳች
የሚበግረው እንደሌለ ያስመሰከረ ነው"
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም
ያልተሸረበበት የተንኮል ጥግ የለም።ያልወረደበት የሃሰት ናዳም እንዲሁ።
ጉዳዩ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ሆነና ምኞት ወለድ ሆኖ እንዲቀር እውነት አስገደደ እንጂ።
እሱ ላይ የተሞከሩ የክፋት ወጀቦች በአንዳንድ ሀገራት መዓት ጣጣ ፈጥሮባቸው...... ሀገረ-መንግስታዊ ቅስማቸውን ሰብሮ፣ ዜጋ አስበትኖ፣ሰላም እንደ ሰማይ አስርቆ፣ ሰንደቅ አስወርዶ፣በድሮ ናፋቂነት ብርድ ያስመታቸውን ሀገራት እኛን ደጅ ጠንተው ሲጠለሉ አይተናል።
በእውነት ሚዛን ላይ የቆመ፣ራስ አስቻይ ሀቅን የተንተራሰ፣ ስሜት የማይንጠው፣ብስለት የሚመራው፣ አሁናዊ ዝማኔን ከዓለማዊ ቴክኖሎጂ ወለድ ተለዋዋጭ አውድ ያስማማ፣ከባቢን ቃኝቶ፣አህጉር ተመልክቶ፣ ዓለምን በዳሰሰ አመክንዮ ተልቆ ሀገር የማተለቅ ብርሃናማ ተቋማዊ ሃሳብ ተግባሩን ለማጨለም ያልተሞከረ የደንቃራ መዓት እና ሟርት ባይኖርም፤እሱ ግን የስኬት ካባ ደርቦ ነበር።አለ።ይኖራል።የሀገሬ የሀገራችሁ ጀግናው ወታደር።
የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም አማታሪው፣ፈተናን ወደ ዕድል ቀያሪው፣የትኛውንም አስቸጋሪ ጋሬጣና መሰናክል በማይበርድ የጋለ የሀገር ፍቅር እና ሞያዊ ዲሲፕሊን ብሎም ተዓምራዊ ጀግንነት በድል ጥሶ የሚረማመደው የኢትዮጵያ ወታደር ሀገር የማጽናት ታሪካዊ ሃላፊነቱንና ትውልዳዊ አደራውን የመወጣት ሂደቱ በውል ሲጤን የባላንጣዎቹ ድብቅ መሻት እርቃኑን ፈጦ ይታያል።
ጸንቶ ኢትዮጵያን በማጽናት ጀግንነታዊ ተጋድሎው ስለ ጋራ ሀገራችን አንድነትና ሰላም ሲል ስለሚከፍነው መስዋዕትነት ቅንጣት አለማቅማማቱ ሲታሰብ የጽናቱ ጥግ ድረስ መሆን በእጅጉ ይደንቃል።
እንደወርቅ በእሳት በተፈተነ ቁጥር በግርማ ሞገስ ከፍ ብሎ፣በድል ደምቆ፣በአሸናፊነት እንዲያንጸባርቅ የሚያደርገው መቼም የማያወላዳው የጋለ የሀገር ፍቅሩ መሆኑ ለሰከንድ አያጠራጥርም።
ለሀገር ኩራት አለኝታው የኢፌዲሪ መከላከያው ጀግና ወታደር አድናቆትና አክብሮት ያለው ህዝብ እልፍ አዕላፍ ነውና ለጥቂቶች ጫጫታ ፊት የሚሰጥ ማንነት ስለሌለው ኢትዮጵያን ከነ ሰንደቋ በልቡ አትሞ ስለ ክብሯ ይዋደቃል።
በበረታ ፈተና በእሳት መካከል በድል እየተረማመደ፣ ሀገር ወዳድ ቅን የሆነ ዜጋን ሁሉ እያኮራ፣በገዛ ሀገራቸው አሟራች ለሆኑ ኢትዮጵያ ጠል ባላንጣዎች የማይቆረጠም የብረት ቆሎ እንደሆነ የቀጠለ የሚቀጥልም ነውና እሱን መረታት ከቶውንም የሚቻል አይደለም።
በየዘመናት የትውልድ ቅብብሎሽ እሱ ዘንድ በመስዋዕትነት የደረሰችን ኢትዮጵያ ከነሙሉ ክብሯ ለቀጣዩ ትውልድ በኩራት የማሻገር ጀግናዬ ስለ ኢትዮጵያ እስከሆነ ከጸሃይ በታች የሚበግረው አንዳችም ሃይል እንደሌለ ያለፈባቸው በብርቱ መስዋዕትነት በድል ያደመቃቸው መንገዶቹ ህያው ምስክር ናቸው።
በአስቻለው ሌንጫ
"የሰሜን ሸዋ ዞን እና የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አመራሮች እና የፀጥታ ሀይሉ ጋር በጋራ በመሆን በተሰራ ስራ የተሻለ ውጤት ማምጣት መቻሉን ብርጋዴር ጀነራል አበባው ሰይድ ተናገሩ "።
ጀነራል አበባው ታደሰ የማእከላዊ ኮማንድፖስት ዋና ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታን ጨምሮ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችና የሰሜን ሸዋዞንና የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አመራሮች በተገኙበት በተሰሩ የሰላም ስራዎች ላይ በከሚሴ ከተማ ገምግመዋል።
ብርጋዲየር ጀነራል አበባው ሰይድ እንደተናገሩት የሁለቱን አጎራባች ዞኖች በጋራ በማድረግ በተደረገ ግምገማ ጥሩ ውጤት የታየ ሲሆን እስካሁን በሁለቱ ዞኖች አስቸግሮ የነበረ የፀጥታና ደህንነት መደፍረስ የሰላም ማስከበር እንቅፋት የሆኑ የሁለቱን ዞኖች የብሄረሰብ ግጭት በማስመሰል ባለፋት ጊዜያት መንገድ እስከመዘጋት ድረስ የሚያደርስ ሁለቱን ብሄረሰብ የማያቋርጥ ግጭት ለማስገባት በሸኔና ፅንፈኞች አለመረጋጋት እንዲፈጠር ሲሰሩ ነበር ያሉት ጀነራሉ በዚህም የሁለቱ ዞኖች አመራሮችና የፀጥታ ሀይሉ ጋር በጋራ በመሆን በተሰራ ስራ የተሻለ ውጤት መምጣት መቻሉን ገልፀዋል።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ እንደገለፁት በተሰጠው አቅጣጫ የሁለቱ ዞን አመራሮች ችግሮችን እንዲፈቱ በተቀመጠው መሰረት በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።በዚህም የሁለቱን ህዝቦች አንድነት ወንድማማችነት ትስስር የሚያጠናክር የቀጠናውን ሰላም ለማምጣት ሊለውጥ የሚችል ስራ መሰራቱን ገልፀው በዚህም በተሰራ የህዝብ ግንኙነት ሰራ ከ62ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማወያየት መቻሉን ገልፀዉ የህግ ማስከበር ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ በበኩላቸው የማእከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት አጠቃላይ በቀጠናው የተሰሩ የህግ ማስከበር ስራዎች በዝርዝር የተገመገመ ሲሆን አቅጣጫ ተቀምጧል በሁለቱ ህዝቦች ጥርጣሬ እንዲፈጠር ሲሰሩ የነበሩ ፅንፈኞ መኖሩን ገልፀዉ ከሁለቱም ዞኖች የአመራር ድክመት መኖሩን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው የሁለቱን አጎራባች ህዝቦች ለመለየት የመሳሪያ ነጋዴዎችና ፅንፈኞች ላይ በተሰራ የህግ ማስከበር በሁለቱም በኩል በተሰራው ስራ ችግሮች እንዲፈቱ አመራር በአዲስ የማደራጀት በተሰራ ስራ የህዝባችን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በትኩረት መሰራቱን ተናግረዋል ።
መረጃው የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ነው።
#UPDATE
ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች።
እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች።
ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።
ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በእስራኤል ላይ እንዲህ ያለውም ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተችው።
ከ360 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን ወደ እስራኤል መወንጨፋቸውን የእስራኤል ሠራዊት አስታውቋል።
አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ (99%) በእስራኤል እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ መደረጋቸው ተገልጿል።
ያም ሆኑ በጥቃቱ መጠነኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።
እስራኤል የለሊቱን ጥቃት ብቻ ለመመከት 1 ቢሊዮን ዶላር ሳታወጣ አልቀረችም ተብሏል።
የአሜሪካ ጦር በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ከአየር ላይ እንዲከሽፉ አድርጓል። ፕሬዜዳንቷም " እስራኤል የኢራንን ጥቃት የመከተችው በአሜሪካ ድጋፍ ነው " ብለዋል።
ዩናይትድ ኪንግደም እና ፈረንሳይም ከጥቃቱ በፊት የአየር ቅኝት በማድረግ እስራኤልን ሲያግዙ አንግተዋል።
ጆርዳን በአየር ክልሏ ሲያልፉ የነበሩ ድሮኖችን እየመታች የጣለች ሲሆን ይህንን " ለህዝቤ ደህንነት ስል ያደረኩት ነው " ብላለች።
ኢራንም ጆርዳንን " አርፈሽ ካልተቀመጥሽ አንቺም ልክ እንደ እስራኤል ትመቻለሽ " ስትል ዝታባታለች።
እስራኤል በቀጣይ የአፀፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን ? የሚለው ብዙዎችን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን " አሜሪካ ተያት አፀፋ አትውሰጂ " ብላታለች።
ቀድሞኑ በእራኤል እና ፍልስጤም ሀማስ ጦርነት የተለያየ አቋም ያላቸው የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል። ውጥረቱ ይረግብ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢራን ፥ እስራኤልን የደበደበችው ከዛሬ 13 ቀን በፊት በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እስራኤል እንደፈፀመችው በምታምነው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጄኔራሏን ጨምሮ አጠቃላይ 13 ሰዎች በመገደላቸው ለሱ አፀፋ ነው።
መረጃው ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የተሰባሰበ ነው።
🚨BREAKING🚨
ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች።
ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል።
እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም ስታደርግ ነበር።
እስራኤልም " እኔ እራሴን ለመከላከል ዝግጁ ነኝ " ስትል ከርማለች።
ገና የእስራኤል እና የፍልስጤም ሀማስ ጦርነት ይህ ነው የተባለ መቋጫ ባላገኘበት ሁኔታ ኢራን እና እስራኤል የለየለት ጦርነት ውስጥ ይገባሉ በሚል ፍራቻ ሀገራት ሲያስጨንቃቸው ቆይቷል።
እንደ አሜሪካ ያሉ የእስራኤል እጅግ ጠንካራ ወዳጅ ሀገራት ኢራንን " አርፈሽ ተቀመጪ ጥቃት እንዳትፈጽሚ " ሲሉ ሲያስጠነቅቁ ነበር።
ዛሬ ለሊቱን በተሰማው ዜና ግን ኢራን እንደዛተች አልቀረችም እስራኤልን በድሮን (ሰው አልባ አውሮፕላን) ማጥቃት ጀምራለች። የሚሳኤል ጥቃትም እንደሚኖር ኢራን ገልጻለች።
እስካሁን ድረስ ከ100 በላይ የድሮን ጥቃቶችን እንደሰነዘረች ተሰምቷል።
የእስራኤል ጦርም የኢራን ድሮኖች ወደ እስራኤል እየተላኩ መሆኑን አረጋግጧል። በትንሹ ከ100 በላይ ድሮኖች የእስራኤል አየር ክልል ሳይደርሱ መከላከል እንደተቻለ ገልጿል።
የአሜሪካ ጦርም እስራኤልን እየተከላከለ ሲሆን እስራኤልን ለማጥቃት የተላኩ ድሮኖችን መቶ መጣሉን አመልክቷል። የዩኬ አየር ኃይልም እስራኤልን እንዲያጠቁ የተላኩ ድሮኖችን መቶ ጥሏል።
እስራኤል ለማንኛውም የኢራን ቀጥተኛ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት እንደተዘጋጀች አሳውቃለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌባኖስ ያለው ሄዝቦላህ በሰሜናዊ እስራኤል የሚሳኤል ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን የየመኑ ሁቲ ደግሞ እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፍቷል።
Must Watch : ከ3 ሳምንት በፊት ፅንፈኛው ሸኝቻቸዋለሁ ያላቸው ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሠይድ ፅንፈኛውን እየሸኙት ነው።
ፅንፈኛው ሸኝቻቸዋለሁ ያላቸው ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሠይድ ፅንፈኛውን እየሸኙት ነው።
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የፅንፈኛውን ቡድን ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂን አኮላሽተናል ሲሉ የዞኑ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢና የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ምክትል አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሰይድ ገልፀዋል፡፡
ባሰበው የጥፋት መንገድ እንዳይጓዝ በማድረግ ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራ በህዝብ ስም የሚነግደው ፅንፈኛ ኃይል ከጠበቀው በላይ ተመትቶ አከርካሪው መሰበሩን ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሰይድ ተናግረዋል።
ይህ ስርዓት አልበኛ ቡድን በህዝቦች መካከል የጥፋት እሳቱን በመጫር የብሔር ግጭት በመቀስቀስ የጥፋት ወላፈኑን በመላው አገሪቱ ለማያያዝ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ይህ እኩይ ህልሙም እንዳይሳካ አድርገን ከነቅዠቱ ቀብረነዋል ብለዋል፡፡
ፅንፈኛው ቡድን ባልዋለበት ሜዳ ሁሉ ራሱን እያዋለ ይህንን ያህል ሠራዊት ደመሰስኩ፣ ሠራዊቱ ያልታጠቀውን መሳሪያ ሳይቀር ማረኩ እያለ በማህበራዊ ሚዲያ ብቻ አለሁ ለማለት የውሸት ፕሮፖጋንዳውን እያሰራጨ የሚገኝ ቢሆንም አሁን ላይ ህዝቡም የዚህን ተስፈኛ ቡድን የውሸት ጥግ የተረዳ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
ሌላው ቀርቶ እኔን እንኳን በማህበራዊ ሚዲያ ሶስት ጊዜ ገድሎኛል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል አበባው ሰይድ ለውሸት ድንበር የሌለው ይህ ፅንፈኛ ቡድን እገሌን አሰናበትኩት እያለ በማህበራዊ ሚዲያ ያልገደለው አመራር የለምም ብለዋል፡፡
የፅንፈኛው ኃይል ተዋጊው ግማሹ ተደምስሷል የቀረው ተበትኖ አመራሩ ብቻውን ቀርቷል ፣ የእኛ ዋና ተግባራችንም ይህንን በጣዕረ-ሞት ውስጥ የሚገኘውንና ራሱን ለማቆየት በየሸለቆው የሚሽሎከለከውን የፅንፈኛ ቡድን እስከመጨረሻው እንደመስሰዋለን ብለዋል።
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በፅንፈኛው ቡድኑ ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በአዲስ አበባ በህቡዕ በተደራጀው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ የተባለው የፅንፈኛው ቡድን አመራር እና አቤነዘር ጋሻው አባተ የተባለ የቡድኑ አባል ከፀጥታ ኃይሎች ጋር ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ ሕጋዊ እርምጃ የተወሰደባቸው ሲሆን ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ የተባለው የቡድኑ አባል ደግሞ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን ገልጿል፡፡
በአዲስ አበባና አካባቢዋ ተወጥኖ ለከሸፈው ህቡዕ የጥፋት ተልዕኮ ዋነኛ ጠንሳሽ የሆነው ናሁሰናይ አንዳርጌ የተባለው ግለሰብ የጽንፈኛ ቡድኑ መሪ እንደነበር የጋራ ግብረ-ኃይሉ በመግለጫ አረጋግጧል።
ናሁሰናይ አንዳርጌ የጽንፈኛ ቡድኑ እኩይ ዓላማ እንዲሳካ የሽብር ጥቃት እንዲፈጽሙ የመለመላቸው ወጣቶች ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ የፋይናንስና የሎጅስቲክስ ድጋፎችን ከሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ከሚገኙ ደጋፊዎቻቸው በማሰባሰብ ሁኔታዎችንም እንዳመቻቸ መግለጫው አትቷል፡፡
የፅንፈኛ ቡድን አባላት የተለያዩ የሽብር ጥቃት ለማድረስ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ህቡዕ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም ከፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል እይታ ውጭ አልነበሩም ብሏል መግለጫው።
የሸብር ቡድኑ አባላት በዛሬው ዕለት በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ መኪናን በመጠቀም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ የሽብር ተግባራቸውን ለመፈፀም በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ በፀጥታ ኃይሉ በሰላም እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ከመሆን ይልቅ በፀጥታ አካላት ላይ ቶክስ በመክፈት በሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት አደርሰዋል ብሏል መግለጫው።
በተጨማሪም አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ የሽብር ቡድኑ አባላት በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም አልተባበር በማለታቸው በፅንፈኛ ቡድኑ አባላት ተገድለዋል፡፡
ጽንፈኛ ቡድኑ በአማራ ክልል እያደረሰ ያለው ጥቃት እንደማያዋጣው በመረዳቱ ራሱን ወደ ሽብርተኝነት ቀይሮ በአዲስ አበባ እና አከባቢዋ የመጨረሻ መፍጨርጨር እያደረገ እንደሚገኝ የገለፀው የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል መግለጫ የከተማዋን ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ ሰላም ወዳዱ የአዲስ አበባ ነዋሪ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን እስከአሁን ድረስ እያደረገ ላለው ትብብር ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረበ ሆቴሎች፣ ገስት ሀውሶች፣ የቤት እና የመኪና አከራዮች እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ኅብረተሰቡ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ቀና ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ጥሪውን አቅርቧል።
በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም‼️
🗣 አዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።
አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።
“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።
“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።
