የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
4 648
المشتركون
-23224 ساعات
-1 7917 أيام
-3 26430 أيام
أرشيف المشاركات
Russia የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ብቻ ይፈጅበታል የተባለለት “ዚርኮን” ከድምፅ በ9 እጥፍ የሚፈጥነው አዲሱ የሩሲያ ሱፐር ሶኒክ ሚሳዔል!!
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያ የጦር መርከቦች በቅርብ ዋት ውስጥ “ዚርኮን” የተባለውን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል እንደሚታጠቁ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ በትናትናው እለት እንዳስታወቁት፤ ዚርኮን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል “የማይበገር” አዲስ የጦር መሳሪያ ነው። በሰዓት ከ6 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚምዘገዘገው ሃይፐርሶኒክ ሚሳዔል አዲሱ የሩሲያ ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል ከድምፅ በ9 እጥፍ የሚፈጥ እና በቀላሉ የማይመታ እንደሆነም ነው እየተነገረ ያለው።
ሚሳዔሉ እስከ 1 ሺሀ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ የማጥቃት አቅም ያለው ሲሆን፤ ሚሳዔሉ በፍጥነቱ በዓለማችን ላይ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም። ሩሲያ በሚሳዔሉ ላይ ሙከራ ማድረግ የጀመረችው በፈረንጆቹ 2021 የበልግ ወቅት ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹ ሙከራዎችም ከሰርጓጅ መርከቦች ላይ የተደረገ ነው ተብሏል።
ሚሳዔሉ ለባህር ኃይል እና ለመድር ጦር እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን፤ ለባህር ኃይል የተሰራው ለሰርጓጅ እና ባህር ላይ ለሚጓዙ መርከቦችም እንዲታጠቁት ተደርጎ ነው የተሰራው። የሚሳዔሉ ፍጥነት ከድምጽ በ9 እጥፍ ይበልጣል የተባለ ሲሆን፤ ይህም የአየር መከላከያ ስርዓቶች አስቸጋሪ እና የማይመታ አድርጎታል።
“አደገኛው” የሩሲያ “ዛላ ኬ.ዋይ.ቢ” ድሮን ሚሳዔሉ በአየር ላይ እያለ የመገለባበጥ አቅም ያለው ሲሆን፤ አውዳሚ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የኒውክሌር አረር መሸከም የሚችል መሆኑም ተነግሯል። የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ ሚሳዔሉ ከዓለም አቀፍ የውሃ አካል ላይ ከተተኮሰ የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ብቻ ይፈጅበታል
“የማይበገር” የተባለው ሚሳዔሉ ከባህር ላይ ተተኩሶ የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ይበቃዋል
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያ የጦር መርከቦች በቅርብ ዋት ውስጥ “ዚርኮን” የተባለውን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል እንደሚታጠቁ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ በትናትናው እለት እንዳስታወቁት፤ ዚርኮን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል “የማይበገር” አዲስ የጦር መሳሪያ ነው።
አዲሱ የሩሲያ ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል ከድምፅ በ9 እጥፍ የሚፈጥ እና በቀላሉ የማይመታ እንደሆነም ነው እየተነገረ ያለው።
ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል ምን የተለያ ያደርገዋል?
ሚሳዔሉ እስከ 1 ሺሀ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ የማጥቃት አቅም ያለው ሲሆን፤ ሚሳዔሉ በፍጥነቱ በዓለማችን ላይ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም።
ሩሲያ በሚሳዔሉ ላይ ሙከራ ማድረግ የጀመረችው በፈረንጆቹ 2021 የበልግ ወቅት ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹ ሙከራዎችም ከሰርጓጅ መርከቦች ላይ የተደረገ ነው ተብሏል።
ሚሳዔሉ ለባህር ኃይል እና ለመድር ጦር እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን፤ ለባህር ኃይል የተሰራው ለሰርጓጅ እና ባህር ላይ ለሚጓዙ መርከቦችም እንዲታጠቁት ተደርጎ ነው የተሰራው።
የሚሳዔሉ ፍጥነት ከድምጽ በ9 እጥፍ ይበልጣል የተባለ ሲሆን፤ ይህም የአየር መከላከያ ስርዓቶች አስቸጋሪ እና የማይመታ አድርጎታል።
ሚሳዔሉ በአየር ላይ እያለ የመገለባበጥ አቅም ያለው ሲሆን፤ አውዳሚ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የኒውክሌር አረር መሸከም የሚችል መሆኑም ተነግሯል።
የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ ሚሳዔሉ ከዓለም አቀፍ የውሃ አካል ላይ ከተተኮሰ የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ብቻ ይፈጅበታል።
የቢሪታኒያው ሚረር ጋዜጣ እንዳስነበበው ከሆነ ደግሞ ሚሳዔሉ ከዓለም አቀፍ የውሃ አካል ላይ ከተተኮሰ የብሪታኒያዋ ለንደን ከተማን ለመምታ 4 ደቂቃ ብቻ ይበቃዋል ተብሏል።
የሩሲያው ታስ የዜና ወኪል መንነታቸው ያልተጠቀሰ የጦረ ምንጭን ጠቅሶ ባወጣው መረጃ፤ ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔልን የታጠቁ የሩሲያ የጦር መርከቦች በቀጣይ መስከረም ወር ወደ ስምሪት እንደሚገቡ አስታውቋል።
ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም
✍ የውትድርና ሙያን በወፍ በረር
እንደ ህዝብ ወይም እንደ ሀገር ክብርንና ዳር ድንበርን አስጠብቆ ለመኖር በአካልና በአዕምሮ የጎለበተ፣ በአስተሳሰብ የላቀ ፣ በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የተካነ ሰራዊት ያስፈልጋል።
በአለም ላይ ካሉ ሙያዎች ሁሉ ፅናትንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ ሙያ ቢኖር ደግሞ የውትድርና ሞያ ነው።
የውትድርና ሙያ እንደ ሌሎች የሙያ አይነቶች ጥቅምን መሰረት ያደረገ ሳይሆን እራስን ለህዝብና ለሀገር አሳልፎ በመስጠት በታማኝነትና በፅናት ራስን ለድል ወይንም ለመስዋዕትነት ማዘጋጀት እና መተግበርን ይጠይቃል። ይህ ብቻም ሳይሆን በሌሎች ሙያዎች ወይም የስራ ዘርፎች ፈሪዎች፣ መንፈሰ ደካሞች እና ወላዋዮች እውቀትና ክህሎት ኖሯቸው አገልግሎቱን ሊሰጡ ይችላሉ።
ውትድርና ግን እነዚህን አያካትትም። ምክንያቱም ፈሪዎች፣ መንፈሰ ደካማዎችና ወላዋዮች ራስ ወዳዶች በመሆናቸው የአካል መጉደልንና የህይወት መስዋዕትነት የሚጠይቀውን ውትድርናን ሊኖሩት አይችሉምና።
ወታደር ጊዜውን፣ አካሉን፣ ህይወቱን በአጠቃላይ ለሀገሩና ለህዝብ ክብር ሲል አሳልፎ በመስጠት የቀን ሀሩሩን፣ የሌሊት ቁሩን፣ እሾህና ጋሬጣውን፣ ዳገትና ቁልቁለቱን፣ ፈተናና ችግሩን በጠንካራ መንፈስ ተቋቁሞ ድልን የሚቀዳጅ የቁርጥ ቀን ልጅ ማለት በመሆኑ የውትድርና ሙያ ምን ያህል ቁርጠኝነትንና ጀግንነት የሚጠይቅ ለመሆኑም ማሳያ ነው።
ውትድርና ፍፁም ታማኝነትንና ሀቀኝነትን የሚጠይቅም ክቡር ሙያም ነው። ይህ ማለት ግን ሌሎች ሙያዎች ታማኝነትን አይጠይቁም ማለት አይደለም። ከሌሎች በተለዬ ምስጢር ጠባቂነትን፣ ፍፁም ታማኝነትን የሚጠይቅ በመሆኑ እንጂ። ምክንያቱም ብዙ ጊዜ በውትድርና ሙያ በሚፈጠር ትንሽ ስህተት የሚያስከፈለው ዋጋ ግን እጅግ የገዘፈ ሊሆን ይችላልና።
ሌላው ውትድርናን ለየት የሚያደርገው ደግሞ ወታደራዊ ስነ-ምግባር ነው። ሌብነት፣ ውሸት፣ ክህደትና አታላይነት የመሳሰሉት በውትድርና ሙያ ውስጥ ቦታ የላቸውም ብቻ ሳይሆን ፍፁም የተወገዙም ናቸው።
ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ስትነካ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ወታደር ቢሆንም በተለይ ግን የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶና ከዚያም በፊት ለውጭ ወራሪዎች ሀገርንና ህዝብን አሳልፎ ላለመስጠት ብዙዎች ተዋድቀው የሀገርን ሰንደቅ አስከብረው አልፈዋል።
ስለሰንደቅ ዓላማ ካነሳን ላይቀር ወታደርና ሰንደቅ አላማ የማይነጣጠሉ የአንዲት ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው ማለትም ይቻላል። ምክንያቱም ወታደር የሚከፍለው መስዋእትነት አንድም ለሰንደቁ ክብር ነውና።
ሰንደቅ አላማ ደግሞ ሀገርና ህዝብን የሚወክል መለያ ምልክት ወይም አርማ በመሆኑ በውትድርና ሙያ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ብቻ ሳይሆን ለነፃነቱና ለሰንደቁ ክብር እስከ-ህይወት መስዋዕትነት መክፈል የተልዕኮው ቁልፍ ተግባር ነው።
ብዙዎች እንደሚሉት ወታደር ወጥቶ አደር ከሚሉት ድርብ ቃላት ጥምረት የተገኘ የሙያ ስም እንደሆነ ይታመናል። በእርግጥም በውትድርና ሙያ ቤተሰብ፣ ልጆች፣ ሌሎች የህይወት አውዶች ከሀገር ቀጥለው የሚመጡ ጉዳዮች ናቸው እንጂ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች አይደሉም።
በዚህም መሰረት ወታደር በበዓል ወይንም በአውደ አመት ብዙ ጊዜ ከቤተሰቡ ጋር አያሳልፍም። ምናልባትም ጉድጓድ ምሶ፣ ድንጋይ ተንተርሶ፣ ሳር ቅጠሉን ለብሶ፣ ከጠላት ጋር ተፋጦ አለያም በጦርነት ሊያሳልፍ ይችላል። ምክንያቱም ከፈጣሪ በታች የሀገር ጠባቂ ከሱ በቀር ማንም የለምና። እነዚህና ሌሎች ውትድርና የሚጠይቃቸው ፅናቶችና ቁርጠኝነቶች ወታደርን ወጥቶ አደር ሊያስብሉት ግድ ይላል።
ውትድርናን እጅግ የተወደደና የተከበረ ሙያ ከሚያደርጉት ነገሮች መካከል ደግሞ በውስጡ ያለው ጓዳዊነት አንዱ ነው።
ለምሳሌ በዘመናችን የዓለማችን ብሎም የሀገራችን ትልቅ ፈተናና በሽታ የሆነው ዘረኝነት በውትድርና ውስጥ ማረፊያ ቦታ የለውም። ይልቁንም በተቃራኒው አንዱ የአንዱን ቋንቋ ለመማር፣ ሌላው ደግሞ የሌላውን ባህልና ልምድ ለመልመድ በወንድማማች ስሜትና በአብሮነት መንፈስ የሚጓዙበት ልዩ ሙያ ነው።
ጓዳዊነትም ከሚለካባቸው መንገዶች አንዱ በቋንቋ፣ በዘርና በሀይማኖት ሳይለያዩ ለተሰባሰቡበት አንድ ዓላማ በፅናት በመቆም አንድነትን ማሳየት ማለት ነው። ይህን ሀሳብ በመላበስም ብዙዎች አንተ ቆይ እኔ ልቅደም እያሉ መስዋእትነት የሚከፍሉበት አድርገውም ያሳዩበት እጅግ የከበረ ሙያ ነው።
በአለም ላይ ያሉና የነበሩ ትላልቅ የሀገራት መሪዎችን ስንመለከትም አብዛኞች በውትድርና ሙያ ያለፋ ናቸው። ይህ የሚያሳየው ዉትድርና የውሳኔ ሰው መሆንንና ኃላፊነት መውሰድን የመሳሰሉ የአመራር ስብዕናዎች እንዲዳብሩ ያለው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ነው።
እንደ አጠቃላይ አሁን ባለንበት ሁኔታ የኢፌዴሪ መከላከያን የትንሿ ኢትዮጵያ ተምሳሌት እንደሆነ ሁሉ የውትድርና ሙያም ትልቁ የሀገር ወዳድ ዜጎች ዩንቨርሲቲ ነው። በዚህ ዩንቨርሲት ብዙዎቻችን ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ቆራጥነትን፣ ሀገር ወዳድነትን፣ ፅናትንና ለህዝብና ለሀገር መኖርን ብሎሞ መስዋዕትነት መክፈል የመሳሰሉትን ተምረንበታል። ይህ የሀገር ህልውና የሚረጋገጥበት የተከበረውን የውትድርና ሙያ በዜጎች ልብ ላይ በትክክለኛው ሚዛን እንዲመዘን መስራት ግን ግድ ይላል።
አንድ ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ለሀገሩ ብዙ ነገሮችን ሊያደርግ ይችላል። ለምሳሌ ካለው ላይ በመቀነስ የገንዘብ ድጋፍ፣ የቁሳቁስ ድጋፍ፣ የሙያ ድጋፍ ወዘተ ሊያበረክት ይችላል። ይህ ተግባር አንድ ሀገሩን የሚወድ ሰው ተግባር ነው። ወታደር ግን ያለውን ሁሉ ይሰጣል እንጂ የሚያስቀረው ነገር አይኖርም። ይህም ማለት አንድ ሰው ለሀገሩ አካሉንና ህይወቱን ጊዜውን ከሰጠ ሌላ ምን ሊቀረው ይችላል።
ሲጠቃለል ውትድርና የአካል መጉደልና የህይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ፤ መውጣት መውረድ የተሞላበት እጅግ ቁርጠኝነትንና ፅናትን የሚጠይቅ ቢሆንም የሚከፈሉ ዋጋዎች ሁሉ ለሀገር ፍቅርና ለህዝብ ክብር በመሆናቸው ሞትን እንኳን ሳይቀር በደስታ የሚምቱበት ልዩ ቦታና የተከበረ ሙያ ነው።
ንጉሴ ውብሊቀር
ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ የሩሲያ “ዋነኛ ስጋት” ነች ሲሉ ፈረጁ
ፕሬዝዳንቱ የሩሲያን የባህር ኃይል ሰፊ ስትራቴጂካዊ አላማዎችን የያዘ ባለ55 ገጽ ሪፎርም ፈርመዋል
ሩሲያ ፕሬዝደንት ቫላድሚር ፑቲን አሜሪካን ዋነኛ የሩሲያ ጠላት አድርገው ፈረጁ፡፡
ፕሬዝደንት ፑቲን ይህን ያሉት በሩሲያ በሴንት ፒተርስበርግ በተከበረው እና ታሪካዊ ነው በተባለው የባህር ቀን ላይ ነው፡፡
ባለፈው ቅዳሜ አዲስ የባህር ኃይል መተዳደሪያ ላይ ፊርማቸውን ያስቀመጡት ፕሬዝደንት ፑቲን አሜሪካ ዋነኛ የሩሲያ ተቀናቃኝ አድርገው አስቀምጠዋል፡፡
በአዲሱ የባህር ኃይል መተዳደሪያ በአርክቲክ እና በጥቁር ባህር ሊኖር የሚችለው የሩሲያ እቅድ መነደፉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
በታላቁ ቄሳር ፒተር በተመሰረተችው የቀድሞዋ የንጉሠ ነገሥት ግዛት ሴንት ፒተርስበርግ በተከበረው የሩሲያ የባህር ኃይል ቀን ላይ ንግግር ያደረጉት ፑቲን ሩሲያን ታላቅ የባህር ሃይል እንዲኖራት የያደረጉትን ፒተርን አመስግነዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ዩክሬንን ትጥቅ ማስፈታት እና የናዚን አስተሳሰብ ማጥፋት የዘመቻው አላማ መሆኑን ሩሲያ መግለጿ ይታወሳል።
በሩሲያ ርምጃ የተቆጡት ምእራባውያን ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ሁሉ ማእቀብ በሩሲያ ላይ ጥለዋል።
የዶምባስ ግዛትን ነጻ የማውጣት የወሰነቸው ሩሲያ አሁንም በደቡብ እና ምሰራቃዊ ዩክሬን ጦርነት እያካሄደች ትገኛለች፡
የአሜሪካ አፈጉባዔ ከቻይና ማስፈራሪያ በኋላ ታይዋንን ከጉዞ ዝርዝር አስወጡ
ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ከሄዱ ቤጅንግ እርምጃ እንደምትወስድ ማስጠንቀቋን ተከትሎ ውጥረቱ አይሏል
የአሜሪካ አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ የእስያ ጉዟቸውን መጀመራቸውን በትናንትናው እለት ገልጸዋል፡፡
አፈጉባዔዋ ወደ እስያ ለመጓዝ ባወጡት ዕቅድ ላይ የታይዋንን ስም አለማካተታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
አፈጉባዔዋ የሩቅ ምስራቅ ጉብኝታቸውን መጀመራቸውን ገልጸው በዚህ ጉዞም ሲንጋፖርን፣ ማሌዥያን ፣ ደቡብ ኮሪያንና ጃፓን እንደሚሸፍን አስታውቀዋል።
የጉዟቸው ዓላማ በአሜሪካ እና በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እንደሆነም ገልጸዋል።
ናንሲ ፔሎሲ በእስያ ጉብኝታቸው ታይዋንን እንደሚጎበኙ ቀደም ብለው ገልጸው የነበረ ቢሆንም በአሁኑ የጉዞ ዝርዝር ግን ታይዋን አልጠቀሱም።
አፈጉባዔዋ በጉዞ ታይዋንን ያልጠቀሱት ከቻይና በተሰነዘረ የማስፈራሪያ ዛቻ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል።
ናንሲ ፔሎሲ ወደ ታይዋን ከሄዱ ቤጅንግ እርምጃ እንደምትወስድ ማስጠንቀቋን ተከትሎ ውጥረቱ አይሏል።
የሁለቱ ፕሬዝዳንቶች የንግግር ርዕስ ታይዋን የነበረች ቢሆንም በተለመደ ያለመስማማት መንፈስ ንግግራቸውን ጨርሰዋል ተብሏል።
በህገ ወጥ መንገድ ወደ ትግራይ ክልል ሊገባ የነበረ ከ8 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ብር ተያዘ ፌደራል ፖሊስ
መንግስት የሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እንዲገባ በፈቀደው መሰረት የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሽፋን በማድረግ ተደብቆ ወደ ትግራይ ክልል ሊገባ የነበረ ከ 8 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ብር ተያዘ፡፡
ህገ ወጥ ገንዘቡ የሰብኣዊ እርዳታ ለማድረስ በተዘጋጀ ተሽከርካሪ ተጭኖ በአፋር ክልል በኩል ወደ ትግራይ ክልል በመጓዝ ላይ ከነበረ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ መኪና ውስጥ ነው የተያዘው፡፡
መነሻውን ከአዲስ አበባ አድርጎ የሰብዓዊ የምግብ ድጋፍ በመያዝ እና በውስጡም የተጠቀሰውን ጥሬ ገንዘብ እና ሌሎች ያልተፈቀዱ ዕቃዎችን በህገወጥ መንገድ ወደ ትግራይ ክልል ለማሳለፍ የሞከረው የከባድ ጭነት ተሽከርካሪ በሰርዶ የፍተሻ ጣቢያ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አባላት በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በተደረገው ፍተሻ ልዩ ልዩ ጌጣጌጦች እንዲሁም ሌሎች ህገ-ወጥና ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶች መያዛቸው ታውቋል ።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በአፋር ክልል ሰርዶ የፍተሻ ጣቢያ የሚያደርገውን ጥብቅ ቁጥጥር አሁንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ምክትል ኢንስፔክተር አብዱረህማን ሀሰን ገልጸዋል ።
የአውሮፖና አሜሪካ ነገር 🤦🏻♂️
የሩሲያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በአፍሪካ ያደረጉት ጉብኝት አውሮፓ ኅብረት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር እንደገና ግንኙነት ለመጀመር ዘገምተኛ መሆኑ አንዳንድ የአውሮፓ መንግሥታትን እንዳሳሰባቸው ፖለቲኮ አስነብቧል።
የሩሲያ በኢትዮጵያ ያሰበቻቸውን እንቅስቃሴዎች የታዘቡት ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይና ሆላንድ ለኢትዮጵያ ጠቀም ያለ የገንዘብ ድጋፍ እንዲለቀቅላት መወትወት መጀመራቸውን ዘገባው ጠቁሟል።አውሮፓዊያን የኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም በሚፈታበት አግባብ ላይ ተመሳሳይ አቋም የላቸውም።
ትናንት በኢትዮጵያ ሰራዊት የተገደለው የአልሸባብ አመራር በአሜሪካ በጥብቅ የሚፈለግ እንደነበረ ተገለፀ
በአሜሪካ በጥብቅ የሚፈለገው አልሸባብ አመራር የሆነው ፉአድ መሐመድ ከለፍ (ሼንጎሌ) ትናንት በኢትዮጵያ ሰራዊት ከተገደሉት የአልሸባብ አመራሮች ውስጥ አንዱ ነበረ።
አሜሪካ ፉአድ መሐመድ ከለፍ (ሼንጎሌ) ያለበትን ለጠቆመ ሰው እስከ 5 ሚሊየን ዶላር የሽልማት ገንዘብ አዘጋጅታ እንደነበረ ሪዋርድ ፎር ጀስቲስ ከተባለ የአሜሪካ መንግስት ድረ ገጽ ላይ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ከላፍ በፈረንጆቹ 2008 በተሸከርካሪ ላይ በተጠመደ እና በሶማያ የሚገኝ የኢትዮጵያ ጦር ካምፕ እና የሽግግር መንግስት አካላትን ኢላማ ያደረገውን ጥቃትን ጨምሮ በሞቃዲሾ የተፈፀሙ የተለያዩ ጥቃቶችን መምራቱ ይነገራል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የአልሻባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊን ፉአድ መሐመድ ከሌፍ (ሼንጎሌ) ጨምሮ ሶስት የአልሸባብ አመራሮችን መግደሉን በትናትናው እለት አስታውቋል።
ሐምሌ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
"ኢትዮጵያን እናልብሳት! ሀዋሳ ሀይቅን እንታደግ!" በሚል መሪ ቃል ሠራዊታችን ከህብረተሰባችን ጋር በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አካሄደ፡፡
በአካባቢው ግዳጅ እየፈፀመ የሚገኘው የአየር ወለድ ክ/ጦር አባላትም ከግዳጅ ጎን ለጎን በተገኘው አጋጣሚ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ዙሪያ እና በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ሻላ ወረዳ ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ በመሆን በርካታ ችግኞችን ተክሏል፡፡
በፕሮግራም ላይ የተገኙት የሀዋሳ ዩነቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ተባባሪ ፕሮፌሰር ደ/ር ሙሉጌታ ዳዲ እንደተናገሩት የሀዋሳ ሀይቅ ዙሪያ ብዛ-ህይወት እና የሀይቁን ደህንነት ለማስጠበቅ በዙሪያው የሚገኙ ተራሮችን በደን ለማልበስ ዩንቨርስቲው አርንጓዴ አሻራ ከተጀመረ እስካሁን 1432 ስኩየር ኪ/ሜ ቦታ ላይ አንድ ሚሊየን ችግኞችን እንዲተከል አድርጓል፡፡
ደ/ር ሙሉጌታ አያይዘው እንደ ተናገሩት
ከሀገር መከላከያ ሠራዊት አየር ወለዶች አባላት ጋር በጋራ በመሆን አሻራቸውን በማሳረፍ ለኢትዮጵያ እየሞቱ ኢትዮጵያን በማልበስ የህብረተሰቡን ወኔና ስሜትም ቀስቅሰዋል፡፡
ለመከላከያ ሠራዊት ያለኝን ፍቅር በቃላት ብቻ የምገልጸው አይደለም የሠራዊት አባል መሆን ታላቅ ፀጋ ነው ሲሎ ተናግረዋል፡፡
ሻ/ል ዮሐንስ ጎአ እና ፶/አ አድማሱ አዴማ በበኩላቸው ህብረተሰቡ ጋር ችግኞችን በጋራ ተክልናል። መትከልም ብቻ ሳይሆን በመንከባክብ ጭምር የዜግነት ግዴታችንን እንወጣለን ብለዋል፡፡
ፈለቀ ዋሲሁን
ፎቶግራፍ ጌትነት አበባው
መንግስት፤ ህወሓት የሰላም ሂደቱ ላይ መሰናክል እየፈጠረ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያሳርፍበት ጠየቀ!
ም/ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የአሜሪካን የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመርን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
አቶ ደመቀ ለልዩ መልዕክተኛው መንግሥት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እየወሰዳቸው ያሉ ርምጃዎች ላይ ገለጻ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያወጣው መረጃ ያመለክታል። በዚህም አቶ ደመቀ፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ አማካኝነት ለተጀመረው የሰላም ጥረት መንግሥት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
መንግሥት ለሰላም ድርድሩ ያለውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ተደራዳሪ ቡድን አቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም አቶ ደመቀ መኮንን ገልፀዋል። ም/ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተኩስ አቁም ስምምነቱ፣ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ ተጀራሽነት እና ሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ተጠናክረው እንደቀጠሉም ለልዩ መልዕክተኛው ገልፀዋል።
መንግሥት ለሰላም ድርድሩ ሙሉ ቁርጠኝነቱን እያሳየ ባለበት ወቅት የህወሓት ቡድን በተቃራኒው እያሳያ ያለው አቋም ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በአፍሪካ ህብረት መሪነት በሚካሄደው እንቅስቃሴ ላይ መሰናክል የሚፈጥር በመሆኑ፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቡድኑ ላይ ጫና ሊያሳርፍ ይገባል ማለታቸውንም ከቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የቻይና ጦር ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ
የቻይና የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ያደረጉት የስልክ ውይይት ያለመግባባት ተጠናቋል
የአሜሪካ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታዋንን ከጎበኙ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ቻይና ከቀናት በፊት ማስጠንቀቋ ይታወሳል።
የቻይና ጦር ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ።
የቻይና ጦር ዌቦ በተሰኘው የሀገሪቱ ማህበራዊ ትስስር ገጹ እንሳሳወቀው ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
የሀገሪቱ 80ኛ ጦር ያወጣውን መገለጫ ዋቢ አድርጎ የሩሲያው አርቲ እንደዘገበው ከሆነ ወደ ጦርነት ለመግባት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
የጦሩ ለጦርነት ዝግጁ መሆኑን ማስታወቁ የአሜሪካ አፈ ጉባኤ የታይዋን ጉብኝት ምላሽ እንደሆነ እየተገለጸ ነው።
አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ከቀናት በኋላ በሚገባው ነሀሴ ወር ላይ ታይዋንን እንደሚጎበኙ መግለጻቸው ይታወሳል።
የአፈ ጉባኤውን የታይዋን ጉብኝት ተከትሎም ቻይና ወታሰራዊ እርምጃዎችን ጨምሮ ማንኛውንም አይነት እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል መናገሯ አይዘነጋም።
የሁለቱ ሀገራት ፕሬዝዳንቶች በዛሬው ዕለት በስልክ የተወያዩ ሲሆን ውይይቱ ያለ ስምምነት መጠናቀቁን ሮይተርስ ዘግቧል።
የአሜሪካዋ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ቻይና የግዛቷ አካል አድርጋ የምትቆጥራትን ታይዋንን ለመጎብኘት ማቀዳቸው ሁለቱን ሀገራት ከፍተኛ አለመግባባት ውስጥ ከቷቸዋል።
የሰሞኑ የሰርጌይ ላቭሮቭ የኢትዮጵያ ጉብኝት እና የሩሲያ ጥብቅ ወዳጅነት አውሮፓውያንን አስደንግጧል ። አለምአቀፉ መፅሄት POLETICO የሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር እየፈጠረቺው ያለው የጠበቀ ግንኙነት የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ያለውን አቋም እንዲቀይር እያደረገው ነው ይላል ።
አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት በመጀመሪያ ለግብፅ ከዚያም ደግሞ ለህወሀት የሰጡት አድሎአዊ ድጋፍና በኢትዮጵያ ላይ የፈጠሩት ያልተገባ ማእቀብና ጫና ኢትዮጵያን ወደ ሩሲያና ቻይና ጎራ የገፋ ከምእራቡ ጎራም ያራቀ ሆኗል ። እናም አሁን አለም ከምእራባውያን ዘዋሪነት እየተላቀቀችበት ባለው ሁኔታ ይህ የምእራባውያን አጥፊ አካሔድ የነርሱን ጎራ እያሳሳ የምስራቁን ጎራ እያደነደነ በመሆኑ ከነርሱ ጎራ ስለሚያፈነግጡ ሀገራት መስጋት ከጀመሩ ሰነባበቱ ።
በተለይም አፍሪካን በንቀት በማየት ችላ እንዳላሏት ዛሬ ቻይናና ሩሲያ አህጉሪቱ ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ኢንቨስትመንት እያካሔዱና አፍሪካን ከምእራቡ አለም አላቀው ወደነርሱ መጠቅለላቸው ለአውሮፓ ትልቅ ስጋትን የፈጠረ ነው ። ኢትዮጵያ ደግሞ ቀዳሚዋ ነች ።
የአውሮፓ ህብረት አሁን ኢትዮጵያን ወደ ማባበል ተመልሷል ። ደጅ መጥኚያ እንዲሆነውም ለኢትዮጵያ የ 81.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍን አፅድቋል ። ፈረንሳይ ፣ ኢጣልያ ፣ ጀርመንና ኔዘርላንድ ከአቋማቸው በመከርበት ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ድጋፍ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነው ።
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የአንድ ቢሊዮን ዩሮ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቱ የምእራባዊያን ክሽፈት ያሳየና የቅኝ ግዛት አስተሳሰባቸው ለአሁኑ አፍሪካ የማይመጥን መሆኑን ያረጋገጠ ነው ። አሁን አሜሪካም የኢትዮጵያን ፍላጎት እያንፀባረቀች ትገኛለች ። ሁሉም እየከዳቸው ያለው ምእራባውያን ሁሉንም እያባበሉ ይገኛሉ ። አለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት ትግራይን ለማልማት ለኢትዮጵያ 300 ሚሊዮን ዶላር የበጀተው ወዶን ሳይሆን እንዳላጣት በሚል ተገዶ ነው ።
ለዚህ ሁሉ ስኬት የመንግስታችንን የድፕሎማሲ ጥንካሬ አለማድነቅ አይቻልም!
©Seid_Mohammed_Alhabeshiy
የአልሻባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊን ፏአድ መሐመድ ከሌፍ (ሼንጎሌ) ጨምሮ ሶስት የቡድኑ አመራሮች ተደመሰሱ
የአልሻባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊን ፏአድ መሐመድ ከሌፍ (ሼንጎሌ) ጨምሮ ሶስት የቡድኑ አመራሮች መደምሰሳቸውን የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊና ጊዜያዊ የፀጥታ ኮማንድፖስት አስተባባሪ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ተናገሩ።
ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ቀናት ከኢፌዴሪ አየር ኃይል ጋር በመቀናጀት በተወሰደው ርምጃ የሽብር ቡድኑ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ያዘጋጃቸውን የትጥቅና ስንቅ ዴፖዎች ማውደም ተችሏል፡፡
በተጨማሪም የአሸባሪ ቡድኑ አመራሮችና ታጣቂዎች በተወሰደው ርምጃ ተደምስሰዋል።
ከተደመሰሱት ውስጥ የአልሸባብ ከፍተኛ ኮማንደሮች ውስጥ:-
1. ፏአድ መሐመድ ከለፍ (ሼንጎሌ) የአልሸባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ሃላፊ፣
2.አብዱላዚዝ አቡ ሙሳ የአልሸባብ ቃል አቀባይ፣
3.ኡቤዳ ኑር ኢሴ የአልሸባብ የቦኮል ዞንና የኢትዮጵያ ድንበሮች አዋሳኝ ሃላፊ መደምሰሳቸውን ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ታሪክን የኋሊት
ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ በፋሽስት ጣሊያን ሰማዕትነት የተቀበሉት የዛሬ 86 ዓመት በዛሬው ቀን ነበር፡፡
ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ መስቀልና ወንጌል ብቻ ይዘው የወራሪውን የኢጣሊያ ፋሽስት ነውሩንና ግፉን ፊት ለፊት ታግለው ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ሕይወታቸውን አሳልፈው የሰጡት ሐምሌ 22፣ 1928 ነበር፡፡
አባ ኃይለማርያም ከመጀመሪያዎቹ አራት ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሆነው ሲመረጡ ስማቸው ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ሆነ፡፡
በቅኔ፣ በዜማ፣ በመፃህፍት ትርጓሜ የተመረቁት አቡነ ጴጥሮስ በ1921 ዓ.ም ጳጳስነት ከተሾሙ በኋላ የኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ኢትዮጵያን እስከወረረበት ጊዜ ድረስ ሙሉ ወሎንና ከሸዋ መንዝን ሃገረ ስብከታቸው አድርገው ቆይተዋል፡፡
ከዚያ በፊትም በወላይታ በዝዋይ በመምህርነት አገልግለዋል፡፡
በማይጨው ዘመቻ ጊዜ ከንጉሰ ነገስቱ ጋር ሳይለዩ ተዋጊውን ሰራዊት እያበረታቱ አዋግተዋል፡፡
ኢትዮጵያኑ ድል ሆነው ካፈገፈጉ በኋላ በትውልድ አካባቢያቸው በሰላሌ ከተሰማሩት አርበኞች ጋር ተቀላቅለው ቆዩ፡፡
በ1928 ዓ.ም ሐምሌ ወር አዲስ አበባን ከኢጣሊያኖች አገዛዝ ነፃ ለማውጣት በተደረገው ከበባ በሰሜን በኩል ከዘመቱት አርበኞች ጋር አዲስ አበባ ገቡ፡፡
አርበኞች አልቀናቸውም፤ ድል ሆነው ሲመለሱ ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ግን ለመመለስ አልፈለጉም፡፡
ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ፀሎት አድርሰው በቀጥታ ወደመሐል ከተማ ገብተው ተያዙ፡፡
የኢጣሊያ ሹማምንት አቡነ ጴጥሮስን አባበሉዋቸው፤ የኢጣሊያን ገዥነት ካመኑ በክብር እንደሚያዙ ነገሩዋቸው፡፡
ጳጳሱ ግን እምቢ አሉ፡፡
ገንዘብህ ለጥፋትህ ይሁን ብለው ረገሙ፡፡
እንኳንስ ሰው ምድሩዋ እንዳትገዛለት አወገዙ፡፡
በአቡነ ጴጥሮስ ድርጊት የተናደደው ጀኔራል ግራዚያኒ እንዲገደሉ ወሰነባቸው፡፡
ሐምሌ 22፣ 1928 ዓ.ም ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ በሰንሰለት ታስረው ከአራዳ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንክ በስተምዕራብ ባለው ቦታ ቆሙ፡፡
ከኋላቸው 8 ወታደሮች ጠመንጃቸውን ወድረው ተሰልፈዋል፡፡
በጊዜው በቦታው የነበረው ጋዜጠኛ እንደፃፈው፤ ጥቁሩ ቀሚሳቸው ጭቃ ነክቶታል፤ ወንጌላቸውንና መስቀላቸውን ይዘዋል፡፡
ግድያቸውን እንዲመለከት በትዕዛዝ ወደተሰበሰበው እየተመለከቱ፤ ሕዝቡም ሆነ ምድሩዋ እንዳትገዛላት አወገዙ፡፡
ወዲያው የኪስ ሰዓታቸውን አወጡና አዩ፡፡
ከረፋዱ 5፡30 ሆኖ ነበር፡- ይልና ጋዜጠኛው ስለአሟሟታቸው እንዲህ ይላል፡፡
“አንድ መኮንን ውሳኔውን እየተንቀቀጠ ሲያነብ እሳቸው ግን ያለምንም ስጋት ያዳምጡት ነበር፡፡
ወዲያው ዓይንዎ እንዲሸፈን ይፈልጋሉ? ሲል ጠየቃቸው፡፡ ጳጳሱም “እሱ የናንተ ተግባር ነው” አሉት፡፡
ትዕዛዝ ሲሰጣቸው ወታደሮቹ ተኮሱ፤ በስምንት ጥይትም መቷቸው፡፡
ግን አልሞቱም ነበርና ኮሎኔሉ በሶስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸው ላይ ተኩሶ ገደላቸው፡፡ ሕዝቡም በሀዘን ተሰበረ ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ንብረታቸውን ወስጃለሁ ያለው ወታደር እንደነገረው ከሆነ ወንጌላቸውና መስቀላቸው በጥይት ተበሳስቷል፡፡
አቡነ ጴጥሮስ በ53 ዓመታቸው አሁን ሐውልታቸው በቆመበት አካባቢ ተገድለው ባልታወቀ ቦታ ተቀብረዋል፡፡
ከነፃነት በኋላ በ1938 ዓ.ም ለመታሰቢያ እንዲሆን ሐውልት ተቀርፆ ቆመላቸው፡፡
አሁን የሚታየው ሐውልት ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሽሎ ተቀርፆ የቆመላቸው ነው፡፡
በፍቼም ለሶስተኛ ጊዜ ሐውልት ተቀርፆላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሙሉ ድምፅ በወሰነው መሰረት ሰማዕትነታቸውን አፅድቆ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሰርቶላቸዋል፡፡
ሰማዕተ ፅድቅ አቡነ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን የታነፀው የሀገረ ስብከታቸው መቀመጫ በሆነው በፍቼ ነው፡፡
የብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የብዙ የጥበብ ሰዎችን ስሜት እየገዛ ገጣሚዎች ገጥመውላቸዋል፣ ቅኔ አዋቂዎች ቅኔ ዘርፈውላቸዋል፤ ድራማ ተሰርቶላቸዋል፡፡
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
#Join https://t.me/Commando_and_AirBorne_Battleship
ታሪክን የኋሊት
ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ በፋሽስት ጣሊያን ሰማዕትነት የተቀበሉት የዛሬ 86 ዓመት በዛሬው ቀን ነበር፡፡
ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ መስቀልና ወንጌል ብቻ ይዘው የወራሪውን የኢጣሊያ ፋሽስት ነውሩንና ግፉን ፊት ለፊት ታግለው ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ሕይወታቸውን አሳልፈው የሰጡት ሐምሌ 22፣ 1928 ነበር፡፡
አባ ኃይለማርያም ከመጀመሪያዎቹ አራት ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሆነው ሲመረጡ ስማቸው ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ሆነ፡፡
በቅኔ፣ በዜማ፣ በመፃህፍት ትርጓሜ የተመረቁት አቡነ ጴጥሮስ በ1921 ዓ.ም ጳጳስነት ከተሾሙ በኋላ የኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ኢትዮጵያን እስከወረረበት ጊዜ ድረስ ሙሉ ወሎንና ከሸዋ መንዝን ሃገረ ስብከታቸው አድርገው ቆይተዋል፡፡
ከዚያ በፊትም በወላይታ በዝዋይ በመምህርነት አገልግለዋል፡፡
በማይጨው ዘመቻ ጊዜ ከንጉሰ ነገስቱ ጋር ሳይለዩ ተዋጊውን ሰራዊት እያበረታቱ አዋግተዋል፡፡
ኢትዮጵያኑ ድል ሆነው ካፈገፈጉ በኋላ በትውልድ አካባቢያቸው በሰላሌ ከተሰማሩት አርበኞች ጋር ተቀላቅለው ቆዩ፡፡
በ1928 ዓ.ም ሐምሌ ወር አዲስ አበባን ከኢጣሊያኖች አገዛዝ ነፃ ለማውጣት በተደረገው ከበባ በሰሜን በኩል ከዘመቱት አርበኞች ጋር አዲስ አበባ ገቡ፡፡
አርበኞች አልቀናቸውም፤ ድል ሆነው ሲመለሱ ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ግን ለመመለስ አልፈለጉም፡፡
ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ፀሎት አድርሰው በቀጥታ ወደመሐል ከተማ ገብተው ተያዙ፡፡
የኢጣሊያ ሹማምንት አቡነ ጴጥሮስን አባበሉዋቸው፤ የኢጣሊያን ገዥነት ካመኑ በክብር እንደሚያዙ ነገሩዋቸው፡፡
ጳጳሱ ግን እምቢ አሉ፡፡
ገንዘብህ ለጥፋትህ ይሁን ብለው ረገሙ፡፡
እንኳንስ ሰው ምድሩዋ እንዳትገዛለት አወገዙ፡፡
በአቡነ ጴጥሮስ ድርጊት የተናደደው ጀኔራል ግራዚያኒ እንዲገደሉ ወሰነባቸው፡፡
ሐምሌ 22፣ 1928 ዓ.ም ብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ በሰንሰለት ታስረው ከአራዳ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንክ በስተምዕራብ ባለው ቦታ ቆሙ፡፡
ከኋላቸው 8 ወታደሮች ጠመንጃቸውን ወድረው ተሰልፈዋል፡፡
በጊዜው በቦታው የነበረው ጋዜጠኛ እንደፃፈው፤ ጥቁሩ ቀሚሳቸው ጭቃ ነክቶታል፤ ወንጌላቸውንና መስቀላቸውን ይዘዋል፡፡
ግድያቸውን እንዲመለከት በትዕዛዝ ወደተሰበሰበው እየተመለከቱ፤ ሕዝቡም ሆነ ምድሩዋ እንዳትገዛላት አወገዙ፡፡
ወዲያው የኪስ ሰዓታቸውን አወጡና አዩ፡፡
ከረፋዱ 5፡30 ሆኖ ነበር፡- ይልና ጋዜጠኛው ስለአሟሟታቸው እንዲህ ይላል፡፡
“አንድ መኮንን ውሳኔውን እየተንቀቀጠ ሲያነብ እሳቸው ግን ያለምንም ስጋት ያዳምጡት ነበር፡፡
ወዲያው ዓይንዎ እንዲሸፈን ይፈልጋሉ? ሲል ጠየቃቸው፡፡ ጳጳሱም “እሱ የናንተ ተግባር ነው” አሉት፡፡
ትዕዛዝ ሲሰጣቸው ወታደሮቹ ተኮሱ፤ በስምንት ጥይትም መቷቸው፡፡
ግን አልሞቱም ነበርና ኮሎኔሉ በሶስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸው ላይ ተኩሶ ገደላቸው፡፡ ሕዝቡም በሀዘን ተሰበረ ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ንብረታቸውን ወስጃለሁ ያለው ወታደር እንደነገረው ከሆነ ወንጌላቸውና መስቀላቸው በጥይት ተበሳስቷል፡፡
አቡነ ጴጥሮስ በ53 ዓመታቸው አሁን ሐውልታቸው በቆመበት አካባቢ ተገድለው ባልታወቀ ቦታ ተቀብረዋል፡፡
ከነፃነት በኋላ በ1938 ዓ.ም ለመታሰቢያ እንዲሆን ሐውልት ተቀርፆ ቆመላቸው፡፡
አሁን የሚታየው ሐውልት ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሽሎ ተቀርፆ የቆመላቸው ነው፡፡
በፍቼም ለሶስተኛ ጊዜ ሐውልት ተቀርፆላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሙሉ ድምፅ በወሰነው መሰረት ሰማዕትነታቸውን አፅድቆ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሰርቶላቸዋል፡፡
ሰማዕተ ፅድቅ አቡነ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን የታነፀው የሀገረ ስብከታቸው መቀመጫ በሆነው በፍቼ ነው፡፡
የብፅዕ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የብዙ የጥበብ ሰዎችን ስሜት እየገዛ ገጣሚዎች ገጥመውላቸዋል፣ ቅኔ አዋቂዎች ቅኔ ዘርፈውላቸዋል፤ ድራማ ተሰርቶላቸዋል፡፡
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
#Join https://t.me/Commando_and_AirBorne_Battleship
" አልሸባብ ዳግም ከፍተኛ ኪሳራ ተከናንቦ ወደ መጣበት ተመልሷል " - ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው
የሀገር መከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊና ጊዜያዊ የፀጥታ ኮማንድፖስት አስተባባሪ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ወደ ኢትዮጵያ ሰርጎ ለመግባት የሞከረው የአልሸባብ የሽብር ቡድን በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት እርምጃ ዳግም ከፍተኛ ኪሳራ ተከናንቦ ወደ መጣበት መመለሱን ተናግረዋል።
ከቀናት በፊት የአልሸባብ አሸባሪ ቡድን በሶማሌ ክልል በ5 ትናንሽ የጠረፍ አካባቢዎች ወደ አገር ውስጥ ሰርጎ በመግባት ጥቃት ለመፈጸም ያደረገው ሙከራ በጸጥታ ሃይሉ ሙሉ በሙሉ መክሸፉን ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም የጸጥታ ኃይሉ ተቆርጠው የቀሩትን የሽብር ቡድኑ አባላትን የማጽዳት ዘመቻ ሲያከናውን መቆየቱን ገልፀዋል።
ባለፉት ቀን ከኢፌዴሪ አየር ኃይል ጋር በመቀናጀት በተወሰደው ርምጃ የሽብር ቡድኑ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ያዘጋጃቸውን የትጥቅና ስንቅ ዴፖዎች ማውደም ተችሏል፡፡ በዚህም በሽብር ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበት ጠቁመዋል፡፡
ነገር ግን የሽብር ቡድኑ #ዛሬ_ሌሊት ላይ የተበታተነ ኃይሉን በማሰባሰብ ኢትዮጵያና ሶማሊያ በሚዋሰኑበት አካባቢ ወደ አገር ውስጥ ሰርጎ በመግባት ጥቃት ለመፈጸም ሞክሮ ነበር።
ሆኖም የጸጥታ ኃይሉ በወሰደው እርምጃ የሽብር ቡድኑ ዳግም ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራዎችን ተከናንቦ ወደ መጣበት መመለሱን ነው ያብራሩት፡፡
እስካሁን ባለው መረጃም ከ150 በላይ የሽብር ቡድኑ አባላት መደምሰሳቸውንና የሽብር ቡድኑ ለአጥፍቶ መጥፋት ያዘጋጃቸው ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ፣ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች እንደተማረኩ አመልክተዋል።
#ENA
ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
#Join https://t.me/Commando_and_AirBorne_Battleship
