ar
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis abeba Ethiopia

إظهار المزيد
4 550
المشتركون
-22324 ساعات
-1 7327 أيام
-3 48930 أيام
أرشيف المشاركات
ሰበር ዜና‼️ #Ethiopia : የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይልና የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የኢትዮጵያ አየር ሃይል በወሰዱት ማጥቃት ፉአድ ሰንቆሌ የተባለው የአልሸባብ ከፍተኛ አመራር/ሁለተኛ ሰው ተገ
ሰበር ዜና‼️ #Ethiopia : የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይልና የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የኢትዮጵያ አየር ሃይል በወሰዱት ማጥቃት ፉአድ ሰንቆሌ የተባለው የአልሸባብ ከፍተኛ አመራር/ሁለተኛ ሰው ተገድላል::

መንግስት ከህወሓት ጋር በየትኛውም ጊዜና ቦታ ለመወያየት መዘጋጀቱን ገለጸ የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሃት ጋር በየትኛውም ጊዜና ቦታ ለመደራደር መዘጋጀቱን የድርድር ቡድኑ አባልና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብ
መንግስት ከህወሓት ጋር በየትኛውም ጊዜና ቦታ ለመወያየት መዘጋጀቱን ገለጸ የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሃት ጋር በየትኛውም ጊዜና ቦታ ለመደራደር መዘጋጀቱን የድርድር ቡድኑ አባልና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ የደህንነት አማካሪ አስታወቁ፡፡ የድርድር ቡድኑ አባልና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሌላኛው የድርድር ቡድኑ አባልና ከፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ጋር በመሆን ከተለያዩ አካላት ጋር ንግግር ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ አምባሳደር ሬድዋንና ዶ/ር ጌዲዮን ቲሞቲዮስ፤ ከተባበሩት መንግስታት፣ ከአውሮፓ ህብረት፣ ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ እንዲሁም ከአሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ጀርመን እና ብሪታኒያ አምባሳደሮች ጋር መወያየታቸው አስታውቀዋል፡፡

መከላከያ በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሀገራቸውን በዓለም መድረክ ከፍ አድርገው ላስጠሩ አትሌቶች አቀባበል አደረገ። አትሌቶቹ ፈተናዎችን ተቋቁመውና ጠንክረው ሰርተው ላስመዘገቡት ድል የሀገር
መከላከያ በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሀገራቸውን በዓለም መድረክ ከፍ አድርገው ላስጠሩ አትሌቶች አቀባበል አደረገ። አትሌቶቹ ፈተናዎችን ተቋቁመውና ጠንክረው ሰርተው ላስመዘገቡት ድል የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ምስጋና አቅርቦላቸዋል። በአቀባበል ስነ ሥርዓቱ ላይ የመከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይን ጨምሮ ም/ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ፣ ጀኔራል መኮንኖች እና ተጋባዥ እንግዶች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንደ ሀገር በተገኘው ድል ላይ የመከላከያ አትሌቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዳበረከቱም ተገልጿል። አትሌቶች ከምንም በላይ ሀገርን በማስቀደም ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጋቸውን የገለፁት የመከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ፈተናዎችን ተቋቁመው በመሥራታቸው ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል። በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአንድነት በመሰለፍ ያሳዩት ብቃት የሚደነቅና የሚመሰገን እንደሆነም ሚንስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ገልፀዋል። አስተያየታቸውን የሰጡት የመከላከያ ሠራዊት አባላትም አትሌቶቻችን ያስመዘገቡት ድል ሀገርን ያኮራና አንድነትን ይበልጥ ያጠናከረ ነው ብለዋል። ለ18ኛ ጊዜ በአሜሪካ ኦሪገን በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ 4 ወርቅ፣ 4 ብር፣ 2 ነሐስ የተገኘ ሲሆነ ከዚህ ውስጥ የመቻል አትሌቲክስ ቡድን በሴቶች 3000 ሜ መሰናክል መሰረታዊ ወታደር ወርቅውሀ ጌታቸው የብር ሜዳል፤ በ5000 ሜ ሃምሳ አለቃ ዳዊት ስዩም የነሐስ ሜዳሊያ ማግኘታቸው ይታወቃል።

ሩሲያ በግዝፈቱ ሁለተኛ የሆነውን የዩክሬን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች የሩሲያ በዩክሬን በግዝፈቲ ሁለተኛ የሆነውን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች፤ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ደቡባዊ ዩክሬን ልካለች። ሩሲያ ጦር
ሩሲያ በግዝፈቱ ሁለተኛ የሆነውን የዩክሬን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች የሩሲያ በዩክሬን በግዝፈቲ ሁለተኛ የሆነውን የኃይል ጣቢያ ተቆጣጠረች፤ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ደቡባዊ ዩክሬን ልካለች። ሩሲያ ጦርነቱ ሲጀመር ከዓለም ትልቅ የሆነው የኒውክለር ኃይል ጣቢያ መቆጣጠር ችላ ነበር የሩሲያ ጦር የኃይል ጣቢያውን መቆጣጠሩንና በደቡባዊ ዩክሬን ወደሚገኙ ሶስት ግዛቶች ብዛት ያላቸው የሩሲያ ወታደሮች መላካቸውን የዩክሬን ፕሬዝደንት አማካሪ ተናግረዋል፡፡ ©ሮይተርስ

#ሽልማት ወርቅ ያመጡ አትሌቶቻችን ! ለሁሉም 1.5 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቷል። እንደተሳትፏቸው መጠንና እንዳስመዘገቡት ስኬት ተጨማሪ ሽልማት ተበርክቷል። 🇪🇹 ለተሰንበት ግደይ (1.5 ሚሊዮ
#ሽልማት ወርቅ ያመጡ አትሌቶቻችን ! ለሁሉም 1.5 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቷል። እንደተሳትፏቸው መጠንና እንዳስመዘገቡት ስኬት ተጨማሪ ሽልማት ተበርክቷል። 🇪🇹 ለተሰንበት ግደይ (1.5 ሚሊዮን ብር + 500 ሺህ ብር ለቡድን ስራ ) 🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ (2.5 ሚሊዮን ብር - ሁለት ሜዳሊያ በማምጣቷ) 🇪🇹 ታምራት ቶላ (1.5 ሚሊዮን ብር + 250 ሺህ ብር ሪከርድ በመስበሩ) 🇪🇹 ጎተይቶም ገብረስላሰ (1.5 ሚሊዮን ብር + 250 ሺህ ብር የሻምፒዮናውን ሪከርድ በመስበሯ)

ሩሲያ ለኢትዮጵያ የ162 ሚሊዮን ዶላር ብድር እዳ ሰረዘች በኢትዮጵያ በህገወጥነት ይኖሩ የነበሩ 60 ሺህ የውጭ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ሰዎች መመዝገባቸው ተገለጸ ሩሲያ ለኢትዮጵያ 162 ሚሊዮን ዶላር ብድር መሰረዝዋን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ያጎለብተዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ከሶቭየት ህብረት የተበደረቻቸውን ብድሮች መሰረዟን በይፋ አሳውቃለች ብለዋል። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት ከሶቭየት ህብረት ወይም አሁን ላይ ሩሲያ ተብላ ከምትጠራው ሀገር 162 ሚሊዮን ዶላር የተበደረችውን ገንዘብ ሰርዛለች ያሉት አምባሳደር መለስ በብድር መልክ ሊከፈል የነበረው ገንዘብ ለምን አገልግሎት መዋል እንዳለበትም ሁለቱ ሀገራት ተስማምተዋልም ብለዋል። ቃል አቀባዩ አቶምባሳደር መለስ በመግለጫቸው አክለውም፣ በኢትዮጵያ በህገወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች ምዝገባ መጀመሩን እና እስካሁን 60 ሺህ ሰዎች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በእስካሁኑ ምዝገባ የካናዳ፣ አሜሪካ፣ኮንጎ፣ ናይጀሪያ ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ኤርትራ ፣ሱዳን፣ቻይና፣ ቡሩንዲ ጋና፣ ህንድ፣ ባንግላዲሽ፣ ላይቤሪያ፣ ጣልያን እና የካሜሩን ዜግነት ያላቸው ህገወጥ ሰዎች መገኘታቸው ተገልጿል። በዚህ ምዝገባ የተካተቱት በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቪዛ ጊዜያቸው የለፈበት፣ በህጋዊ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ፣ የስደተኝነት ፈቃድ የሌላቸው እና ፈቃድ ለማግኝት በሂደት ላይ ያሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች ናቸው ተብሏል። በግብፅ ብዙሃን መገናኛዎች የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ከግብጽ አቻቸው ጋር በጋራ ሆነው ተናገሩት ተብሎ የወጣው ዘገባ የአንድ ወገን አስተያየት ነው፣ በመሆኑም የሶማሊያ መንግስት በይፋ ስለ ህዳሴው ግድብ ያወጣው መግለጫ እንደሌለም ተገልጿል። 

ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም ✍ ትኖሪያለሽ ገና የጥንት ውበትሽ እንደነበረ፣ ሠምና ወርቅሽ እንደከበረ፣ በህብር ታጥሮ እንደሠመረ፣ ዘመን ተሻግሮ እየዘመረ። ይልቃል ገና! ገና! የአንቺማ አላማ፣ የጀ
+9
ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም ✍ ትኖሪያለሽ ገና የጥንት ውበትሽ እንደነበረ፣ ሠምና ወርቅሽ እንደከበረ፣ በህብር ታጥሮ እንደሠመረ፣ ዘመን ተሻግሮ እየዘመረ። ይልቃል ገና! ገና! የአንቺማ አላማ፣ የጀግኖች ደም ነው ውህድሽ ግርማ፤ እኮ ይሄ ድምቀትሽ ስንቶችን ያማለለው፣ ከአለም ድረስ ዘልቆ ከፍ ብሎ ሚውለበለበው፤ ማይዛነፍ ማይታጠፍ ይህ ልሳነ ሠንደቅ፣ በሶስት ቀለማቶች ተውቦ ቀለሙ የማይለቅ፤ አርማው መሀል ገብቶ፣ እኩልነት ሠጥቶ፤ በፍቅር ያስዋጀን፣ ብዙ የሚያስቃኘን፣ ሩቅ የሚያስጉዘን፣ ሠንደቅ አላማችን፤ በተተኪው ትውልድ ዝቅ ላትይ እንደነበርሽ፣ ትኖሪያለሽ ገና! ገና! በድል ጎዳና እንደደመቅሽ። ቀለመወርቅ አዳነ

የአማፂው ህውሃት ቡድን ለድርድሩ ቅድመ ሁኔታ በማስቀመት በጊዜ ገደብ ተፈፃሚ ካልሆነ ወደ ጦርነት እንደሚገቡ ተናገሩ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደረጋል ለተባለው ድርድር ወይም
የአማፂው ህውሃት ቡድን ለድርድሩ ቅድመ ሁኔታ በማስቀመት በጊዜ ገደብ ተፈፃሚ ካልሆነ ወደ ጦርነት እንደሚገቡ ተናገሩ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደረጋል ለተባለው ድርድር ወይም ውይይት ቅድም ሁኔታ እና የጊዜ ገደብ መቀመጡን የአማፂው የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል ተናገሩ። ጦርነቱ በሰላማዊ እና ፖለቲካዊ ውይይት እንዲጠናቀቅ ፍላጎታቸው መሆኑንንም ተቅሰው በዋነኛነት የሚመሩት አሜሪካኖች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ “የሰላም ውይይቱን ለመጀመር አስቀድሞ መሰረታዊ አገልግሎቶች ተመልሰው መከፈት አለባቸው” ብለዋል። “ሕገ መንግሥትን መሰረት ያደረገ ድርድር ለማካሄድ ዝግጁ ነን” ያሉት ዶ/ር ደብረጽዮን ውይይቱን እየተከታተሉ ነው ላሏቸው አሜሪካኖች፤ “አገልግሎት የሚጀመርበትን ጊዜ ቁርጡን ንገሩን። ቃላቸውን የሚጠብቁ ካልሆነም እንዲሁም ያስቸገራቸው ነገር ካለም እንዲነግሯቸው ለመጨረሻ ግዜ የጊዜ ገደብ ሰጥተናቸዋል የማይመልሱ ከሆነም ለኛ መልስ ነው። እንዳልፈለጉ እንቆጥረዋለን የሚመልሱ ከሆነ ደግሞ ስለ አፈፃፀሙ እናወራለን። ዝም ብለን መጠበቅ የሚባል ነገር የለም።” ብለዋል። ተሰጠ ያሉት የጊዜ ገደብ ለምን ያህል ጊዜ እንደሆና ባይናገሩም፤ ካልሆነ ግን ወደ ውጊያ እንደሚገቡ ገልፀው ማስጠንቀቃቸውን ተናግረዋል። በዚህ የህወሓት መሪ አስተያየት ላይ ከዩናይትድ ስቴትስ በኩል የተሰማ ቀጥተኛ ምላሽ የለም። ምንጭ፦ ቪኦኤ

ጀግናቹ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል በኦሪገን የአለም ሻምፒዮና የተሳተፋት አትሌቶቻችን 4 የወርቅ፣ 4 የብር እንዲሁም 2 የነሀስ በድምሩ 10 ሜዳልያዎችን በማስገኘት፣ ይህ ውድድር ለኢትዮጵያ በሜ
+8
ጀግናቹ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል በኦሪገን የአለም ሻምፒዮና የተሳተፋት አትሌቶቻችን 4 የወርቅ፣ 4 የብር እንዲሁም 2 የነሀስ በድምሩ 10 ሜዳልያዎችን በማስገኘት፣ ይህ ውድድር ለኢትዮጵያ በሜዳልያ ብዛት በታሪኳ ቀዳሚ እንዲሆን አስችለዋል። አትሌቶቹ ረቡዕ ማምሻውን አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፤ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ከፍተኛ የመንግስት ባለ ስልጣናት የአበባ ጉንጉን በመያዝ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የባህል እና ስፖርት ሚንስቴር በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ አትሌቶቹ እዚያው ቦሌ በሚገኘው ስካይላይት ሆቴል የሚያርፉ እንደሚሆን አስታውቋል። በመቀጠል በወጣው መረሐ ግብር መሰረት ሀሙስ ጠዋት አትሌቶቹ ከላይ ክፍት በሆነ አውቶብስ በከተማይቱ ዋና ዋና ጎዳናዎች በመዘዎወር ከህዝቡ ጋር ደስታቸውን እንደሚካፈሉ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። በዚህም መሰረት አትሌቶቹ ጠዋት ከ2:30 ጀምሮ ያረፋበትን ስካይላይት ሆቴልን መነሻ በማድረግ፤ በቦሌ መንገድ አድርገው፤ ወደ መስቀል አደባባይ፤ ከዚያም በሂልተን ሆቴል አድርገው ወደ አራት ኪሎ፤ ቀጥለውም ከአራት ኪሎ ወደ ፒያሳ፤ ከፒያሳም ቸርችል ጎዳናን ይዘው ቁልቁል ወደ ለገሀር የሚያቀኑ ይሆንና፤ በኋላም ወደ መስቀል አደባባይ መልሰው በመዞር፤ በስተመጨረሻ በቤተ መንግስት የሽልማት ስነስርአት እንደሚኖር የሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ጨምሮ ገልጿል። የከተማው ህዝብ አትሌቶቹ በሚዘዋወሩበት ጎዳናዎች ላይ በመገኘት ደማቅ አቀባበል ያደርግላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። #Ethiopia #Oregon2022 #WorldAthleticsChamps #TeamEthiopia

" ጀግኖቻችን በሰላም ገብተዋል " በዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮናው ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን ዛሬ ምሽት በሰላም አዲስ አበባ ገብቷል። ልዑካን ቡድኑ
+3
" ጀግኖቻችን በሰላም ገብተዋል " በዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮናው ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን ዛሬ ምሽት በሰላም አዲስ አበባ ገብቷል። ልዑካን ቡድኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገዋል። ነገ በተመረጡ የመዲናችን አካባቢዎች ህዝቡ በዓለም መድረክ ሀገራችንን #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ከፍ ላደረገው የአትሌቲክስ ቡድን አድናቆቱን በመግለፅ አቀባበል ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። #ENA @tikvahethiopia

የምስራቅ አምበሶች🙏
የምስራቅ አምበሶች🙏

ጀግኖቹ አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሰዋል::
ጀግኖቹ አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሰዋል::

የሱዳን የአብዬ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ታሪካዊ ዳራ 🙏 ወቅቱ እንደ አዉሮፓዉያን ዘመን ቀመር በ1919 ዓ.ም 63 የአለማችን ሃገራት በጥምረት ከአንደኛዉ አለም ጦርነት ማግስት የአሁኑን የተባበሩት መንግስታት የቀድሞውን ሊግኦፍኔሽን መሰረቱ፡፡ አላማዉም በአለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ ግጭቶችንና ወረራዎችን በመከላከል የሃገራትን የጋራ ደህንት መጠበቅ የድርጅቱ ዋነኛ ተልዕኮ ነበር፡፡ በወቅቱ ሊግኦፍኔሽ ከመሰረቱሃገራት መካከል ከአፍሪካ ግምባር ቀደም ኢትዬጵያ ነበረች፡፡ ለዓለም አቀፍ ህግና ስርዓት መገዛት ቅድሚያ የሰጠችዉ ሃገራችን በወቅቱ በድርጅቱ ለጋራ ደህንነት /Collective security/ መጠንከር በአለም_አቀፍ መድረክ ለአለም ሰላም አለኝታነቷን አሳየች፡፡ ከድርጅቱ ምስረታ ማግስትም ሃገራችን ኢትዬጵያ የመጀመሪያዋን አለም አቀፍ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በ1945ዓ.ም ወደ ኮሪያ አዘመተች፡፡ በዚሁ ሁኔታ የተጀመረዉ የሃራችን ኢትዬጵያ የአለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በኮንጎ ፣ በላይቤሪያ ፣ በሩዋንዳ ፣ በቡሩንዱ ፣ በሱዳን ዳርፉር ፣ በሶማሊያ ፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ፣በሱዳን አብዬ ግዛት ሰራዊቱን አሰማርታለችል፡፡ የአብዬ ተልዕኮ ታሪካዊ ዳራ የሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ታሪካዊ ድልድይ ተደርጋ የምትወሰደው አብዬ 10 ሺህ 460 ከ.ሜ የመሬት ስፋት ሲኖራት ዋና ከተማዋም አብዬ ታዉን የሚባል ሲሆን በዋነኝነት የአካባቢዉ ነዋሪዎች የሚጠቀሙባቸው የመግባቢያ ቋንቋዎች አረብኛ እና እንግልዝኛ ናቸዉ፡፡ አብዬ አዲስ በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት ግዛቷ በጊዜአዊነት ከደቡብ ኮርዶፋን/የደቡብ ሱዳን ግዛት/እስከ ሰሜን ሱዳን ሰሜናዊ ባህር ኤላ-ጋዚል/የሰሜን ሱዳን ግዛት ድረስ የሚሸፍነዉን ክልል ይይዛል፡፡ የአብዬ ግዛት የይገባኛል ጥያቄ የሰላም ስምምነቱን አደጋ ዉስጥ በማስገባቱ ከሪፍረንደሙ በኋላ የሚከሰተዉን አደጋ ለማስቀረት አለም አቀፍ የዳኞች ቡድን የአብዬ ግዛት ድንበር እንደገና ለማደስ ወስኗል፡፡ በአለማችን ታሪክ ሁለተኛ ረዥ ጊዜ የወሰደዉን የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም እ.ኤ.አበ2004 ዓ.ም ስምምነት ተፈራረሙ ፡፡በዚህ ታሪካዊ ስምምነት /CPA/ መሰረት በልዩ አስተዳደራዊ ደረጃ የተሰጣት አብዬ በደቡብ ሱዳን መንግስት የይገባኛል ጥያቄ ቢቀርብበትም ይህ የነዳጅ ምንጭ የሆነዉ አካባቢ በሰሜን ሱዳን ወታደሮች ቁጥጥር ስር ወድቆ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ሰሜን ሱዳንና ደቡብ ሱዳን ወደ ወ/ዊ ግጭት አምርተዉ በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎች ከቤት ንብረታቸዉ እንዲፈናቀሉና ለህልፈተ ሂወት እንዲደረጉ ምክንያት ሆኟል፡፡ሁለቱም ሃገራት በቀድሞ በደቡብ አፍሪካዉ ፕሬዘዳነት ታቦ ኢንቤኪ ሸምጋይነት ስምምነት በመድረሳቸዉ ሰሜንና ደቡብ ሱዳን መንግስት አዲስ የሰላም ስምምነት ሰኔ 20ቀን 2003ዓ.ም በአዲስ አበባ እንዲፈራረሙ ተደረገ፡፡ ይህ የሰላም ስምምነት ዋና ዓላማ አድርጎ የተነሳዉ ዳግም የሁለቱን ሱዳኖች ጦር ሰራዊት ከ አብዬ አካባቢ ጠቅልለዉ እንዲወጡና አካባቢዉ ከሁለቱም ሃገራት ጦር ሰራዊት ነፃ እንዲሆን ነበር፡፡ ሁለቱም መንግስታት ይህን ሃሳብ መቀበላቸዉን በፊርማቸዉ አረጋገጡ፡፡ በተጨማሪም በዚህ ነፃ ቀጠና ማለትም በአብዬ አካባቢ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሃይል እንዲሰማራና የአካባቢዉን ሰላምና ፀጥታ ማረጋጋት ስራ እንዲሰራ ከስምምነት ተደረሰ፡፡ በዚህም መሰረት የተባበሩት መንግስታት ሃላፊዎች በአብዬ አካባቢ የሚሰማራዉ የሰላም አስከባሪ ጦር ከሁሉም ሃገሮች የተዉጣጣ መሆን አለበት የሚለዉን ሃሳብ ሲያቀርቡ የሰሜንና የደቡብ ሱዳን መንግስት ተወካዬች ግን የተመድ ተወካዬች ያቀረቡትን ሃሳብ አልተቀበሉትም፡፡ በዚህም ምክንያት በሁለቱም ሱዳኖች መንግስታት የየራሳቸዉን ሀሳብ እንዲያቀርቡ እድል ተሰጣቸዉ፡፡ ሁለቱም መንግስታትም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአብዬ ቀጠና የኢትዬጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ሰራዊት ካልሆነ የሌላ ሃገር ሰራዊት እንዲገባ አንፈቅድም በማለት ተስማሙ፡፡ በሁለቱም ሱዳን መንግስታት ስምምነት መሰረትም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታ የሰላም መፍትሄ አስፈላጊ ኮሚሽን ማለትም ማለትም፡-The UN Security Council Resolution 1990 authorized aunited4250/የኢትዬጵያ ሰላም አስከባሪ ጦር ሰራዊት በአብዬ ቀጠና ሰላምና ፀጥታን ለማረጋጋት እንዲሰማራ በወሰኑት መሰረት የኢትዬጵያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት ተሰማራ፡፡ ይህ የኢትዬጵያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት ተልዕኮ ከሌሎች ከሰላም ማስከበር ተልዕሎዎች በሁለት አብይት ነጥቦች ይለያል፡፡ እነርሱም፡- 1ኛ.የኢትዬጵያ ሰራዊት የሰላም አስከባሪ ሃይል 2.3 ስኬዌር ኪ.ሜ ይሸፍናል። ከተመድ ከሁሉም ከሰላም አስከባሪ ተልዕኮዎች ሲለካም በትልቅነቱ ስለሚጠቀስ ብቻ ሳይሆን የሚሸፍነዉ የማረጋጋት አካባቢ በመልክዓ_ምድራዊ ስፋት በትልቅነቱ የሚታወቅ መሆኑ ነዉ፡፡ 2ኛ. ሌላዉ ሴክተሩ የሚመራዉ በኢትዬጵያዉያን ጀኔራል መኮንኖች ነዉ፡፡ የአንድ ሃገር ሰራዊት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በብቸኝነት መሰማራቱ እና ይህ ተልዕኮ የኢትዬጵያ ሰራዊት በአለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ማስከበር ተልዕኮዉን በፅናት እና በዲሲፕሊን በአለም ህዝብ እና መንግስት እየተመሰከረለት መምጣቱ የሚያሳይ ነዉ፡፡ የፀጥታዉ ምክር ቤት እ ኤ አ ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባሳለፈዉ ዉሳኔ መሰረት ሁሉም ጣታቂ ሃይሎች ከአብዬ ግዛት መዉጣታቸዉን ማረጋገጥ ጨምሮ የአብዬን የተመድ ጊዜአዊ የፀጥታ ሃይልዉክልና የማስፈፀም ተልዕኮ ለሴክተሩ አዛዥ ለጄነራል መኮንኖች ተሰጣቸዉ፡፡ ዛሬ በአብዬና ቀጠናዉ አንፃራዊ ሰላም ሰፍኗል፡፡ ህዝቦች በሰላም ወጥተዉ በሰላም ይገባሉ አልፎ አልፎ በሚሲሪያ እና ዲንካ ጎሳዎች በሚከሰቱ ግጭቶች ና የእንስሳት ዝርፊያዎች መጠነኛ መፈናቀሎች ቢኖሩም ከዚህ በፊት በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶች ህዝባዊ ባህሪዉ ከሃገር አልፎ ድንበር በተሸገረዉ በሰራዊታችን ጥረት መንገዶችና ድልድዬች የተሰሩ ሲሆን የጥገና ስራዎችም ተሰርተዋል። ት/ትቤቶች ፣ ክሊኒክ ፣ ሆስፒታል እና የመሳሰሉት የመሰረተ ልማት ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ በአጠቃላይ በአብዬ ቀጠና በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን መልሶ በመገንባት ረገድ የሰላም ተመራጭ ሀይል የሆነው የሃገራችን የሰላም አስከባሪ ሰራዊት የሰላም ተምሳሌትና ህዝባዊ ሰራዊት መሆኑን በተግባር አስመስክሯል፡፡ ቤተሰብ ይሁኑ! 👇👇👇👇👇👇👇👇 #Join https://t.me/Commando_and_AirBorne_Battleship

ኢትዮጵያ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለመሸጥ ተስማማች። ለዓመታት ድርድር ሲደረግበት የቆየው የኢትዮ- ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ድርድር ትናንት ማምሻውን በስምምነት መጠናቀቁን የ
ኢትዮጵያ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለመሸጥ ተስማማች። ለዓመታት ድርድር ሲደረግበት የቆየው የኢትዮ- ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ድርድር ትናንት ማምሻውን በስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል። ስምምነቱን የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የኢፌዲሪ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ በተገኙበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኬንያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር ጎፌሪ ሙሊ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ ኢትዮጵያ አሁን ላይ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለመሸጥ የሚያስችላት ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን እስከ 400 ሜጋ ዋት ከፍ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ጅቡቲ ጋር የኃይል ሽያጭ እያካሄደች ሲሆን ከሶማሌ ላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ስምምነት ፈርማለች፡፡ የግንባታ ሥራው በ2008 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮ-ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ መጠናቀቁ ይታወሳል።

የቀድሞው የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝደንት የቶማስ ሳንካራን ቤተሰቦች ይቅርታ ጠየቁ የቀድሞቀው ፕሬዝዳንት ኮምፓውሬ በስልጣን ዘመኔ ለፈጸሙት በደል ሁሉ ይቅርታ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል የቀድሞው የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት ብሌስ ኮምፓውሬ የቶማስ ሳንካራ ቤተሰቦችን ይቅርታ ጠየቁ፡፡ በተቀሰቀሰባቸው ህዝባዊ ተቃውሞ ከስልጣናቸው በመልቀቅ በስደት ይኖሩ የነበሩት ብሌስ ኮምፓውሬ አሁን በስልጣን ላይ ያለው ወታደራዊ መንግስት ባደረገላቸው ምህረት ወደ ኦጋዲጉ ተመልሰዋል፡፡ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ በሰጡት መግለጫ “በስልጣን ዘመኔ ቡርኪናቤዎች ላይ ለፈጸምኩት በደል ተጸጽቻለሁ፣ በተለይ የቶማስ ሳንካራ ቤተሰብ ይቅርታ እንዲያደርግልኝ እጠይቃለሁ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የ71 ዓመቱ የቀድሞው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት በፈረንጆቹ 2014 ላይ በህዝባዊ አመጽ ከስልጣን የለቀቁ ሲሆን ወደ ጎረቤት ሀገር ኮቲዲቯር ተሰደው ይኖሩ ነበር፡፡ በዚህ ክስ ምክንያትም የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው ብሌስ ኮምፓውሬ ቶማስ ሳንካራን እንዳልገደሉ በተደጋጋሚ ሲናገሩ ቢቆዩም በመጨረሻም ስለ ፈጸሙት በደል ሁሉ ቤተሰባቸው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው በይፋ ጠይቀዋል፡፡ የቡርኪናፋሶ የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት የነበሩት ቶማስ ሳንካራ ከ34 ዓመት በፊት ነበር የተገደሉት። የሚወዳት ሀገሩን እየመራ የነበረው ቶማስ ሳንካራ አሰቃቂ በተባለ ግድያ ህይወቱ ቢያልፍም በበርካታ አፍሪካውያንና የአፍሪካ ወዳጆች ስሙ ጎልቶ ይነሳል። አፍሪካዊው ቼ ጉቬራ እየተባለ የሚጠራው ሳንካራ እንዲገደል አሲረዋል በሚል የተጠረጠሩ 14 ሰዎች ችሎት ቀርበው የሀገሪቱ ፍርድ ቤት በግድያ ወንጀሉ ዙሪያ ከሁለት ወር በፊት ፍርድ መስጠቱ ይታወሳል፡፡ የቶማስ ሳንካራ ባለቤት ከ34 ዓመታት በኋላ የሳንካራ ገዳዮች የፍርድ ሂደትን ስትጠብቀው የነበረ ሁኔታ እንደነበር ገልጻ መንግስት ወደ ሀገራቸው የተመለሱት የቀድሞቀው ፕሬዝዳንት ኮምፓውሬን እንዲያስርላቸውም ጠይቀዋል፡፡ 

የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ሞሐመድ ከሱማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አቋርጠው የገቡት የአልሸባብ ታጣቂዎች ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በሸበሌ ዞን ፌርፌር ወረዳ አ
የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ሞሐመድ ከሱማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር አቋርጠው የገቡት የአልሸባብ ታጣቂዎች ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። በሸበሌ ዞን ፌርፌር ወረዳ አካባቢ የተማረኩ የአልሸባብ ታጣቂዎች ራሳቸውን "የኢትዮጵያዊያን ሙጃህዲን" በማለት እንደሚጠሩ የገለጡት ሙስጠፋ፣ አልሸባብ ታጣቂዎቹን የላከው በኦሮሚያ ክልል ባሌ ተራሮች ለመመሸግ እንደነበር ተናግረዋል። የአልሸባብ የቀድሞ አመራሮች በበኩላቸው፣ ቡድኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያደርገውን የሽብር እንቅስቃሴ የሚመሩት ዓሊ ዲያር የተባሉ የሱማሌ ክልል ተወላጅ መሆናቸውን ለቪኦኤ ሱማሌኛ ክፍል መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።