የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 461
المشتركون
-40724 ساعات
-2 4147 أيام
-2 42630 أيام
أرشيف المشاركات
በደሴ ከተማ አስተዳደር ህዝባዊ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፋ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ከጧቱ 12ሰአት ጀምሮ ወደ ሆጤ ሜዳ ልዩ ልዩ መፈክሮችን በማሰማት እየተመመ ይገኛል ። ሰልፉ በሆጤ ስታድዩም መልዕክት ተላልፎ ይጠናቀቃል ተብሎ ይገመታል።
# መፈክሮቹ (የዕለቱ መልዕክቶች)
1. መንግስት በተደጋጋሚ የሚያደርገውን የሰላም ጥሪ እንደግፋለን!
2. በደምበጫ በገርጨጭ፣ በላሊበላና በሌሎች አካባቢዎች ንፁሃንን የጨፈጨፉ ፅንፈኛ ሀይሎች ለህግ ይቅረቡልን!
3. ክልላችንን የሰላምና የልማት ማዕከል ለማድረግ ሁላችንም ለሰላም ዘብ እንቆማለን!
4. መንግስት ህግ በማስከበር የንፁሃን ሰዎችን ገዳዮች ለህግ ያቅርብልን!
5. መንግስት ለሰላም መስፈን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች እንደግፋለን!
6. በደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ከተማ ፅንፈኛው ሀይል በንፁሀን ላይ የፈፀመውን ዘግናኝ ጭፍጨፋና ግድያ በፅኑ እናወግዛለን!
7. ንፁሀንን በግፍ እየገደሉ በአስከሬናቸው መነገድ አረመኔያዊነት ነው!
8. የልማት ማዕከል የነበረውን ክልላችንን የጦርነት ቀጠና ለማድረግ የሚሠራው ሥራ የባንዳነትና የፅንፈኝነት ጥግ ነው!
9. ንፁሀንን በግፍ መጨፍጨፍ የአረመኔነት ጥግ ስለሆነ ሊወገዝ ይገባዋል!
10. ለክልላችን የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይሆን ሰላም እና ልማት ነው!
11. ፅንፈኛ እና ተላላኪዎች ከባዕዳን ተልዕኮ ወጥተው የሰላምን አማራጭ ሊከተሉ ይገባል!
12. ሰላም የጋራ ሀብት ነው፤ በጋራ ይለማል በጋራ ይጠበቃል!
13. መንግስት ህግ በማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ሊያስጠብቅ ይገባል!
14. ፅንፈኛው ሀይል በንፁሃን ላይ የሚፈፅመው ግድያ፣ ማገትና ማፈናቀል ሊቆም ይገባል!
15. መከላከያ ሰራዊታችን፣ የፌዴራል የፀጥታ ሀይሎች እና የክልላችን የፀጥታ ሀይሎች ለከፈሉት ዋጋ ክብር እንሰጣለን!
Dessie City Administration Communication
ኢትዮጵያ ክሪፕቶ ከረንሲን ለመገበያያነት ለመጠቀም የሚያስችል መመሪያ ልታወጣ እንደምትችል የብሔራዊ ባንክ ገዢ ጥቆማ ሰጡ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ “የክሪፕቶ አሴትን” እና የዲጂታል ገንዘብን በኢትዮጵያ መጠቀም የሚያስችል መመሪያ ወደፊት ሊያወጣ እንደሚችል የተቋሙ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።
ብሔራዊ ባንክ መመሪያውን የሚያወጣው በማዕከላዊ ባንኪንግ፣ በገንዘብ ፖሊሲ እና በገንዘብ አስተዳደር ያሉ ዓለም አቀፍ “ለውጦችን” እና “እድገቶችን” እያየ መሆኑን አቶ ማሞ ተናግረዋል።
አቶ ማሞ ይህን ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአዋጅ ማሻሻያ ዛሬ ማክሰኞ ታህሳስ 8፤ 2017 በተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀበት ወቅት ከፓርላማ አባል ለቀረበ ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ ነው።
የአሁኑ አዋጅ ካካተታቸው አዳዲስ ድንጋጌዎች መካከል ክሪፕቶ ከረንሲ እና የዲጂታል ገንዘብን መጠቀም የተመለከተው አንዱ ነው።
አዋጁ “አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ብሔራዊ ባንክ ካልፈቀደ በስተቀር፤ ክሪፕቶ ከረንሲ ወይም ሌላ ማንኛውንም ዲጂታል ወይም የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ በመጠቀም ክፍያ መፈጸም አይችልም” ሲል ክልከላ ያስቀምጣል።
አዋጁን በመተላለፍ በእነዚህ መንገዶች ክፍያ የፈጸመ ማንኛውም ሰው፤ ከሶስት ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት እና ከአስር ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ እንደሚቀጣም ተደንግጓል።
በሞስኮ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ የሩሲያ የኒውክሌር ኃይል አዛዥ ተገደሉ
ዛሬ ማክሰኞ ማለዳ በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ አንድ አፓርትመንት ሕንፃ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ፤ የሩሲያ ጦር የራዲዮሎጂካል፣ ኬሚካል እና ባዮሎጂካል ኃይል አዛዥ ሌተናንት ጄኔራል ኢጎር ኪሪሎቭ ከረዳታቸው ጋር መገደላቸው ተገልጿል፡፡
ኢጎር እና ረዳታቸው የተገደሉት ከክሬምሊን በስተደቡብ ምስራቅ 7 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከሚገኘው የመኖሪያ አፓርትመንታቸው ውጭ በደረሰ ፍንዳታ ነው ተብሏል።
ጄነራሉ የተገደሉት በመኖሪያ ቤታቸው መግቢያ ላይ በኤሌክትሪክ ስኩተር ላይ በተጠመደና ቤት ውስጥ የተሰራ ቦንብ መሆኑን በሩሲያ መንግሥት የሚተዳደረው ታስ የዜና ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡ ሌተናንት ጄኔራል ኢጎር፤ በኮስትሮማ ከፍተኛ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የኬሚካል መከላከያ ትምህርት ቤት ወታደራዊ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን፤ ከፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 ጀምሮ የጦር ኃይሉን እንዲመሩ ተሹመዋል።
ጄኔራሉ የሩሲያ ጦር የራዲዮሎጂካል፣ ኬሚካል እና ባዮሎጂካል ኃይል አዛዥ ጨምሮ ከአደገኛ ፈንጂዎች ጋር በተዛመደ በሩሲያ ወታደራዊ ኃይል ውስጥ በተለያዩ ሚናዎች አገልግለዋል። በትላንትናው ዕለት የዩክሬን የደህንነት አገልግሎት ዩክሬን ውስጥ የተከለከለ የኬሚካል ጦር መሳሪያ ተጠቅመዋል ሲል ጄኔራል ኢጎርን ከሶ ነበር፡፡የዩክሬን የደህንነት አገልግሎት በኪሪሎቭ መሪነት ሩሲያ 5 ሺሕ ያህል የኬሚካላዊ መሳሪያዎችን ተጠቅማለች ሲል ተናግሯል።
ሌተናንት ጄኔራል ኢጎር "በዩክሬን በሩሲያ ጦርነት ላይ አውዳሚ ኬሚካል ጦር መሳሪያዎች ተጠቅመዋል" በሚል በብሪታኒያ፣ ካናዳ እንዲሁም በሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ማዕቀብ ተጥሎባቸው ቆይቷል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሳምንቱ መጨረሻ ኢትዮጵያን እና ጁቡቲን ይጎበኛሉ ተባለ
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት በኢትዮጵያ እና ጁቡቲ ጉብኝት እንደሚያካሂዱ ተገለጸ።
ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ታህሳስ 12 እና 13 ቀን 2017 ዓ.ም በሚኖራቸው ቆይታ ከጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እና ከሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ተጠቁሟል።
ማክሮን በተጨማሪም በአዲስ አበባ በፈረንሳይ ድጋፍ የታደሰውን የብሔራዊ ኢዮቤልዩ ቤተመንግስትን መርቀው ለጎብኚወች ክፍት እንደሚያደርጉ ከካፒታል ጋዜጣ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
የፈረንሳይ አለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (AFD) ለብሔራዊ ኢዮቤልዩ ቤተ መንግስት እድሳት 12 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ ማድረጉ የተጠቆመ ሲሆን ከአንድ አመት ተኩል እድሳት በኋላ በማክሮን ተመርቆ ክፍት ይሆናል ተብሏል። የመጀመሪያው ዙር የቤተመንግስቱ እድሳት አጠቃላይ 20 ሚሊዮን ዩሮ ይፈጃል የተባለ ሲሆን ትኩረቱም ለጎብኙዎች ክፍት በማድረግ የቱሪስት መስህብ እንዲሆን ማስቻል መሆኑም ተጠቁሟል።
የቤተ መንግስት አስተዳደር የእድሳቱን ስራ በፈረንሳይ ባለሞያተኞች እና በዘርፉ ልምድ ያላቸው ድርጅቶች እየታገዘ ክትትል እና ቁጥጥር ሲያደርግ እንደነበር የጠቆመው ዘገባው ባለሞያተኞቹ የፈረንሳዩን ታሪካዊ ቬርሳይል ቤተመንግስትን ጨምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ ልምድ ያላቸው መሆናቸውን አመላክቷል።
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአምስት አመታት በፊት መጋቢት 3 እና 4 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጉብኝት ማካሄዳቸው ይታወሳል፣ የሳምንቱ መጨረሻ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለሁለተኛ ግዜ ይሆናል።
#CapitalNews የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ማክሮን አዲስ የታደሰዉን ብሔራዊ ቤተመንግሥት ሊመርቁ ነዉ
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአምስት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ቀንድ ሊመለሱ ሲሆን ከታህሳስ 11 እስከ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. በጅቡቲ እና አዲስ አበባ ጉብኝት እንደሚያርጉ ተሰምቷል።
በዚህ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ማክሮን አዲስ የታደሰውን ብሔራዊ ቤተመንግስትን በታህሳስ 12፣ 2016 ዓ.ም. የሚያስመርቁ ሲሆን ይህም ከአንድ አመት ተኩል ያህል ሰፊ እድሳት ከተደረገ በኋላ መሆኑ እንደ ትልቅ ምዕራፍ እንደሚያሳይ ተመላክቷል።
የመጀመርያው የኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ተብሎ የሚጠራው ይህ መዋቅር እ.ኤ.አ. በ1955 ዓ.ም የአፄ ኃይለ ሥላሴ የብር ኢዮቤልዩ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሰየመ ሲሆን ታሪካዊ ፋይዳው ቢኖረውም ቤተ መንግሥቱ ለሕዝብ ተደራሽ ባለማድረግ ለፕሬዚዳንቱ ይፋዊ መኖሪያ ሆኖ እና የመንግሥት ሥራ የሚካሄድበት ቦታ ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል።
የብሄራዊ ቤተ መንግስት እድሳት የፈረንሳይ መንግስት የኢትዮጵያን ባህላዊ ቅርሶች ለመደገፍ የገባው ቁርጠኝነት አካል ሲሆን ይህ ጅምር ፕሬዚደንት ማክሮን እኤአ በ 2019 አዲስ አበባን ከጎበኙ በኋላ ተጠናክሯል ።
የህወሓት ክንፍ ግፍ ተቆጥሮ አያልቅም!!
በመቐለ ከተማ ውጥረት ነግሷል ፤ በፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የተሾመ የመቐለ ከንቲባ ወደ ፅህፈት ቤቱ እንዳይገባ በነጀነራል ታደሰ ወረደ የሚመራው የህወሓት ጦር የመቐለ መዘጋጃ ቤትን መክበቡ ተሰምቷል ።
መላው ክልሉን ለማመሳቀል የተነሳው የደብረፅዮን ህወሓት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶች፣ አረጋውያንና እናቶች ሳይቀር ከፈጀ በኋላ አሁን የክልሉ ስልጣን ለመያዝ እየተፍጨረጨረ ይገኛል፡፡
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው‼️
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን፣ በኢትዮጵያና ሱማሊያ ይፋዊ ጉብኝት ሊያደርጉ ማቀዳቸውን አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን በኹለቱ አገራት ጉብኝት ለማድረግ ያቀዱት፣ ከቀጣዩ ጥር እስከ የካቲት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ እንደኾነ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ የገለጡት፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ከሶማሌላንድ ራስ ገዝ ጋር በተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ሳቢያ በኹለቱ አገራት መካከል በባሕር በር ዙሪያ የተፈጠረውን ዲፕሎማሲያዊ ቁርሾ አንካራ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይንና ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድን በማሸማገል በፈቱ ማግስት ነው።
የኢትዮጵያ ሠራዊት ለሶማሊያ ሠላም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 06 ቀን 2017 ዓ.ም
እኛም እንሰዋ ደማችንም ይፍሰስ የቀብር ሳጥናችን ባንዲራዋን ይልበስ የምንኖረው ለሷ ክብር የምንሞተው ለሀገር ዳር ድንበር ለዜጎች ሰላም መረጋገጥ ስለሆነ ድካማችን ፍሬ አልባ ሁኖ አያውቅም።
ከመላው ኢትዮጵያ ተጠራርተን አንዲት እሷን ብለን በአንድ በልተን በአንድ ጠጥተን በአንድ ተዋግተን አላማ አጋምዶን የሰሜኑ ደቡብ የምዕራቡ ምስራቅ የኦሮሚያው የአማራ የትግራይ የጋምቤላው ሽናሻ የአፋር ሱማሌ በቻ በአጠቃላይ ከ4ቱ ማዕዘን ተሰብስበን ኢትዮጵያን የምናስከብረው ልጆቿ እልፍ ነን።
እልፍነታችን ውጤታማ ነው አንድም ቀን ከስሮ አያውቅም ፈረሱ ሲሉን አለን ተበተኑ ሲሉን እንበዛለን ገደልናቸው ሲሉን አሸንፈናቸው እንገኛለን። በዘመናዊ የሚዲያ ጦርነታቸው ታሪካዊዎቹ ጠላቶቻችን የሚለጥፉልን የሀሰት ስም ቀደን በመጣል ሁሌም የእናት ኢትዮጵያን ክብር የማይወዱ አካላትን አሳፍረን ድል እየተቀዳጀን እንገኛለን እኛ።
የህዝቦችን አንድነት ለማስቀጠል የሀገርን ሉአላዊነት ላለማስደፈር በምንከፍለው መስዋዕትነት ውስጥ ሁሌም ቢሆን ተቋማችን መከላከያም ይሁን ወገናችን አሳፍረን አናውቅም ብዬ በድፍረት ብናገር ሀቅ ነው።
ከራሳችን ሀገር አልፈን ጎረቤታችን ሶማሊያን መጠነ ሰፊ መስዋዕት በመክፈል እንደ ሀገር ራሷን ችላ መንግስት ኑሯት እንድትቀጥል ያደረገው ሰራዊታችን ከራሱም አልፎ ለጎርቤት ተቆርቋሪ መሆኑን አስመስክሮ ዛሬ ላይ አድርሷታል።
ተቋማችን መከላከያ ጎሬቤቴ ቤት የጨሰው ጭስ ነገ እሳት ሁኖ ተቀጣጥሎ ለእኔም ነው በሚል እሳቤ ከሽብርተኞች ጋር ተዋግቶ የሶማሊያ ዜጎች እፎይታ እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር በቀጠናው ሰላም እንዲሠፍን አስችሏል።
በብርሃኑ አባተ
‹‹ወደቡን ኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ እንድትጠቀምበት ሐሳብ አቅርበናል፣ አሁንም ድረስ የኢትዮጵያን ምላሽ እየተጠባበቅን ነው››ጂቡቲ
የጂቡቲ መንግሥት የኢትዮጵያና የሶማሊያን ውጥረት ለማርገብ ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ የታጁራን ወደብ በማስተዳደር እንድትጠቀምበት ያቀረበው ሐሳብ እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን አስታወቀ።
የጂቡቲ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሐመድ ዓሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽንን ለመምራት እየተደረገ ባለው ውድድር ላይ ዕጩነታቸውን በሚመለከት፣ አዲስ አበባ በሚገኘው የአገሪቱ ኤምባሲ ሐሙስ ታኅሳስ 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ ወቅት ነው ይህ የተነገረው።
አገራቸው ለኢትዮጵያ ያቀረበችውን ወደብ አስመልክቶ ከሪፖርተር ጥያቄ የቀረበላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹ወደቡን በጋራ ለማስተዳደርና ኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ እንድትጠቀምበት ሐሳብ አቅርበናል፣ አሁንም ድረስ የኢትዮጵያን ምላሽ እየተጠባበቅን ነው፤›› ብለዋል።
ሚኒስትሩ በነሐሴ ወር አገራቸው ኢትዮጵያ ወደቡን እንድትጠቀምበት የሚለውን ሐሳብ ባቀረበችበት ወቅት በሰጡት ማብራሪያ፣ ‹‹በአሁኑ ወቅት ከታጁራ ወደብ የሚገባንን ጥቅም እያገኘን አይደለም። በሁለት ወራት ውስጥ አንድ መርከብ ብቻ ነው እያስተናገደ የሚገኘው። የጂቡቲ መንግሥት ይህንን ወደብ ለመገንባት 60 ሚሊዮን ዶላር ወጪ አድርጓል። ከታጁራ ወደብ እስከ ባሎህ ግዛት ድረስ ያለውን መንገድ ለመገንባት ደግሞ 110 ሚሊዮን ዶላር ወጪ አድርጓል። በታጁራ ወደብ ለሠራተኞች ደመወዝ እየተከፈለ ያለው ከዶላሌ ወደብ ከሚገኝ ገቢ ነው። ይህ መሆኑ ትክክል ነው ትላላችሁ? አይደለም፤›› ማለታቸው ይታወሳል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቱርኪዬ አመቻችነት ባለፈው ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና በሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሸኪህ መሐመድ መካከል ስምምነት በመፈረሙ መደሰታቸውን ገልጸው፣ ድንበራቸው በየብስ የተከለለ አገሮች በዓለም አቀፍ ሕግጋት መሠረት የባህር በር የማግኘት መብት ላይ ያላቸውን ምልከታም አብራርተዋል።
‹‹የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የባህር በር ማግኘትን የተመለከተው ኮንቬንሽን በጣም ግልጽ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው። ወሰናቸው በየብስ የተከበበ አገሮች ነፃ፣ መተንበይ የሚቻልና ያልተደናቀፈ የባህር በር የማግኘትና የመጠቀም መብት አላቸው። በዓለም አቀፉ የሕግ ማዕቀፍ መሠረት የእነዚህ አገሮች መብት በትክክል በተግባር ላይ እንዲውል ጠንክረን መሥራት ያለብን ይመስለኛል፤›› ብለዋል።
ሚኒስትሩ አገራቸው ለኢትዮጵያ የታጁራ ወደብን በአማራጭነት ማቅረቧንም አስታውሰዋል። ‹‹የባህር በር ተጠቃሚነትን በተመለከተ ጂቡቲ ከጎረቤቶቿ ጋር በአጋርነትና በትብብር ለመሥራት ሁሌም ክፍት ናት። ነገር ግን በአገሮች መካከል የሚደረጉ የግልግል ዳኝነቶች በዓለም አቀፍ ሕጎች መሠረት መከናወናቸው ጠቀሜታው የላቀ ነው፤›› ብለዋል።(ሪፖርተር)
💎
ከብርጋዲየር ጄኔራል ካሣ ወልደሰማዕት ጋር በወታደራዊ ህይወታቸው ዙሪያ የተደረገ ቆይታ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
በ1928 ዓ.ም የካቲት ወር በኢሊባቡር ክፍለ ሀገር በጎሬ ከተማ ተወልደዋል፡፡ ወደ ሚወዱት የውትድርና ሙያ በ1949 ዓ.ም ተቀላቅለዋል። በሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤት በ17ኛው የዕጩ መኮነንነት ኮርስ በመሳተፍ ተገቢውን ወታደራዊ ሳይንስም ወስደዋል፡፡
በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በመዘዋወር የተሰጡ ግዳጆችን በብቃት በመወጣት ለ34 ዓመታት ሀገራቸውን በታማኝነትና በጀግንነት ከምክትል መቶ አለቃ እስከ ብርጋዲየር ጄኔራል ድረስ በተለያዩ የአመራርነት ዕርከን አገልግለዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ አልፎ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ወታደራዊ ትምህርት ተምረዋል ተልዕኮዎችንም በብቃት ፈፅመዋል፡፡
በተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ጦር በኮንጎ እና የህይወቴ ጉዞ የሚል መጽሐፍም ለንባብ አብቅተዋል ብርጋዲየር ጄኔራል ካሣ ወልደሰማዕት፡፡ ብዙ የሚነገር የሚዘከር ታሪክ አላቸው
ብርጋዲየር ጄኔራል ካሳ ኢትዮጵያዊነት ከምንም ከማንም በላይ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ አንድ ስለሆነች ልዩ ፍቅር አለኝ ከሚገልፀው በላይ ዕንቁ ናት፡፡ ውትድርና ህይወቴ ነው፡፡ ውትድርና ውድ ህይወትን ደም አጥንትን ለሀገር ሉዓላዊነት ለህዝቦች ክብርና ሠላም ተብሎ የሚሰጥበት ልዩ ሙያ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለውጭ ሀገራት ዋጋ የሚከፍል ጀግና ወታደር ያላት ሀገር ናት፡፡ ሀገር የሚከበረው በወታደርና በውትድርና ነው ሲሉ ሙያዊ የህይወት ተሞክሯቸውን ይገልፃሉ፡፡
መከላከያ በሪፎርሙ በትጥቅ ፣በአደረጃጀት ፣ በሰው ሀይል እና በሁሉም ዘርፎች ከፍተኛ ለውጥ አስመዝግቧል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያን የሚያሰጋ ሀይል አለ ብየ አላምንም ተቋሙን ለዚህ ያበቁ መሪዎች ሊመሰገኑ ይገባቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግና የማይነጥፍባት ሀገር ከመሆኗ ባሻገር አስተማማኝ እና ጠንካራ ደጀን ያላት ሀገር ናት፡፡ አሁንም ህዝቡ የሚሰዋላትን መከላከያ በመደገፍ አንድነቱን ማጠናከር ይገባል እላለሁ ሲሉም ጄኔራል መኮንኑ ሃሳባቸውን አጋርተዋል፡፡
ሠላም እጅግ ወሳኝ ነገር እና የሁሉም ነገር መሠረት ነው፡፡ እኛ ከሀገራችን አልፈን በኮንጎ ለሠላም ዋጋ ከፍለን መጥተናል፡፡ ሠራዊቱም በተለያዩ አካባቢዎች እና ሀገራት ለሠላም ዋጋ እየከፈለ ይገኛል፡፡ በታጠቀ ጦር ብቻ ሠላምን ማስፈን አይቻልም፡፡ ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባዋል፡፡ የሠላም ጥሪ የሚደረግላቸው አካላትም ወደ ሠላም መንገድ መጥተው ለኢትዮጵያ ሠላምና አንድነት በጋራ መቆም ይገባቸዋል ሲሉም ይመክራሉ፡፡
ብርጋዲየር ጄኔራል ካሣ ወልደሰማዕት ለኢትዮጵያ ሠላሟን ፣አንድነቷን እና ብልፅግናዋን አብዝቼ እመኛለሁ ሀገራችን ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ሠራዊቱ በጀግንነት እየተወጣ ያለውን ተልዕኮ አጠናክሮ በመቀጠል የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጎ ማውለብለብ እንዳለበትም አምናለሁ ሲሉ ሀገር ወዳድነት መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷ ተከብሮ ፣ዳር ድንበሯ ተጠብቆ ለዛሬ የደረሰቸው እንዲሁ በከንቱ አይደለም ብዙ ዋጋ ተከፍሎላት ነው፡፡ ስለዚህ መከላከያ ሠራዊቱ ፣ ሌሎች የፀጥታ አካላት እና መላው ኢትዮጵያዊ የቀደምት አባቶቹን ገድል እያሰበ ዘር ፣ብሔር ፣ቋንቋን ሳይለይ በአንድነት ፣በፍቅር ፣በመቻቻል እና በመተሳሰብ ኢትዮጵያን በክብር ማስቀጠል እና ለትውልዱ ማሻገር ይገባል ሲሉም ብርጋዲየር ጄኔራል ካሣ ወልደሰማዕት ተናግረዋል።
ብርጋዲየር ጄኔራል ካሣ ወልደሰማዕት በ34 ዓመታት የውትድርና አገልግሎት ቆይታቸው ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ አለም አቀፍ ተቋማት ሜዳሊያዎች፣ ሠርተፊኬቶች እና ዲፕሎማዎች ተበርክቶላቸዋል፡፡
ሀገራችንን ከሚያኮራ ታሪክ ፣ከሚያስመሰግን ባህል ፣ከሚያስከብር ጀግንነት ጋር ያስረከቡንን አባቶቻችንን ሁል ጊዜ ልንዘክር በሕይወታችን ልንገልፃቸው ልናወድሳቸው ይገባል፡፡ ጀግና ሲታወስና ሲወደስ እልፍ ጀግና ይፈጠራልና፡፡
ኢትዮጵያና ዩጋንዳ በወታደራዊዉ መስክ በጋራ ለመሥራት ተሥማሙ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የዩጋንዳ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙሖዚ ኬንሩጋባ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
የሁለቱ አገራት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሞች በተለያዩ ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያም በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
ከውይይቱ በሗላ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሁሉም ወታደራዊ አቅሞቻችን በጋራ ለመስራት ተስማምተናል ነው ያሉት።
እንደ ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ማብራሪያ በመረጃ፣ በወታደራዊ ኢንዱስትሪ፣በስልጠና እና መሰል ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ስምምነት ደርሰዋል።
ዩጋንዳና ኢትዮጵያ ረጅም አመታትን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ከስደተኞች ጋር በመመሸግ ወንጀል የሚፈፅሙ አካላትንም ለመለዋወጥ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውን ተናግረዋል።
የዩጋንዳ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም
ጄነራል ሙሖዚ ኬንሩጋባ በበኩላቸው ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበልና የኢትዮጵያ መንግስት ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ ስለጋበዛቸው ምስጋና አቅርበዋል።
ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በተለያዩ ወታደራዊ መስኮች በትብብር የሚሰሩት ስራዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።
ዘጋቢ በላቸው ክንዴ
ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ሕግ አንጻር …
በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት መነቃቃት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ የራሷ ወደብ እንደሌላት ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች አንዳቸው የሌላኛቸውን ሉዓላዊነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት እንዲሁም በተባበሩት መንግሥታት እና በአፍሪካ ሕብረት ደንቦች ላይ የሰፈሩ ዓለም አቀፍ ሕጎችን ለማክበር ተስማምተዋል።
ይህን የአንካራ ስምምነት ተከትሎ የሕግ ባለሙያው አንዷለም በእውቀቱ÷ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከሶማሊያ ጋር የተፈራረመችው ስምምነት የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ሕግ አንጻር ወሳኝ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር በአፍሪካ የባሕር በር ከሌላቸው ሀገራት ሕዝብ 33 በመቶውን እንደሚሸፍን በተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጉዳዮች የ2024 ሪፖርት ያመለክታል ብለዋል።
ለሺህ ዓመታት የቀይ ባሕር ገናና ሀገር የነበረችው ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የነበራትን የባሕር በር ማጣቷንም አውስተዋል፡፡
ይህን ተከትሎም የቀጣናው ቁልፍ እና በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በዘላቂነት የራሴ የምትለው የባሕር በር አጥታ ወደ ጎረቤቶቿ ለማማተር መገደዷን ነው የጠቀሱት፡፡
በአንካራው ስምምነት ሁለቱ ሀገራት በወዳጅነትና የመከባበር መንፈስ ያለፉ ልዩነቶችን እና አወዛጋቢ ጉዳዮችን ወደ ኋላ በመተው በትብብር ለጋራ ብልጽግና ወደፊት ለመሥራት መስማማታቸውን በማድነቅ ትክክለኛ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ በቨርሳይ ስምምነት ፈረንሳይ፣ ብሪታኒያ፣ አሜሪካና ወቅቱ ሶቪዬት ሕብረት የኤርትራ ዕጣ ፈንታን ሲወስኑ የኢትጵያን የባሕር በር የማግኘት መብት ግምት ውስጥ ሊገባ እንደሚገባ አቋማቸውን ማንጸባረቃቸው ለጉዳዩ የሰጡትን ትኩረት ያሳያል ነው ያሉት፡፡
የሶማሊያን የግዛት አንድነት ባከበረ ሁኔታ ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር መተላላፊያ ማግኘቷ የሚኖረውን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታን ሁለቱ ሀገራት ዕውቅና እንደሚሰጡም ተገልጿል፡፡
በሉዓላዊ የሶማሊያ መንግሥት ስር ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ዘላቂ የባሕር መተላላፊ እንድታገኝ የሚያስችል ለሁለቱም ሀገራት ጠቃሚ የሆኑ የኮንትራት፣ የኪራይ፣ እና ተመሳሳይ የንግድ አሠራር መንገዶችን በጋራ በመሆን ለማጠናቀቅ ተስማምተዋል።
ይህን ስምምነትም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ የአውሮፓ ሕብረት እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ደግፈውታል፡፡
FBC
#aa_prosperity
