የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 461
المشتركون
-40724 ساعات
-2 4147 أيام
-2 42630 أيام
أرشيف المشاركات
ኢትዮጵያና ኡጋንዳ‼
የኡጋንዳ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙሆዚ ካኒሩግባ አዲስ አበባ ናቸው።ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ መምከራቸውን ሰምተናል።
ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ከስደተኞች ጋር መሽገው ወንጀል የሚፈፅሙትን በጋራ ለመከላከልና ለመስራት መግባባት ላይ መድረሳቸውም ተሰምቷል።ዚህም ሁለቱ ሀገራት የፀጥታ መረጃ መቀያየር፣ ሁሉን አቀፍ ስልጠና እንዲሁም ለቀጣናው ሰላም በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተዘግቧል።
💎
የድሮን ጥቃት በጎጃም ፅንፈኛውን እምሽክ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
“ለኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ” ጅቡቲ
ጅቡቲ ኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄዎችን ለማስተናገድ በሯ ክፍት መሆኑን አስታወቀች፡፡
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና መሃሙድ አሊ የሱፍ በአዲስ አበባ የጅቡቲ ኤምባሲ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በቅርቡ ለሚደረገው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ምርጫ እጩ ሆነው ቀርበዋል፡፡
በመግለጫቸው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ሆነው ቢመረጡ ሊሠራቸው የሚያሰቧቸው ሥራዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የባህር በር ካላቸው ሀገራት በምን መልኩ መጠቀም እንደሚችሉ የሚገልጽ የአለም አቀፍ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ያነሱት የጂቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ አሊ የሱፍ፤ ኢትዮጵያም ዓለም አቀፍ ህጎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የጅቡቲን ወደቦች መጠቀም እንደምትችል አንስተዋል፡፡
ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የታጁራ ወደብን ኢትዮጵያ እንድታሰተዳድር ግብዣ አቅርባ ነበር ፡፡ ጅቡቲ አሁንም ቢሆን የወደብ ስምምነቶችን ለማድረግ በሯ ክፍት መሆኑን ጠቁማለች፡፡
በመግለጫቸው ኢትዮጵያና ሶማሊያ በቱርክ አደራዳነት በአንካራ ከስምምነት መድረሳቸውንም ጂቡቲ በደስታ አንደምትቀበል አስታውቀዋል። ስምምነቱ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላም እና መረጋጋትን ለማስፈን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነርነት እጩ የሆኑት የጂቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ አሊ የሱፍ፤ የህብረቱ ኮሚሽነር ቢሆኑ ለወጣቶች እና ሴቶች ተሳትፎ ፤ ለሠላም እና መረጋጋት ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ጠቁመዋል፡፡
#ጂቡቲ #ወደብ #የባህር_በር #የባህር_በር_ለኢትዮጵያ #Djibouti #landlocked #seaaccess #AfricanUnion
የኢትዮጵያና የሶማሊያ ስምምነት ለቀጠናው ሠላም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 03 ቀን 2017 ዓ.ም
ኢትዮጵያና ሶማሊያ ረዥም ደንበር የሚጋሩ በበርካታ ማህበራዊ ጉዳዮች የተግባቡና አንድ የሆነ ባህላዊ እሴቶች ያሏቸው የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ናቸው።
ከዚያድባሬ መንግስት ውድቀት ወዲህ ሠላም የራቃት በተለይም ደግሞ የምስራቅ አፍሪካ አሸባሪ ቡድን በሆነው አልሻባብ ሠላሟን እየተገፈፈች በአጥፍቶ ጠፊዎች ዜጎቿን እየተነጠቀች የአሸባሪው መፈንጫ ሆና ሠላም እንደናፈቃት ዛሬ ላይ ደርሳለች።
ለጎረቤት ሀገራት የሠላም እጦት ፈጣን መፍትሄዊ ምላሽ የምትሰጠው ኢትዮጵያም ባለፋት አሥራ ሁለት አመታት የሠላም አሥከባሪ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ ግዛት በመላክ ለወንድም የሱማሌ ህዝብ ሠላም ዕውን መሆን እንዲሁም ለቀጠናው ሠላም ማረጋገጥ ተልዕኮዎችን እየፈፀመች መጥታለች።
የኢትዮጵያ ሠራዊት አሁን ላይም በሶማሊያ ሠላም የማሥከበር ተልዕኮውን እየተወጣ ይገኛል። ከተልዕኮው በተጓዳኝ በህዝባዊ ወገንተኝነቱ አርአያ ሆኖ የሚነሳው የኢትዮጵያ ሠራዊት የሶማሊያ ህዝብ የውሃ እጥረት ሲያግጥመው በቦቲ በማድረስ ለተቸገሩትም የዕለት ደራሽ ምግብ በማቅረብ ወንድማዊ አጋርነቱን እያረጋገጠ በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅነትን ያገኘ ነው።
ባለፉት አሥራ ሁለት አመታት ለሶማሊያና ለህዝቦቿ ሠላም መሥዋዕትነት በመክፈል ጭምር አጋርነቱን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ወታደር ለሶማሊያ መንግስት እንቅፋት ሆኖ የቀጠለውን አልሸባብ በመደምሰስና የሶማሊያ ሀገረ መንግስት እንደ መንግስት እንዲቆም የተደረገው አሥተዋፅኦ በሶማሌያዊያን ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ ተሰጥቶታል።
እውነታው ይህ ሆኖ እያለ የሁለቱን ሀገራት ቅርበትና ወዳጅነት በማለያየት ለራሳቸው ማትረፍ የፈለጉ ጥቂት ሀገራት "ከእኛ በላይ ለሶማሊያ አሳር ነው" የሚል ግን ያልሆነ ሊሆንም የማይችል ጩኸት በማሥተጋባት ልዩነትን የመፍጠር ሴራ ተጠምደው ሥለመቆየታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።
የዛሬው ሰበር ዜና "ኢትዮጵያና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ለማደስ ተስማሙ" ሲል እነኛ የተንኮል ክብሪት ጫሪ ሀገራት ምን ይሰማቸው ይሆን? መልሱን ለእንናተው ልተው።
በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና በሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሙሃመድ በቱርካ አሸማጋይነት ኢትዮጵያና ሶማሊያ የደረሱት ስምምነት በሁለቱ ሀገሮች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ምእራፍ ለመውሰድ የሚያሥችል ነው።
ሁለቱ ሃገራት የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ በቀጣይ አራት ወራት በቱርክዬ አስተባባሪነት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር እና መሰል አሰራሮች ላይ ለመግባባት ተስማምተዋል።
በእርግጥም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ይቅርና ለመላው አለም ሰላም መረጋገጥ የምታደርገው አሥተዋፅኦ በብዙዎች ዘንድ መረጋገጡ በተግባር የታዬ እውነታ ሥለመሆኑ የዛሬው የሁለቱ ሀገራት ስምምነት አንዱ ማሣያ ነው።
እናም የኢትዮጵያና የሶማሊያ የሁለትዮሽ ሥምምነት ለህዝቦቻቸው ሠላም እና ልማት መልካም ዜና ነው። የእነኛ ሴረኛ ሀገራት እጣ ፈንታስ ምን ይሆን ?
በውብሸት ቸኮል
#BREAKING #Update
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ምን ተስማሙ ?
በቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ስምምነቱ " የአንካራ ስምምነት " ተብሏል።
ይህ ተከትሎ በወጣው የስምምነት ሰነድ የተስማሙባቸው ጉዳዮች በዝርዝር ተቀምጠዋል።
ምንድናቸው ?
➡️ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያ መሪዎች አንዳቸው ለሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ፣ አንድነት ፣ነፃነት እና የግዛት አንድነት ለማክበር ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።
➡️ በወዳጅነት እና በመከባበር መንፈስ ልዩነቶችን እና አከራካሪ ጉዳዮችን በመተው ፤ በመተጋገዝ ለጋራ ብልጽግና ለመስራት ተስማምተዋል።
➡️ ሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለከፈሉት መስዋዕትነት እውቅና ሰጥታለች።
➡️ ኢትዮጵያ የሶማሊያን የግዛት አንድነት ባከበረ ሁኔታ የባህር በር ተጠቃሚ መሆኗ / ወደ ባህር እና ' ከ ' ባህር / ሊያስገኝ የሚችለው ልዩ ልዩ ጥቅም ላይ ተማምነውበታል።
➡️ ሁለቱንም ተጠቃሚ ባደረገ ሁኔታ የንግድ ውል ይታሰራል።
➡️ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና እና ቀጣይነት ያለው / ዘላቂ የባህር በር መዳረሻ / አክሰስ እንዲኖራት ስምምነት ላይ ተደርሷል ፤ ይህም በሉዓላዊ የሶማሊያ መንግሥት ስልጣን ስር የሚተገበር ነው።
ለዚህም የሚሆን ፦
- የኮንትራንት
- የሊዝ ውልን ጨምሮ ሌሎች ሞዳሊቲዎች ላይ በቀጣይ በቅርበት አብሮ ለመስራትና ለማጠናቀቅ ተስማምተዋል።
ለነዚህ ዓላማዎች መሳካት በጥሩ እምነት ከየካቲት 2025 መጨረሻ በፊት የቴክኒካል ድርድር ለመጀመር ወስነዋል። ይህም በቱርክ አመቻችነት የሚሳለጥ ሲሆን በ4 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ስምምነት ይፈረማል።
ለዚህም ቁርጠኝነትና ለቃል ኪዳኑ ተግባራዊ መደረግ የቱርክን እገዛ በደስታ ተቀብለዋል።
➡️ በአተገባበር ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ ' እንደአስፈላጊነቱ ' በቱርክ ድጋፍ ለመፍታት ቃል ገብተዋል።
#TikvahEthiopia
+1
ሁሌም መዘጋጀት የሠላም ፍላጎት ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 02 ቀን 2017 ዓ.ም
መከላከያ የሀገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች መልክ ይዞ ሀገሩ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልክ የተገነባ ነው። ለሁሉም ወገኑ የሚሠራ ሁሉንም የሚያኮራ ተቋም ነው። መካላከያ ማለት የሀገር ጋሻ መከታ ዋልታና ማገር ብቻ ሳይሆን ምልክትም ነው።
ከወታደር ተግባራት አንዱ ሁሌም ለጦርነት መዘጋጀት ነው።ለውጊያ መዘጋጀት ማለት ሠላም መጥላት አይደለም። በተቃራኒው ጦርነትን በሩቅ ለማስቀረት ከመጣም የከፋ ጉዳት ሳያስከትል ለመርታት ነው።
ሠራዊታችን የሠላም ዋጋ በሚገባ የሚገነዘብ ለዜጎች ሠላም ወጥቶ መግባት ዕድገትና ከፍታ ዘብ የሚቆም ነው። ትልቁ ደስታና እፎይታው ከአብራኩ የወጣው ወገን እርካታ ነው።
መከላከያ ጨርስኩ ብሎ የሚያቆመው ሥራ የለውም። የአቅም ግንባታው ፤ሙያው እይታው ፤የብቃት ከፍታው እያደር የሚጨምር ወደላቀ ደረጃ የሚሻገር አዳዲስ ትንታግ ሠንደቅ ዓላማ ዘቦችን የሚፈጥር ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሀገራዊ ፍቅሩ ፤ህዝባዊ ክብሩ ፤ሙያዊ ብቃቱ የማይላላው እምነቱ ፤ጀግንነትና ፅናቱ ፤ድል አድራጊነቱ አብሮት የሚኖር ዘመናትን የሚሻገር ነው ብለናል። ሁሌም የሚዘጋጀው ከጦርነት ናፍቆት ሳይሆን ለፍፁም ሠላማዊ ሀገር እውነት ካለው ተቋማዊ ፍላጎት ኃላፊነት ነው።
በፈይሳ ናኔቻ
+3
#Berbera
የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስቴር ዛሬ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ መጀመሩን ገልጿል።
የሶማሌላንድ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አብዲረሺድ ኢብራሂም ደግሞ " የሶማሌላንድ መንግሥት በበርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ አስጀምሯል " ሲሉ ይፋ አድርገዋል።
" ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ምዕራፍ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ ውጥን ቀጠናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ሶማሌላንድ ያላትን ቁርጠኝንተ ያሳያል ሲሉ አክለዋል።
ቢሮው በወደቡ የሚራገፉ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ መዳረሻዎች እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው ተብሏል።
በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን በይፋዊ ማስጀመሪያ ስርዓቱ ላይ ወደቡን የሚያስተዳድረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትሱ DP World በርበራ ዋና ስራ አስፈፃሚ ስፓቺ ዋታንቫራቺ ተገኝተው እንደነበር ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ፤ " ይህ ቢሮ ወደቡ ላይ የሚራገፉ የተለያዩ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው " ብለዋል።
የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስትሩ ሳድ (ዶ/ር) " ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ግንኙነታቸው የተጠናከረ ነው ፤ 120 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ አማራጭ ወደቦችን መጠቀም ትችላለች " ማለታቸውን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
Photo Credit : #SomalilandFinanceDevelopment
+4
"ለማትደፈር ሀገር የማይበገር አየር ወለድ" በሚል መሪ ቃል 64ኛ አመት የአየር ወለድ ምስረታ እየተከበረ ነው፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
የአየር ወለድ ምስረታ በአሉ እየተከበረ የሚገኘው በቢሾፍቱ የአየር ወለድ ትምህርት ቤት ሲሆን በክብረ በአሉ ላይ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ የቀድሞ 102ኛ አየር ወለድ ክፍለጦር አዛዥ የነበሩ ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሀበተማሪያምን ጨምሮ የቀድሞ አየር ወለዶች አሁን በስራ ላይ የሚገኙ የአየር ወለድ አባላትና አሠልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
በመድረኩ ላይም የአየር ወለድን ታሪክን ያቀረቡት ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ የአየር ወለድ ሠራዊት በ1953 ዓ.ም የዛሬ ስልሳ አራት አመት መመስረቱን ገልፀው የአየር ወለድ ሠራዊት ለአንድ ሀገር አስፈላጊና ወሳኝ የሠራዊት ክፍል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አየር ወለድ በግዳጅ ጊዜ በመብራቅ አሊያም በንስር ወይንም በነብር ይመሰላል ያሉት ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፈዬ በችግር ጊዜ ለወገንና ለሀገር ፈጥኖ ደራሽም ነው ብለዋል፡፡
#BREAKING🚨
የበሽር አላሳድ አገዛዝ ተገረሰሰ።
የሶሪያው ፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ አገዛዝ ወደቀ። እሳቸውም ሀገር ለቀው ጠፍተዋል።
የታጠቁ የሶሪያ ተዋጊዎች የፕሬዚዳንት በሽር አል አሳድን የ24 ዓመት አገዛዝ ለመደምሰስ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ የተጠናከረ ወታደራዊ ዘመቻ እያካሄዱ ነበር።
በተለይም በሰሜናዊ ክፍል የሚገኙ የታጣቁ ተቃዋሚዎች ከረዥም ዓመታት በኋላ የአገሪቱ ጦር ላይ ድንገታዊ ጥቃት ከከፈቱ በኃላ ብዙ ቦታዎችን በፍጥነት ይዘዋል።
ከሳምንት በፊት ነው አሌፖን ዘልቀው የገቡት።
ከዛ በኃላ በመላ ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የመንግስት መከላከያዎች በአስደናቂ ፍጥነት ፈራርሰዋል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች የአማጽያኑን ምት መቋቋም ከብዷቸው ድንበር አቋርጠው ኢራቅ ለመግባትና ጥገኝነት ለመጠየቅ ተገደዋል።
ተቃዋሚዎቹ በቀናት ውስጥ እጅግ በርካታ ቁልፍ ከተሞችን እና ቦታዎችን ከአላሳድ አገዛዝ ነጻ ያደረጉ ሲሆን ለሊቱን የአሳድ መቀመጫ ወደ ሆናችው ደማስቆ መግባታቸው ታውቋል።
አላሳድ ከደማስኮ ወጥተው ሄደዋል ተብሏል።
የፕሬዜዳንቱን ከደማስቆ መልቀቅ ሁለት ከፍተኛ የጦር አመራሮች ለሮይተርስ አረጋግጠዋል።
አሁን ላይ አሳድ የት እንደገቡ የሚታወቅ ነገር የለም።
የታጠቁት ተቃዋሚዎች ባወጡት መግለጫ ፤ " ጨቋኙ በሽር አላሳድ ከደማስቆ ለቀው ሄደዋል " ብለዋል።
" ደማስቆን ከጨቋኙ በሽር አላሳድ ነጻ አውጥተናል " ሲሉም ገልጸዋል።
በሽር አላሳድ ሀገሪቱን ለቀው መጥፋታቸውንም አሳውቀዋል።
ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያውንም ተቆጣጥረውታል።
አንዳንድ ቪድዮዎች እንዲሁም ሮይተርስ የአይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ እንደዘገበው በደማስቆ ጎዳናዎች ሶርያውያን ወጥተው ' ነጻነት ! ነጻነት ! ' እያሉ መፈክር ሲያሰሙ ደስታቸውን ሲገልጹ ታይተዋል።
እነ ሩስያ ፣ ኢራን ፣ አሜሪካ እና ቱርክ ?
የአገዛዙ ዋነኛ አጋር የሆኑት ሩሲያ እንዲሁም ኢራን ለአሳድ ቀጣይነት ያለውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ሲያሳውቁ ቢሰነብቱም አገዛዙን ከመፍረስ አልታደጉም።
ሩስያ በዩክሬን በሚያደርገው ጦርነት የተጠመደች ሲሆን፣ ኢራን ደግሞ እስራኤል በሊባኖስ ሔዝቦላህ ላይ በከፈተችው ዘመቻ ምክንያት ተዳክማለች።
ጦርነቱ ሲባባስ ሞስኮ የሩሲያ ዜጎች አገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ ጥሪ ስታቀርብ ነበር።
በሶሪያ የረጅም አመታት የእርስ በርስ ጦርነት ዋና ተዋናይቷ አሜሪካም ብትሆን ሁኔታውን አይታ ዜጎቿን " በደማስቆ በረራዎች እስካሉ ድረስ " ሶሪያን ለቅቀው እንዲወጡ ስትጮህ ነበር።
ቱርክ በሶሪያ ያሉ አንዳንድ የታጠቁ ተቃዋሚ ቡድኖችን ትደግፋለች።
የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለወራት አሳድን ከተቃዋሚዎች ጋር ፖለቲካዊ መፍትሄ ላይ አንዲደርሱ ግፊት ሲያደርጉ ነበር።
ፕሬዜዳንቱ የተቃዋሚዎችን የቅርብ ጊዜ ግስጋሴ እንደሚደግፉ ተናግረው " አሳድ ጥሪዬን ቢቀበል ኖሮ ይህ አይከሰትም ነበር " ብለዋል።
#ሶሪያ : እ.ኤ.አ. ከ2011 ጀምሮ በተቃውሞ ስትናጥ ከቆየች በኃላ በከፋ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኝ ሲሆን በዚህም እጅግ በርካታ ሰዎች አልቀዋል። ሀገሪቱ እንዳልነበረ ሆናለች። ለሀገሪቱ እንዲህ መሆን የውጭ ኃይሎች አገዛዙን እና አማጽያንን በመደገፍ ረገድ ትልቅ ድርሻ አላቸው።
መረጃው ከአልጀዚራ፣ ሮይተርስ እንዲሁም ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።
#Update
" የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ ነው " - የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል
" ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ ነው " ሲል የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ።
ማዕከሉ እንዳስታወቀው የሲስተሙን ቮልቴጅ በማረጋጋት የተቋረጠውን ኃይል ደረጃ በደረጃ ለመመለስ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ነው።
በአዲስ አበባ በአንዳንድ አካባቢዎች እንዲሁም በክልል ከተሞች የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት መመለሰ መጀመሩን ገልጿል።
የተፈጠረው ችግር ሙሉ በሙሉ አልተፈታም።
ችግሩ ሙሉ በሙሉ እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት ተጠባበቁ ተብሏል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
