ar
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

الذهاب إلى القناة على Telegram

Addis abeba Ethiopia

إظهار المزيد
5 461
المشتركون
-40724 ساعات
-2 4147 أيام
-2 42630 أيام
أرشيف المشاركات
ማንነቱን ሰውሮ የቆየው ተዋጊ የሶሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነ -------- በሶሪያ አዲስ መንግስት በማዋቀር ላይ የሚገኘው ቡድን አሳድ ሃሰን አል ሻይባኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አድርጎ ሾመ። አዲ
ማንነቱን ሰውሮ የቆየው ተዋጊ የሶሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነ -------- በሶሪያ አዲስ መንግስት በማዋቀር ላይ የሚገኘው ቡድን አሳድ ሃሰን አል ሻይባኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አድርጎ ሾመ። አዲሱ ተሿሚ  ሶሪያን ከተቆጣጠረው  ሃያት ጣህሪር አል ሻም  ( HTS) ከተሰኘው ዋንኛ ወታደራዊ ቡድን መሪ አቡ መሃመድ አል ጁላኒ ጋር በመሆን በሃገሪቱ ይንቀሳቀስ የነበረው የአል ኑስራ ግንባር ( Al Nusera Front ) እስላማዊ ታጣቂ ቡድን መስራች ነው። አሳድ ሃሰን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት መሾሙን ተከትሎ ለአመታት ድብቅ የነበረው ማንነቱ አሁን በይፋ መገለፅ ጀምሯል። 38ኛ አመቱ ላይ የሚገኘው አሳድ የሶሪያን መንግስት ያስወገደው የሃያት ጣህሪር አል ሻም ፓለቲካዊ ጉዳዮች ሃላፊ ሆኖ ሲሰራ ነበር። አሳድ ሃሰን እአአ በ2009 ከደማስቆ ዩኒቨርስቲ በድግሪ ከተመረቀ ሁለት አመት በኋላ በሶሪያ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ አመፅ ተከትሎ የትጥቅ ትግል መጀመሩ ታውቋል። በአሻባሪነት ይፈለጉ ከነበሩ የቡድኑ ቁልፍ መሪዎች አንዱ የነበረ ሲሆን ቅርብ ጊዜ ድረስ " ዛይድ አል አታር " እና " አቡ አይሻ " በሚሉ ሃሰተኛ ስሞች  ይታወቅ ነበር።  አሁን ወደ መንግስት ሃላፊነት ሲመጣ ትክክለኛ ስሙ አሳድ ሃሰን አል ሻይባኒን እንደሆነ ታውቋል። አሳድ ፥ ስሙን ብቻ ሳይሆን መኖሪያ ሃገር ጭምር እየቀያየረ እስከ 2024 መጨረሻ በድብቅ ማንነት ይኖር እንደነበር የተገለፀ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜውን ያሳለፈው በቱርክ እንደነበር ተነግሯል።

የዕለተ ቅዳሜ፣ ታኅሳስ 12/2017 ዓ፣ም ዕለታዊ ዜናዎች 1፤ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዝዳንት ማክሮንን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሂደው የተቀበሉት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ከማክሮን ጋር "ፍሪያማ ውይይት" አደርጋለኹ ብለው እንደሚጠብቁ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ገልጸዋል። ፈረንሳይ፣ ኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ጣቢያ እንድትገነባ 100 ሚሊዮን ዶላር ለማበደር ከጥቂት ዓመታት በፊት መስማማቷ የሚታወስ ሲኾን፣ ኾኖም በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ከሦስት ዓመት በፊት የስምምነቱን ተግባራዊነት ማገዷ አይዘነጋም። ማክሮን አዲስ አበባ የገቡት፣ ዛሬ ወደ ጅቡቲ አቅንተው ከፕሬዝዳንት ኢስማኤል ጌሌ ጋር በኹለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተወያዩ በኋላ ነው። 2፤ ዓለም ባንክ፣ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማጠናከር የሚውል የ700 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጽድቋል። ከብድሩ 90 በመቶው የንግድ ባንክን ሒሳብ ለማስተካከልና ባንኩን መልሶ ለማዋቀር እንደሚውል ዓለም ባንክ ገልጧል። ከፊሉ ብድር ለብሄራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ማጠናከሪያና መዋቅራዊ ማሻሻያ እንደሚሰጥ ባንኩ ጠቅሷል። ብድሩ በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚለቀቀው፣ የባንኮቹ አፈጻጸም፣ የደንቦችና የመዋቅሮች ማሻሻያ ሂደት እየታየ የሚለቀቅ ነው። የብድሩ ዓላማ፣ የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግና ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለመ እንደኾነም ባንኩ ባሠራጨው አጭር መግለጫ አውስቷል። ንግድ ባንክ መዋቅራዊ ማሻሻያውን ከመተግበሩ በፊት፣ የቅርንጫፎችና የሠራተኛ ቅነሳን ጨምሮ ማሻሻያው ሊያስከትላቸው በሚችላቸው ማኅበራዊ ተጽዕኖዎች ዙሪያ በቅድሚያ ጥናት ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል። 3፤ የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤትና የዘርፍ ማኅበራት በቅርቡ ለሚያካሂደው የአዲስ ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንት እና ዋና ጸሃፊ ምርጫ ያቋቋመው የዕጩዎች አጣሪ ኮሚቴ በከተማዋ ንግድ ቢሮ ተጽዕኖ እንደፈረሰ ከምንጮች መስማቱን ሪፖርተር ዘግቧል። የንግድ ምክር ቤቱ አመራሮች በምክር ቤቱ ሕገ ደንብ መሠረት የተቋቋመውን የዕጩ አጣሪ ኮሚቴው ያፈረሱት፣ መንግሥት የራሱን ሰዎች በዕጩነት በማስገባት የንግድ ምክር ቤቱንና የዘርፍ ማኅበራትን የሥልጣን ቦታዎች ለመቆጣጠር በመፈለጉ እንደኾነ ምንጮቹ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በምክር ቤቱ ሕግ መሠረት በአመራርነት ምርጫ መሳተፍ የሚችሉት፣ በአባልነት የተመዘገቡና መዋጮ የሚያዋጡ አባላት ብቻ ናቸው። የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በበኩላቸው፣ ምክር ቤቱ መዋቅራዊ ማሻሻያ በማድረግና ሕገደንቡን በማሻሻል ሂደት ላይ መኾኑን ገልጠው፣ ቀጣዩ ምርጫ እስካኹን አባል ያልነበሩ አካላትን ጭምር ማካተት አለበት የሚል ጠንካራ ግፊት መኖሩንና በነባሩ አሠራር መቀጠል እንደማይቻል ተናግረዋል ተብሏል። 4፤ የሱማሊያዋ ፌደራል ግዛት ፑንትላንድ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ፣ ፑንትላንድ በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት የራሷን መገበያያ ገንዘብ ለማተም ማቀዷን አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ መንግሥታቸው የሱማሊያ ብሄራዊ መገበያያ የኾነውን ሽልንግ ሙሉ ለሙሉ ለመተው የወሰነው፣ የግዛቲቷን ኢኮኖሚ ለማሳደግ በማሰብ እንደኾነ ተናግረዋል። ፑንትላንድ፣ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ በመገበያያነት የምትጠቀመው የአሜሪካን ዴላር ነው። በሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያና በምርጫ ሥርዓት ዙሪያ ከፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ ፌደራል መንግሥት ጋር ውዝግብ ውስጥ የቆየችው ፑንትላንድ፣ ከወራት በፊት ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ግንኙነቷን ሙሉ በሙሉ ማቋረጧ አይዘነጋም። 5፤ አሜሪካ፣ በደቡብ ሱዳን ዘላቂ ሰላም እንዳይሰፍን እንቅፋት ኾነዋል ባለቻቸው በርካታ ባለሥልጣናትና ግለሰቦች ላይ የጉዞ ማዕቀብ ጥላለች። አሜሪካ የአገሪቱ ባለሥልጣናት ሙስናን ማስወገድ፣  የብዓዊ መብት ጥሰቶችን ማስቆምና ሰላም ማስፈን እንዳልቻሉ የጠቀሰችው አሜሪካ፣ በዚህ ሳምንት ደቡብ ሱዳን ሱዳናዊያን በመጀመሪያው ምርጫ መሪዎቻቸውን የሚመርጡበት ሳምንት ይኾናል ብላ ተስፋ አድርጋ እንደነበርና ኾኖም የአገሪቱ መሪዎች የሽግግር መንግሥቱን የቆይታ ጊዜ በድጋሚ በማራዘም ዕድሉን አባክነውታል በማለት ወቅሳለች። መንግሥት እና አማጺው ኃይል ከስድስት ዓመት በፊት የሰላም ስምምነት ተፈራርመው የብሄራዊ አንድነት የሽግግር መንግሥት ከመሠረቱ ወዲህ፣ አሜሪካ በአገሪቱ ባለሥልጣናት፣ ግለሰቦችና ቤተሰቦቻቸው ላይ ማዕቀብ ስትጥል ያኹኑ ሦስተኛዋ ነው። አሜሪካ የአዲሱ ማዕቀብ ዒላማ የኾኑትን ግለሰቦች ብዛትና ማንነት አልጠቀሰችም። [ዋዜማ] ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇 👇Telegram https://t.me/Commando_And_Airborne_Command 👉YouTube 👇 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36 Facebook 👇 https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force

ፑንትላንድ የራሷን መገበያያ ገንዘብ መጠቀም እንደምትጀምር ይፋ አደረገች --------- ከሶማሊያ ግዛቶች አንዷ የሆነችው ፑንትላንድ ከፈረንጆቹ አዲስ አመት ጀምሮ የራሷን መገበያያ ገንዘብ መጠቀም እ
ፑንትላንድ የራሷን መገበያያ ገንዘብ መጠቀም እንደምትጀምር ይፋ አደረገች --------- ከሶማሊያ ግዛቶች አንዷ የሆነችው ፑንትላንድ ከፈረንጆቹ አዲስ አመት ጀምሮ የራሷን መገበያያ ገንዘብ መጠቀም እንደምትጀምር ዛሬ አስታውቃለች። የግዛቷ ኘሬዝደንት ሰኢድ አብዱላሂ ዴኒ ዛሬ እንዳስታወቁት ከ2ዐ25 ጀምሮ የሶማሊያ ገንዘብ የሆነው የሶማሊያ ሺልግ በፑንትላንድ መገበያያነቱ ያበቃል ብለዋል። ኘሬዝደንቱ " በምትኩ የራሳችንን አዲስ ገንዘብ የምንጠቀም ሲሆን ይህም ጠንካራ እና ነፃ ኢኮኖሚን የመገንባት ፍላጎታችን አካል ነው " ሲሉ ተናግረዋል። በከፊል ራስ ገዝ የሆነችው ፑንትላንድ እና የሶማሊያ ፌደራል መንግስት መካከል ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተካረረ የመጣው አለመግባባት ለሶማሊያ አንድነት ትልቅ ፈተና ሆኗል። ልክ እንደ ሶማሌላንድ የነፃነት ጥያቄ በማንሳት እየተንቀሳቀሰች የምትገኘው ፑንትላንድ የሃሰን ሼህ መሃሙድ መንግስትን በፓለቲካ አሻጥር ፣ በጎሰኝነት ፣ በሙስና እና በስልጣን ጥመኝነት ትወነጅላለች። ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇

የአሜሪካ ለሶማሊላንድ ዕውቅና መስጠት የምዕራብ እስያን ጂኦፖለቲካ ይቀይረው ይሆን? *** በቅርቡ ሥልጣን የሚረከቡት ዶናልድ ትራምፕ ከየመን ጋር ለሚደረገው ጦርነት እንዲረዳቸው እና ቻይና በቀጣናው
+2
የአሜሪካ ለሶማሊላንድ ዕውቅና መስጠት የምዕራብ እስያን ጂኦፖለቲካ ይቀይረው ይሆን? *** በቅርቡ ሥልጣን የሚረከቡት ዶናልድ ትራምፕ ከየመን ጋር ለሚደረገው ጦርነት እንዲረዳቸው እና ቻይና በቀጣናው ላይ ያላትን ተፅዕኖ ለመቀነስ ሲሉ ለሶማሊላንድ ዕውቅና ለመስጠት ቢያቅዱም፤ እስራኤል በአካባቢው በምታደርገው ጦርነት የምዕራብ እስያ አጋሮቿን ሊያሳጣት እንደሚችል ይነገራል። የአሜሪካ ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ የሀገርነት ዕውቅና በመስጠት ብዙዎችን የሚያስገርም እርምጃ ለመውሰድ ማቀዳቸው ይነገራል። ይህ የትራምፕ ዕቅድ ይፋ የተደረገው በቀድሞው የብሪታንያ መከላከያ ሚኒስትር ጋቪን ዊልያምሰን ሲሆን፤ ውሳኔው በአፍሪካ ቀንድ እና በምዕራብ እስያ የባሕር መተላለፊያዎች ላይ ያለውን ጂኦፖለቲካዊ ሂደት በአስደናቂ ሁኔታ ሊለውጠው እንደሚችል ይገለጻል። ትራምፕ በዓረብ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ ለምትገኘው ሶማሊላንድ እውቅና መስጠት እ.አ.አ ከጥቅምት 2023 ጀምሮ ወደ እስራኤል የሚጓዙ መርከቦችን በዘጋው የየመኑ ሀውቲ አማጺ ላይ ለሚደረገው ጦርነት ለምዕራቡ ዓለም አዲስ ስትራቴጂያዊ መሠረት እንደሚሰጥ በማመን ነው። ይሁን እንጂ ይህ እንቅስቃሴ አሜሪካ ከሶማሊያ ጋር ጠንካራ ትስስር ያላቸው እንደ ግብፅ እና ቱርክ ካሉ ዋና ዋና የቀጣናው አጋሮች ጋር ያላትን ግንኙነት አደጋ ላይ እንደሚጥልም ስጋት ፈጥሯል።

ተመራጩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሶማሊላንድ ይሰጡታል ተብሎ የሚጠበቀው ዕውቅና …. ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ ይሰጡታል ተብሎ የሚጠበቀው ዕውቅና በቀጣናው ጂኦፖለቲካል ውስጥ
ተመራጩ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሶማሊላንድ ይሰጡታል ተብሎ የሚጠበቀው ዕውቅና …. ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሶማሊላንድ ይሰጡታል ተብሎ የሚጠበቀው ዕውቅና በቀጣናው ጂኦፖለቲካል ውስጥ ትልቅ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተመላከተ፡፡ ጉልህ በሆነ የጂኦ-ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ትራምፕ ሶማሊላንድን እንደሀገር ዕውቅና እንደሚሰጧት መታቀዱን የቀድሞ የብሪታኒያ የመከላከያ ሚኒስትር ጋቪን ዊሊያምሰን ሪፖርቶች ለመረዳት ተችሏል። ይህ ውሳኔ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የኃይል እንቅስቃሴ ሊለውጥ እንደሚችልም ነው እየተገለጸ የሚገኘው፡፡

አሜሪካ አዲሱን የሶሪያ መሪ ለመያዝ መድባ የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ሰረዘች አሜሪካ የሶርያውን መሪ አህመድ አል-ሻራ በቁጥጥር ስር ለማዋል ለመያዝ መድባው የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላ
አሜሪካ አዲሱን የሶሪያ መሪ ለመያዝ መድባ የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ሰረዘች አሜሪካ የሶርያውን መሪ አህመድ አል-ሻራ በቁጥጥር ስር ለማዋል ለመያዝ መድባው የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ከከፍተኛ ዲፕሎማቶች እና ከሃያት ታህሪር አል ሻም (ኤችቲኤስ) ተወካዮች ጋር ውይይት ካደረገች በኋላ ነው የሰረዘችው። ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባርባራ ሌፍ ከሻራ ጋር የተደረገው ውይይት "በጣም ውጤታማ ነበር" ካሉ በኋላ እርሱም "ለመወያየት ዝግጁ" ሆኗል ብለዋል። የአሜሪካ ልዑካን ቡድን ዋና ከተማዋ ደማስቆ የደረሰው የኤች ቲ ኤስ ታጣቂዎች የበሽር አል አሳድን መንግሥት ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ካስወገዱ በኋላ ነዉ። ዋሽንግተን አሁንም አማፂ ቡድኑን በአሸባሪነት እንደ ፈረጀች ነው። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ዲፕሎማቶቹ በአሜሪካ የሚደገፍ "የሽግግር መርሆዎች" ላይ፣ ቀጠናዊ ሁኔታዎች እንዲሁም አይኤስን የመዋጋት አስፈላጊነት ላይ መወያየታቸውን አረጋግጠዋል። ቃል አቀባዩ አክለውም፣ ባለሥልጣናቱ በአሳድ አገዛዝ ዘመን ስለጠፉት አሜሪካውያን ዜጎች፣ በ2012 በደማስቆ የተጠለፈውን ጋዜጠኛ ኦስቲን ቲስ ፣ እና በ2017 የጠፋውን ሳይኮቴራፒስት ማጅድ ካልማዝ በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን አስታውቀዋል። ጉብኝቱ ከአስር ዓመታት ወዲህ በደማስቆ ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገ መደበኛ የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት ነው። ይህ ጉብኝት በሶሪያ የአሳድ ከስልጣን መወገድን ተከትሎ የታየ ድንገታዊ ለውጥ ሲሆን፣ አዲስ ስልጣን የሚረከበውን መንግሥት የአረብ አገራት ድጋፍ ተጨምሮበት አሜሪካ እና አውሮፓ ተጽዕኖ ለማሳረፍ የወሰዱት እርምጃ ነው። ኢትዮ ኤፍ ኤም

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ዛሬ ምሽት ጅቡቲ ገብተዋል። ኢማኑኤል ማክሮን ጅቡቲ ሲደርሱ በሀገሪቱ ፕሬዝደንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ማክሮን በጅቡቲ ቆይታቸው በቀይ ባህር እና በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጋር እንደሚወያዩ ተገልፆአል። የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ከጅቡቲ ጉዟቸው በመቀጠል  ወደ ኢትዮጵያ በማምራት በአዲስ አበባ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋ እንደሚገናኙም ነው የተጠቆመው። ከቀናት በፊት የወጡ መረጃዎች ፕሬዝደንቱ በአዲስ አበባ ቆይታቸው ( ዕለተ ቅዳሜ) በፈረንሳይ መንግስት ድጋፍ እድሳት የተደረገለት የእዮቤልዩን ቤተመንግስት እንደሚመርቁ አመላክተዋል።

#INSA #NEWS ተቋማት ሳይውቁ አፈትልከው ሊወጡ ወይም ሊሰረቁ የሚችሉ መረጃዎች የትኞቹ ናቸው? ባለንበት የዲጂታል ዓለም የመረጃ (data) ሾልኮ መውጣት ወይም መሰረቅ ለተቋማት ከስጋቶቻቸው መካ
#INSA #NEWS ተቋማት ሳይውቁ አፈትልከው ሊወጡ ወይም ሊሰረቁ የሚችሉ መረጃዎች የትኞቹ ናቸው? ባለንበት የዲጂታል ዓለም የመረጃ (data) ሾልኮ መውጣት ወይም መሰረቅ ለተቋማት ከስጋቶቻቸው መካከል  አንዱና ዋነኛው ነው። የመረጃ መንታፊዎች ከተቋማት  "መረጃ" ብቻ አይሰርቁም፤  ለተቋማት የስራ እንቅስቃሴም ሆነ ለመልካም ዝና  ወሳኝ የሆኑ ንብረቶችም ጭምር የአጥቂዎች ኢላማዎች ናቸው፡፡ የመሰረቅ  ስጋት ውስጥ ያሉ  የተቋማት መረጃዎች የትኞቹ ናቸው?  1.  የድርጅት እና የፋይናንስ መረጃዎች፡- ሚስጥራዊ ሪፖርቶች፣ የገቢ መረጃዎች እና ትንበያዎች፤ 2.  የአእምሯዊ ንብረት እና የንግድ ሚስጥሮች፡- የተቋሙ የመወዳደሪያ አቅም  የጀርባ አጥንት የሆኑ ጉዳዮች፤ 3.  የደንበኞችን መረጃዎችን የያዙ  የመረጃ ቋት (Database)፡- ሚስጥራዊነት ያላቸው የደንበኛ ዝርዝሮችን ማጋለጥ፤ 4.  የግለሰቦችን ማንነት የሚያሳውቁ መረጃዎች (Personally identifiable information)፡- ግለሰቦችን ለአደጋ የሚያጋልጥ መረጃ፤ 5.  የተጠቃሚዎች  መረጃዎች፡- ያልተፈቀደ የስርዓቶች መዳረሻን መስጠት፤ 6.  የግል የፋይናንስ መረጃዎች፡- የክፍያ እና የመለያ (account) ዝርዝር መረጃዎች፤ 7.  የመልእክት (Mailing) አድራሻዎች፡- የማስገር (phishing) እና የማስመሰል (impersonation) ጥቃቶችን ማመቻቸት፤ 8.  የምስጠራ ቁልፎች፡ - የተመሰጠሩ ግንኙነቶች እና ስርዓቶች የመረጃ (data) ማጭበርበርን ለመከላከል ዘመናዊ  ደህንነታቸው የተጠበቁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም፣ መደበኛ የሳይበር ደህንነት  ኦዲቶችን ማድረግ፤ እንዲሁም በድርጅትዎ ውስጥ የሳይበር ደህንነት ግንዛቤ ባህል ማሳደግ ዋና ዋና የመከላከያ መንገዶች ናቸው፡፡

በአንካራው ስምምነት የታደሰው የኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት የአንካራው ስምምንት ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ስታቀርበው ለነበረው እና አብዛኛውን ጊዜ ትኩረት ሳያገኝ ለቆየው የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ የ
በአንካራው ስምምነት የታደሰው የኢትዮጵያ የባህር በር ፍላጎት የአንካራው ስምምንት ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ስታቀርበው ለነበረው እና አብዛኛውን ጊዜ ትኩረት ሳያገኝ ለቆየው የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ የሰጠ፣ በሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።  በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ጥናት ዳይሬክተር ጄኔራል ግዛቸው አስራት (ዶ/ር) በዚሁ ጉዳይ ላይ ባቀረቡት ጽሑፍ፣ “በሶማሊያ እና በቱርኪዬ እንዲሁም በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና ሀገራት እውቅና የተሰጠው ይህ ስምምነት፣ የኢትዮጵያን የባህር በር መሻት ሕጋዊነት ያረጋገጠ፣ ጉዳዩን በዓለም አቀፍም ሆነ ቀጠና አቀፍ መድረኮች ላይ ማንሣት እንደነውር ይቆጠር የነበረውን አስተሳሰብ የሰበረ ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የአፍሪካ ቀንድ የለውጥ እርምጃ መሆኑን ጠቁመው፣ በተለይ ደግሞ ለኢትዮጵያ ላለፉት 30 ዓመታት ሊደረስበት የማይችል ነው የተባለውን ግብ በማደስ ረገድ ሥልታዊ እመርታ ነው ይላሉ።

" መልሼ አጤነዋለሁ " - ሶማሊያ የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ መካተታቸውን በተመለከተ " መልሶ ለማጤን " ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል። አንድ የሶማሊያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ " የሶማሊያ መንግሥት ለልዑኩ ኅይል ከሚያዋጡት ሀገራት ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ወታደሮችን አግኝቶ ደልድሏል " ሲሉ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ አንዳቸው የሌላውን ሉዐላዊነት፣ እንዲሁም የግዛት አንድነት እንደሚያከብሩ አንካራ፣ ቱርክ ላይ ባለፈው ሳምንት ስምምነት መፈጸማቸውን ገልጸዋል። ስምምነቱ በመፈጸሙም ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮች በአዲሱ ልዑክ ውስጥ የመካተታቸውን ጉዳይ " እንደገና እንደምታጤን "  ባለስልጣኑ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የፈጸመችውንና የባሕር በርን የተመለከተውን የመግባቢያ ስምምነት የማትሰርዝ ከሆነ የኢትዮጵያ ወታደሮች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ሶማሊያ ስትጠይቅ ቆይታ ነበር። ሶማሊያ ይህን ብትልም ኢትዮጵያ ግን በሶማሊያ የሚገኙት ወታደሮቹ አል ሻባብን መዋጋት እንደሚቀጥሉ ሲያስታውቃ ነበር። የኢትዮጵያ ትኩረት ' አል ሻባብ ' ላይ መሆኑን የኢትዮጵያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በቅርቡ አስታውቀው ነበር። የኢትዮጵያ 🇪🇹 ወታደሮች ለሶማሊያ ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋት የደም ዋጋ ከፍለዋል ፤ ዛሬም ድረስ እየከፈሉ ነው።  ኢትዮጵያ ለሱማሊያ ያልከፈለችው መስዕዋትነት የለም ፤ ይህ ውለታ ተረስቶ ነው የሶማሊያው መሪ ሀሰን ሼክ መሀሙድ አስተዳደር ስለ ኢትዮጵያ መከላከያ ብዙ የሚያስተዛዝብ ንግግር ሲናገር የከረመው። በአንካራው ስምምነት ፕሬዜዳንቱ ፤ ሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለሀገራቸው (ሶማሊያ) ለከፈሉት መስዋዕትነት በይፋ እውቅና ሰጥተዋል።

"የእኔ መማር ብቻ በቂ አይደለም !"አሉ የደሴ ከተማ 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ታዳጊዋ ነጃት አህመድ ትባላለች ነጃት የዘጠኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን በደሴ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳትፎ ባደረገችበት ወቅት ነው ያገኘናት ። ጠይሟ ደግሞም ፈገግታዋ የሚገባው ታዳጊ ነጃት የትውልድ አጋርቿ የነገ እጣ ፈንታ ያሳሰባት ይመስላል እኔ የምኖርበት ከተማ ደሴ ትምህርት አልተቋረጥምነገር ግን በአማራ ክልል በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ መማር አልቻሉም፤ ይህ ደግሞ ያሳዝናል ሁሉም ለእነዚህ ተማሪዎች ሊደርስላቸው ይገባል ስትል የሰላም ጥሪን አቀረበች። በዚህ አላበቃችም እኛ ብቻ ሳንሆን እነሱም ሊማሩ ይገባል ያለችው ነጃት በክልሉ ያለው የሰላም እጦት ለመሰሎቿ የትምህርት መሰናክል በመሆኑ ሁሉም ለሰላም ዋጋ መስጠት አለበት የሚል መልዕክቷን አስተላለፋለች ። የደሴ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጫኔ መንገሻ፣ ወ/ሮ መብራት ፈለቀ እና አቶ አህመድ ሙሀመድ የሰላም እጦት በርካታ ፈተና እንድናሳልፍ አድርጎናል የሰሜኑ ጦርነት በበርካታ ሰቆቃና ችግር ዳርጎን አልፏል ይህ በወንድማማቾች መካከል የሚደረግ ጦርነት ሊቆም ይገባል ለሰላም ሁሉም ዘብ እንቁም የሚል ጥሪን አቅርበዋል። አቶ ጫኔ መንገሻ የጦርነት ዳፉው በቀላሉ የሚለቅ አይደለም የሚሉት አቶ ጫኔ ንፁሃን ለህልፈት ተዳርገዋል የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውም በእጅጉ ተዳክሟል ሰላም የብዙ ነገር መፍቻ በመሆኑ ከዚህ ሁኔታ ክልሉ እንዲወጣ እንፈልጋለን ብለዋል። የታጠቁ ሀይሎችም የመንግስት ተደጋጋሚ ጥሪ ተቀብለው ችግሮች ቢኖሩ እንኋ በሰላም እንዲፈቱ እንጠይቃለን ብለዋል አቶ ጫኔ መንገሻ። ወ/ሮ መብረት ፈለቀ በበኩላቸው ሰላም በመታጣቱ እናቶች በወሊድ ምክኒያት እየሞቱ ፣ የህክምና አገልግሎትም ማግኘት አስቸጋሪ ሁኗል ብለው የመኸር ወቅት ላይ በቅናሽ የአመታዊ ፍጆታ ሸመታ የሚደረግበት ጊዜ መሆኑን አንስተው አሁን ላይ ግን በጦርነቱ ምክኒያት ምርት ማግኘት ባለመቻላችን የኑሮ ውድነት ችግር ላይ ጥሎናል ነው ያሉት። እነዚህ ችግሮቻችን መፍትሄ የሚያገኙት ሰላሙ ወደ ቀደመው ሲመለስ የታጠቁ ወገኞችም ለሰላም ጥሪ ምላሽ ሲሰጡ በመሆኑ የሰላም መንገድን ለህዝቡ ሲሉ ትጥቅ ፈተው ወደ ህዝባቸው በሰላም ይቀላቀሉ ብለዋል። ሀገር ተረካቢ ተተኪ ትውልድ ያስፈልጋል ያሉት ወ/ሮ መብራት ትውልድ በትምህርት መጓተት መባክን የለበትም ብለው ሰላሙን ለማምጣት ሁሉም የበኩሉን ሀላፊነት ይወጣ ፣ሰላምን እንደግፋለን፣ ጦርነትን እንቀቃወማለን፣ ለሰላም ሁሉም ዘብ መቆም አለበት የሚል ጥሪያቸውን አቅርበዋል ። ሰላም የልማት በር ነው ሰላም ከጠፋ አለም እንደጠፋ ይቀጥራል የሚሉት ሌላኛው የደሴ ከተማ ነዋሪ አቶ አህመድ ሙሀመድ ሰዎች ከቤት ወጥተው መግባት አልቻሉም ነጋዴዎች እንድልባቸው ተንቀሳቅሰው መስራት አልቻሉም ይህ ደግሞ የክልሉንም የከተማዋንም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በእጅጉ አዳከመው ነው፤ መፍትሄ በሌለው ጦርነትን ህዝብን ለሶቆቃና እንግልት ከመዳረግ የሰላም መንገድን በሰለጠነ አግባብ መጠቀም ይገባል ነው ያሉት። ሰላምን ለሁሉም ሊባል ይገባል መንግስት በህግ ማሰከበር ዘመቻ ወቅት ለንፀሀን ልዩ ጥበቃ እንዲያደርግ ማደረግ አለብትም ብለዋል አቶ አህመድ የደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው በጫካ የሚገኙ ፅንፈኞችን መንግስት በተደጋጋሚ የሰላም በሩን ከፋቶ በሰጠው እድል ተጠቃሚ የሆኑ እንዳሉ ሁሉ አሁንም ኋላ ቀር የአሁኑን ትውልድ የማይመጥን ትግል ከማድረግ ተመለሱ ፤ በከተማችንም ይህን እኩይ ተግባር በተለያየ አግባብ ገብቷችሁም ሳይገባችሁም የሎጀስቲክ ድጋፋ የምታደርጉ የምደግፉ ግለሰቦች በፍጥነት ታረሙ አቁሙ ፤ ይህ ካልሆነ ለህዝባችን ሲባል አስተማሪ ርምጃ ህግ ማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የርስ በርስ ጦርነት ቁሞ ችግሮችን በሰላም መፍታት ይገባል ብለው የህዝባችን እውነተኛ ፍላጎት ሰላም ነው የንብረት ውድመት ፣አሰቃቂ የዜጎች ግድያ እንዲሁም ወደ ትምህርት ቤቶችን የማይሄዱ ተማሪዎች ላይ የትውልድ ብክነት እንዳይፈጠር ለአማራ ህዝብ ሰላም የሚያስብ ወደ ሰላም መጥቶ በውይይት በሰላማዊ ምክክር ችግሮቻችን እንፍታ ሲሉ ጠይቀዋል። አማራ ክልል ወደ ሰላምና መረጋጋት እንዲመለስ እንፈልጋለን ያሉት ተማሪ ነጃትና የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ሁሉም ለሰላም ፊቱን ሊያዞር ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ደሴ ህዝብ በቃን አለ
+9
ደሴ ህዝብ በቃን አለ

በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ አጭበርባሪዎች በዝተዋል፤ ይጠንቀቁ! ****** አጭበርባሪዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመርን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም የተለያዩ ማጭበርበሪያ ዘዴዎችን ተጠቅመው የመረጃና ገንዘብ ምዝበራ በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡ አጭበርባሪዎች ከሚጠቀሙባቸው ዘዴዎች ጥቂቶቹን እና መከላከያ መንገዶችን እንጠቁማችሁ፡፡ 1.  ፊሺንግ (Phishing) በዚህ የሶሻል ምህንድስና ጥቃት አጭበርባሪዎች ማኅበራዊ ሚዲያን ጨምሮ በተለያዩ ዲጂታል የመልእክት መለዋወጫ መንገዶች ሀሰተኛ መልእክቶችን በመላክ ተጠቃሚዎች የግል እና ሌሎች እንደ ሂሳብ፣ የይለፍ ቃል የመሳሰሉ መረጃዎቻቸውን አሳልፈው እንዲሰጡ፣ እንዲሁም አደገኛ ሊንኮችን እንዲከፍቱ እና ሶፍትዌሮችን እንዲጭኑ ያደርጋሉ፡፡ 2.  የኢንቨስትመንት ማጭበርበሮች (Investment Scams): የውሸት በሆኑ ወይም በሌሉ ምርቶች ወይም ንግዶች ላይ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያበረታቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ማስታወቂያዎች ተበራክተዋል። ብዙዎችም የምዝበራ ሰለባ ሆነዋል፡፡ 3.  ነፃ የሙከራ አገልግሎቶች (Free Trial Products): በሀሰተኛ የምርቶች ነጻ ሙከራ (Free-trial) ማስታወቂያ ሰዎችን በማታለል  ለነጻ የምርት ሙከራው እንዲመዘገቡና  የክፍያ ካርድ  መረጃቸውን እንዲያስገቡ የማድረግ ማጭበርበሪያ ዘዴ ነው፡፡  ተጠቂው ከሱ እውቅና ውጪ ውል ውስጥ በመግባቱ  ምክንያት ክፍያ ያለባለቤቱ እውቅና ተቀናሽ ይሆናል። 4.  የኦንላይን ግብይት ማጭበርበሮች በኦንላይን ግብይት የተለያዩ ምርቶችን በቅናሽ እንሸጣለን በሚል የምዝበራ ተግባር ላይ የተሠማሩ አጭበርባሪዎች አሉና ይጠንቀቁ፡፡ 5.  ክሊክቤይት (Clickbait)፡ ይህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተጠቃሚዎችን ትኩረት የሚስቡ ጉዳዮችን የያዙ ይዘቶችን በማውጣት ተጠቃሚዎች ይበልጥ ለማወቅ ሊንኩን እንዲጫኑ የማድረጊያ ዘዴ ነው፡፡ ይህን ዘዴ አጭበርባሪዎች ሲጠቀሙበት ተጠቂው ጥቃት አድራሾቹ ወደ ሚመሩት ማስፈንጠሪያ በሚገባበት ጊዜ የግል መረጃውን አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል። 6.  የውሸት ጓደኛ ጥያቄዎች (Fake Friend Requests)፡ አጭበርባሪዎች የማኅበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን በመክፈት ወይም  የሌሎችን አካውንቶች በመጥለፍ  ወደተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የጓደኝነት ጥያቄ ይልካሉ። እነዚህን ጥያቄዎች መቀበል የእርሶን እና የጓደኞቻችሁን መለያ እንዲጠለፍ እና የግል መረጃ እንዲያፈተልክ ያደርጋል። 7.  የሥራ እድል ማጭበርበሮች ሀሰተኛ የስራ እድል ማስታወቂያዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ በስፋት ይተዋወቃሉ። ገቢዎን ያሳድጉ ወይም ከቤት ሆነው ሥራ ይስሩ በማለት አጓጊ ጥቅማጥቅሞችን በመንገር ተጠቃሚው ቶሎ ውሳኔ እንዲወስን (sense of urgency) በማድርግ ማጭበርበሩን ይፈጽማሉ። እነዚህ አጭበርባሪዎች የተጠቃሚውን መረጃ የግል እና ሊሎች መረጃዎች ይወስዳሉ ወይም ለሥልጠና ወይም ለሌላ ጉዳይ በቅድሚያ ክፍያ ይጠይቃሉ። 8.  ስጦታ በራሳቸውም ሆነ የሌሎችን ስምና ዝና በመጠቀም ሀሰተኛ የማኅበራዊ ሚዲያ ገፆችን በመክፈት ተከታይ ስትሆኑ፣ ተከታይ ስታስገቡ፣ ልጥፎችን ስታጋሩ፣ አስተያየት ስትሰጡ፣ ስትወዱ ስጦታ እንሰጣለን በሚሉ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች ያጭበረብራሉ፡፡ እነዚህ አጭበርባሪዎች የተከታዮችን ግላዊ መረጃ ለመውሰድ መልካም አጋጣሚ ይሆንላቸዋል፡፡  እንዴት ከአጭበርባሪዎች ራሳችንን እንጠብቅ? •  ከማያውቁት ግለሰብ የሚደርስዎትን የማኅበራዊ ሚዲያ እንወዳጅ ጥያቄ አይቀበሉ፡፡ •  የቅናሽ ማስታወቂያዎችን በጥርጣሬ ይመልከቱ፤ •  በኦንላይን ብቻ ለተዋወቁት ግለሰብ ገንዘብ አይላኩ፡፡ •  በማኅበራዊ ሚዲያ የግል መረጃዎን አይስጡ። •  የማስታወቂያ አስነጋሪዎችን ህጋዊነት ሳያረጋግጡ ምንም አይነት እርምጃ አይውሰዱ፡፡ •  ከማህበራዊ ሚዲያ ጓደኛ የሚመጣን የእርዳታ ጥሪ በጥንቃቄ ይፈትሹ። •  ከማያውቁት አካል በሚደርስዎት አጭር የፅሁፍ መልእክት፣ ኢሜይል ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ መልእክት የሚያገኙትን ማስፈንጠሪያ (link) አይክፈቱ፡፡ •  ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችን ይከተሉ፡፡

ኢትዮ-ኮንጎ‼ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሽርክና ያቋቋሙት የኮንጎ አየር መንገድ ሥራ ጀመረ። የኮንጎ አየር መንገድ በሁለት ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች በዴሞ
ኢትዮ-ኮንጎ‼ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሽርክና ያቋቋሙት የኮንጎ አየር መንገድ ሥራ ጀመረ። የኮንጎ አየር መንገድ በሁለት ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ውስጥ ባሉ ሰባት ኤርፖርቶች በረራ በማድረግ አገልግሎት መጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋ ያደረገው ትናንት ማክሰኞ ነው።  በኮንጎ አየር መንገድ ውስጥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 49 በመቶ፣ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት 51 በመቶ ድርሻ አላቸው። ሁለቱ ሸሪኮች የተፈራረሙት ሥምምነት የአውሮፕላን ኪራይ እና አጠቃላይ ቴክኒካዊ ድጋፍን እንደሚያጠቃልል የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።  በስምምነቱ መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዜጎች የአውሮፕላን አብራሪዎች፣ የበረራ አስተናጋጆች፣ የአገልግሎት ሠራተኞች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች እንዲሆኑ ያሰለጥናል።

በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 09 ቀን 2017 ዓ.ም ህዝባዊ ሰልፎቹ በበርካታ የክልሉ ከተሞች እየተካሄዱ ሲሆን መንግሥት እያካሄደ ያለውን ሕግ የማስከበር ዘመቻ የሚደግፉ መልዕክቶችም እየተላለፉ ይገኛሉ፡፡ ሰልፈኞቹ የመንግስትን የሰላም ጥሪ እንደግፋለን፣ ፅንፈኛ ሃይሎች ለህግ ይቅረቡልን፣ ክልላችንን የሰላምና የልማት ማዕከል ለማድረግ ሁላችንም ለሰላም ዘብ እንቆማለን፣ መንግስት ለሰላም መስፈን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች እንደግፋለን ለመከላከያ ሠራዊታችን ክብር እንሰጣለን የሚሉና ሌሎች መልዕክቶች እያስተላለፉ ነው። ለክልላችን የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይሆን ሰላምና ልማት ነው፣ መከላከያ ሠራዊታችን፣ የፌዴራልና የክልላችን የጸጥታ ኃይሎች ለከፈሉት ዋጋ ክብር እንሰጣለን የሚሉትን ጨምሮ ሌሎች መፈክሮችም ይገኙበታል፡፡ የሐይማኖት አባቶችን ጨምሮ የመንግሥት ሠራተኞች እና ተማሪዎችን ባካተተው በበርካታ አካባቢዎች የተካሄደው ሰልፍ ላይ ሀገር አፍራሹ ፅንፈኛ ቡድን በቃህ ሊባል ይገባል ትውልድ ገዳይ የሆነ አመለካከቱን አሥተካክሎ ወደ ሠላም መምጣት እንዳለበትም ተገልጿል።