የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
الذهاب إلى القناة على Telegram
5 576
المشتركون
-40724 ساعات
-2 4147 أيام
-2 42630 أيام
أرشيف المشاركات
አል-ሲሲ ምን እያሉ ነው ?
ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ከባህር በር ጋር በተያያዘ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ ማግስት አንስቶ ከሶማሊያው መሪ ጋር እየተደዋወሉ እና እየተገናኙ ፦
" ° አይዟችሁ እኛ አለን ፤
° ከፈለጋችሁ ወታደርም እንልካለን ፣
° የጦር መሳሪያ ድጋፍም ይኸው፣
° በሰላም ማስከበርም እንሳተፋለን ፣
° እናተን ማንም እንዲነካ አንፈቅድም " እያሉ ሲለፍፉ የከረሙት የግብጹ መሪ አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ አሁን ደግሞ የአንካራውን ስምምነት " በቅርበት እየተከታተልን ነው ፤ መረጋጋትንም ሊያመጣ ይችላል " የሚል ዲስኩር ይዘው ብቅ ብለዋል።
ድሮውንም የኢትዮጵያ ነገር አይኗን የሚያቀላው ግብፅ ከመግባቢያ ስምምነቱ (MoU) በኃላ ስለ ኢትዮጵያ ብዙ አሉታዊ ነገር ስታወራ ፣ የማጠልሸት ስራ ስትሰራ ነበር የከረመችው።
ትላንት የግብፁ መሪ አል-ሲሲ በቅርብ ኢትዮጵያ መጥተው ከነበሩትና የኢትዮጵያ የባህር ባር ጥያቄን በይፋ ከደገፉት የፈረንሳዩ ፕሬዜዳንት ማክሮን ጋር የስልክ ውይይት አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት ፥ አል ሲሲ በቱርክ አሸማጋይነት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የፈረሙትን ስምምነት ጠቅሰው " በቅርብ እየተከታተልን ነው ፤ ስምምነቱ በአፍሪካ ቀንድ ፀጥታ እና መረጋጋት ሊያመጣ ይችላል " ሲሉ ተናግረዋል።
" ይህ ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት እንደሚያመጣ ተስፋ አለኝ ዓለም አቀፍ ሕግን ተከትሎ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ቀንድ ያለው መረጋጋት እና የግብፅ ብሔራዊ ጥቅምት የተሳሰሩ ናቸው " ሲሉ እንደገለጹም ተነግሯል።
አል-ሲሲ " ለሶማሊያ ድጋፍ ለማድረግ እንሰራለን ይህ ድጋፍ በሁለትዮሽ ግንኙነት አሊያም በአፍሪካ ሕብረት የሰላም አስከባሪ ሚሽን አማካይነት ነው " ብለዋል።
ግብፅ ፤ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ቁርሾ ውስጥ በከረሙበት ወራት ስታወጣ የነበረው መግለጫና ስታደርግ የነበረው እንቅስቃሴ ሀገራቱን ወደ መግባባትና ሰላም እንዲመጡ ለማድረግ ሳይሆን ነገሩን ለማጋጋል ፣ ለማባባስ ፣ የለየለት ቀውስና ጦርነት እንዲፈጠር ለማድረግ የታስበ እንደሆነ አመላካች እንደነበር ብዙዎች የሚገልጹት ነው።
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
9 አዲስ የብሪክስ አባል ሀገራት!!
በፈረንጆቹ 2025 መባቻ ብሪክስ ዘጠኝ ሀገራትን በአባልነት እንደሚቀበል ተገልጿል፡፡
ሀገራቱም ቤላሩስ፣ ቦልቪያ፣ ኢንዶኖዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ኩባ፣ ማሌዥያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤከስታን መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የብሪክስ አባል ለመሆን ከ30 በላይ ሀገራት ጥያቄ አቅርበው እንደነበር የሚታወስ ነው።
ከነዚህም ዘጠኙ በሩሲያ ካዛን በተካሄደው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የአባልነት ጥያቄያቸው ፀድቋል፡፡
በቅርቡም ተጨማሪ አራት ሀገራት ብሪክስን ይቀላቀላሉ ተብሏል፡፡
አዳዲስ አባል ሀገራት ሲቀላቀሉ ብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን የአባላቱን ቁጥር ወደ 18 አድጓል ።
ኢትዮጵያም ከዚህ ቀደም ከነበሩት ዘጠኝ አባል ሀገራት አንዷ መሆኗ የሚታወቅ ነው።
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
የዚያድባሬ መንግስት - በኢትዮጵያ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
ሶማሊያን ለ21 ዓመታት ያስተዳደሩት ዚያድባሬ ታላቋን የሶማሊያ ሪፐብሊክ ለመመስረት በሚል መነሻ ድንበራችን እስከ አዋሽ ይደርሳል ብለው በመዛት በኢትዮጵያ ላይ የጦርነት ነጋሪት ጎሰሙ። ወራሪው የዚያድባሬ መንግስት በ1969 ዓ.ም በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ግዙፍ ጦር አሰማርቶ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በመዳፈር በጥልቀት እስከ ሐረር ድረስ በመዝለቅ ጦርነት ከፈተ፡፡
በወቅቱ የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት፣ ከሶስት መቶ ሺህ በላይ ሠራዊት በአፋጣኝ ክተት በታጠቅ ማሠልጠኛ በማሠልጠን የወራሪውን ኃይል በመፋለም በከፍተኛ ድል የዚያድባሬን የወረራ ፍላጎት ማምከን ችሏል። የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጦር የእብሪተኛውን የዚያድባሬ ጦር ካራ ማራ ላይ ድል በማድረጉ የኢትዮጵያ አሸናፊነት በአደባባይ ታውጇል።
በጦርነቱ የኢትዮጵያን ትንሳኤ በታላቅ መስዋዕትነት ያበሰሩ የአድዋን የጀግንነት ድል ዳግም ያረጋገጡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ተፈጠሩ።
ጦርነቱ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባውን ወራሪውን የሶማሊያ ጦር ከአገር ለማስወጣትና ድል ለማድረግ በመሆኑ የሕይወት መስዋዕትነት በመክፈል የኢትዮጵያን ክብር ማሥጠበቅ ተችሏል። አይነኬ የአፍሪካ ኩራት የሆነችው ሀገራችን ያለመደፈር ታሪኳን አድሳለች። በወዳጅ ሀገራት ዘንድ ተወድሳለች።
ድሉ ኢትዮጵያ ወራሪውን ሃይል በማሸነፍ ዳግም ነጻነቷን ያወጀችበትና ኢትዮጵያዊያን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍለው ሉዓላዊነታቸውን ያስጠበቁበት እንደሆነም ተረጋገጠ። ታሪካችንን በአድዋ ድል ያወቁ ሁሉ የካራማራውን ድልም አውቀዋል።
ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች ኩራት ከመሆኗ በዘለለ ለማንኛውም ጠላት የማይንበረከኩ ጀግኖችን በየዘመናቱ የምታፈራ ሀገር መሆኗ በካራማራው ድል ተመሠከረ።
ታላቋን ሶማሊያ እንመሠርታለን በሚል የተዛባ ስሌት ይበጀኛል የሚላቸውን ወዳጅ ሀገራት ድጋፍ ይዞ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ሰፊ ግዛታችን ላይ ወረራ ለመፈፀም የሞከረው የዚያድባሬ መንግስት ሃሳቡ ሳይሳካ ከሸፈ ሩቅ ሳይጓዝ ህልሙ በከንቱ መክኖ ውድቀቱን አፋጥኗል።
ሶማሊያ ከዚያድባሬ መንግስት ውድቀት ወዲህ ሠላም የራቃት በተለይም ደግሞ የምስራቅ አፍሪካ አሸባሪ ቡድን በሆነው አልሻባብ ሠላሟን እየተገፈፈች በአጥፍቶ ጠፊዎች ዜጎቿን እየተነጠቀች የአሸባሪው መፈንጫ ሆና በሁለት እግር መቆም ተስኗት ሠላም እንደናፈቃት እነሆ ዛሬ ላይ ደርሳለች።
ከዚያድባሬ ውድቀት በኋላም ሶማሊያ ሠላሟን አጥታ እርስ በእርሷ ስትታመስ ኢትዮጵያ የጉርብትናዋ መገለጫ የሆነውን ሠላም ለማረጋገጥ የአለሁልሽ ድምጿን አሠምታለች። ለሶማሊያ ህዝብ ሠላም ሠርታለች በተግባርም አረጋግጣለች።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት - የኢትዮጵያ ልክ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
👉 መከላከያ ሠራዊት በሠንደቅ ዓላማው ፊት ለገባው ቃልኪዳን መቼም የትም በፅናት የሚቆም የኢትዮጵያ ልክ ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት ምንግዜም ለሕዝብና ለሀገር ጥቅም ቅደሚያ የሚሰጥ የሕዝብና የሀገርን ጥቅም የሚፃረሩ ተግባራትን በሙሉ ለማክሸፍ ሌት ተቀን የሚተጋ ኃይል ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት-የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የመጨረሻ ምሽግ በመሆኑ ሰራዊቱን ማክበር ኢትዮጵያን ማክበር ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት የቴክኖሎጂ መፍለቂያ እና የልማት ሀይል ነው
👉 መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያ በዘመናት ውስጥ የገጠሟትን እና የሚገጥሟትን ፈተናዎች ድል በማድረግ ከፍታዋን አስጠብቆ ያኖረ እና የሚያኖር ሠራዊት ነው።.
👉 የመከላከያ ሠራዊት ደስታና ስኬት የኢትዮጵያ ክብር እንዳይደፈር በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ ውስጥ ስለ ክብሯ ከፊት መቅደም ነው።
👉 የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ለሃገሩም ሆነ ለዓለም አቀፍ ሰላም መከበር መስዋዕትነት የሚከፍል ሰራዊት ነው።
👉 የሀገር መከላከያ ሠራዊት ማንኛውንም ዋጋ ከፍሎ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማስከበር ዝግጁ ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት በመላው ሀገሪቱ የሚኖሩ ህዝቦች ላይ የሚቃጣን ፍላፃ ሁሉ ውድ ዋጋ ከፍሎ የሚመክት የኢትዮጵያ ምልክት ነው።
👉 መከላከያ ታሪክ ጠገብ ተቋም እና ታሪክ እየሰራ ያለና ኢትዮጵያን እያጸና የሚቀጥል የጀግንነትና የልማት ተምሳሌት ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ እና በዓለም የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ብቃቱን ያስመሰከረ ሠራዊት ነው።
👉 መከላከያ ሠራዊት ደሙን የሚያፈሰው አጥንቱን የሚከሰክሰው ህይወቱን የሚሰዋው ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማጽናት ነው።
+1
ኢትዮጵያ የሶማሊያ መንግስት ያቀረበባትን ክስ መሰረተ ቢስ ስትል አጣጣለች
የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣዉ መግለጫ የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ኃይሎች በሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ላይ ጥቃት አድርሰዋል በሚል ያቀረበዉን ክስ አጣጥሏል፡፡
ድርጊቱ የተፈፀመዉ ኢትዮጵያ ኃይሎች ሳሆን የሁለቱን አገራት ግንኙነት ለማበላሸት በሚፈልጉ ሶስተኛ ወገኖች የተፈጸመ ነዉ ብሏል፡፡
ኢትዮጵያ መሰል ትንኮሳዎችና የሁለቱን አገራት ግንኙነት የሚያበላሹ ድርጊቶችን ለመከላከል ቁርጠና መሆኗንም አረጋግጣለች፡፡
የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ዱሎው በተባለችው የጁባላንድ ከተማ የኢትዮጵያ ኃይሎች ጥቃት ፈፅመዋል ሲል መዉቀሱ የሚታወስ ነዉ፡፡
ታኀሣሥ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
ሩሲያ በ10 ሀገራት የኒዩክሌር ሃይል ማመንጫዎችን እየገነባች ነው፡፡
ሩሲያ በኒዩክሌር ሃይል ማመንጫ ግንባታ የአለማችን ቀዳሚዋ ሀገር ለመሆን እየሰራች መሆኑን አስታውቃለች።
በክሬምሊን የዘላቂ ሃይል አለማቀፍ ትብብር ልዩ መልዕክተኛው ቦሪስ ቲቶቭ እንደገለጹት፤ ሃገሪቱ በቻይና፣ ግብጽ፣ ህንድ፣ ኢራን እና ቱርክን ጨምሮ በ10 ሀገራት እየተገነቡ የሚገኙት የኒዩክሌር ሃይል ማመንጫዎች ሩሲያን በዘርፉ ቀዳሚ ያደርጋታል።
ሩሲያ በዩክሬን በጀመረችው ጦርነት ምክንያት የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ የወጪ ንግዷ ከፍተኛ ማዕቀብ ቢጣልበትም በኒዩክሌር ሃይል ማመንጫዎች ግንባታ ቀዳሚዋ ሆና ቀጥላለች።
ልዩ መልዕክተኛው ቦሪስ ቲቶቭ፥ ሩሲያ ከዩራኒየም ሽያጭ ብቻ ሳይሆን በኒዩክሌር ሃይል ማመንጫዎች ግንባታ የአለማችን ቀዳሚዋ ሀገር መሆን የሚያስችላትን ስራ እየከወነች ነው ብለዋል።
የሩሲያው ሩሳቶም ከኒዩክሌር ማብለያዎች ግንባታ እና ሌሎች አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ከ54 ሀገራት ጋር እንደሚሰራ የኖርዌይ የአለማቀፍ ጉዳዮች ተቋም ያወጣው መረጃ ያሳያል።
ፋይናንሽያል ታይምስ በበኩሉ በአሁኑ ወቅት በመላው አለም እየተገነቡ ከሚገኙ የኒዩክሌር ማብለያዎች ውስጥ ሲሶው በሩሲያ እንደሚከናወን መዘገቡ ይታወሳል።
Via : አለ-ዐይን
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
የሶማሌላንድ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ።
የሶማሌላንድ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር አብደል መሐመድ አረብ በሶማሌላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ከተሾመ ሹንዴ ጋር በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ወይይት አካሂደዋል።
አምባሳደር ተሾመና የደህንነት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ በሁለቱ ሀገራት የጸጥታ ጉዳዮችና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ አጠቃላይ ፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸውን ሸገር ታይምስ ሚዲያ ከሶማሌላንድ ብሄራዊ ጣቢያ የተመለከተው መረጃ ይጠቁማል።
በውይይታቸው በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ መንግስት እና በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግስት መካከል ያለውን የጋራ የጸጥታ ትብብር ለማጠናከርና በጋራ መስራት እንደሚገባም መስማማታቸውንም ነው ዘገባው የጠቆመው።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በአዲስ አበባ የነበራቸው ቆይታ ከአጼ ሚኒሊክ ጀምሮ አጼ ሃይለስላሴ ኮሎኔል መግስቱ ሃይለማሪያም እና አቶ መለስ ዜናዊ በቤተ መንግስት ይጠቀሙብቸው የነበሩ መኪኖችና ቁሳቁሶች የተተያዩ የአለም መንግስታት ለነገስታቱ የሸለሟቸውን ሽልማቶችና ሎችም ጥንታዊና ታሪካዊ ነገሮችን ብክብር ተቀምጠው ጎብኝተዋል::
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
